Telegram Web
ለአዲስ ገቢ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች!

ደብረ ብርሃን ምን አይነት ጊቢ ነው? የከተማው አየሩ ፀባይስ? እውነት እንደሚባለው ቀዝቃዛ ነው? ማህበረሰቡስ? ምግብስ የጊቢውና የውጪው እንዴትነው? ዋጋውስ? የአካባቢው ጊዜያዊ ፀጥታ ሁኔታ? የእምነት ተቋማት አሉ ወይ? እያላችው እያሰባችሁ እንደሆነ አንጠራጠርም ።

እነዚህን ጥያቄዎች  DBUDAILY  ከሞላ ጎደል ሊመልስላችሁ ወደደ።

ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ  በ1999ዓ.ም ከተቋቋሙት ሁለተኛ ትውልድ አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ነው። ግቢው አሁን ላይ በሁለት ካምፓስ (ጤና ካምፓስ እና ዋና ካምፓስ ) ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል።

በግቢው ውስጥ 4 ላይብረሪዎች አሉ። የሴቶች ላይብረሪ /ለሴቶች ዶርም በጣም ቅርብ የሆነና ብዙ ጊዜ በሴቶች ተመራጭ ላይብረሪ ነው።/፣ከበደ ሚካኤል ላይብረሪ (የsocial ተማሪዎች ላይብረሪ በመባል ይታወቃል።) የህግ ተማሪዎች ላይብረሪ ፣ተስፋገብረስላሴ ላይብረሪ (ዋና ላይብረሪ) በስፋቱም በይዘቱም ከሌሎቹ
የተሻለ ነው።

ይቀጥላል ...

@dbu11
@dbu111
👍36👎12😁1
ለአዲስ ገቢ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች!
.
.
.
የደብረብርሃን ማህበረሰብ በባህሉ ሰው ወዳድ፣ እንግዳ ተቀባይ ማህበረሰብ ነው።

የምግቡን ነገር እንመልከት፦ ከካፌው ስንጀምር
የካፌው ምግብ ከአብዛኛው የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ካፌዎች ጋር ተመሳሳይ ነው። ነገር ግን የተለየ የጤና ችግር ያለባችሁ ከሆነና  የህክምና ማስረጃ ማቅረብ የምትችሉ ከሆነ  special cafe መመገብ ይፈቀድላችኋል። ከnormal cafe የተሻለ እዛ ይገኛል።

ከዛም በተጨማሪ በግቢው ውስጥ  3 lounge  ታገኛላችሁ ዋጋቸውም ከ50-80 እንደምግብ አይነቱ ያወጣሉ። ከዛ በተሻለ እዛው ግቢ ውስጥ መገዘዝ እንዲሁም ማርካን የተባሉ የግል ካፌዎች አሉ። ዋጋቸውም ከ60-90 ያወጣሉ።

እነዚህም ተስማሚ ካልሆናችሁ ከግቢ አቅራቢያ የሚገኙ ግን ከግቢ ውጪ ምግብ ቤቶች  አሉ።  ዋጋቸውም በአማካኝ ከ70-120 እንደምግብ አይነቱ ያወጣሉ። በኮንትራት ከሆነ ደግሞ 10 ና 15 እንደየቤቱ ቅናሽ ያረጋሉ።

የአካባቢው የፀጥታ ሁኔታን ስንመለከት አሁን ላይ(ህዳር 2017)ከተማዋ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ስትሆን የባጃጅ አገልገሎት  በከተማዋ ከ12 ሰዓት በኃላ አገልግሎት አይሰጡም። እንዲሁም ምንም አይነት መኪናዎች ከ2ሰዓት በኃላ አይንቀሳቀሱም። በተጨማሪም እግረኛ መንቀሳቀስ የሚችለው እስከ 4 ሰዓት ድረስ ነው።
 
ወደ እምነት ተቋማት ስናልፍ  የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና ገዳማት በዩኒቨርስቲው አቅራቢያ ለማግኘት በጣም ቀላል ነው። እንዲሁም ከግቢው በስተጀርባ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዬች ቤተክርስቲያን እናም ለእስልምና እምነት ተከታዮች መስኪድ አሉ።

መልካም የትምህርት ዘመን!😊

@DBU11
@DBU111
👍39😁14👎2
የ2017_ዓ_ም_የአዲስ_ተማሪዎች_የህንጻ_እና_የዶርም_ድልድል.xlsx
112.7 KB
በ2017 ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች የወጣ የዶርም ድልድል

@DBU11
@DBU111
👍4
በ_2017ዓ_ም_አዲስ_ለሚገቡ_ተማሪዎች_ንብረትዶርም_የሚያስረክቡ_ሰራተኞች_ስም_ዝርዝር.docx
20.3 KB
2017 ለሚገቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ዶርም የሚያስረክቡ ሰራተኞች ስም እና ስልክ ቁጥር ዝርዝር

@DBU111
@DBU11
👍10😁3
እንኳን ደህና መጣችሁ!

ከዛሬ ቀን 17/03/2017 ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲያችን ለምትቀላቀሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች እንኳን ደህና መጣችሁ!

ውድ ተማሪዎች
በጉዞ ሂዲት እንደባለፉት ዓመታት ተማሪዎችን የሚቀበል በዩኒቨርሲቲው የተመደበ መኪና አለመኖሩን አውቃችሁ ከአጭበርባሪዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁም በዚሁ አጋጣሚ ልንገልፅ እንወዳለን!

@DBU11
@DBU111
👍11
የተከለከሉ ስፍራዎች

ለነባር ተማሪዎች

አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ቅበላ ምክኒያት በማድረግ ብሎክ 1፣8፣9፣39፣40 መግባት የማይቻል መሆኑ ተገልፁአል።

@DBU11
@DBU111
😁25👍16
2025/07/12 23:38:43
Back to Top
HTML Embed Code: