#ሥላሴ_ኃይሌ መመኪያዬ ነው
በሥላሴ ስም ጠላቴ ሰይጣንን እክድዋለሁ
እግዚአብሔር ከዓለም በፊት በመንግሥቱ ነበረ እግዚአብሔር #በሦስትነቱ እግዚአብሔር በመለኮቱ አለ ከጎኅና ከጽባሕ ከብርሃናት መመላለስም በፊት እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ፡፡
{ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ}
#ሥላሴ_ማለት ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም #ሦስትነት ማለት ነው፡፡ #ሥሉስ_ቅዱስ ማለት ደግሞ ልዩ ሦስት ማለት ነው፡፡ #አብ ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣# ወልድም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣ #መንፈስቅዱስም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው።
#የእግዚአብሔር የአንድነትና የሦስትነት ባለቤት ስለሆነ #ሥላሴ ይባላል ።
#የአብረሃሙ_ስላሴ ከክፉ ይጠብቀን
ሀሳብ ምኞታችን ተሳክቶ በደስታ እንድንኖር ይርዳን አሜን
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
በሥላሴ ስም ጠላቴ ሰይጣንን እክድዋለሁ
እግዚአብሔር ከዓለም በፊት በመንግሥቱ ነበረ እግዚአብሔር #በሦስትነቱ እግዚአብሔር በመለኮቱ አለ ከጎኅና ከጽባሕ ከብርሃናት መመላለስም በፊት እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ፡፡
{ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ}
#ሥላሴ_ማለት ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም #ሦስትነት ማለት ነው፡፡ #ሥሉስ_ቅዱስ ማለት ደግሞ ልዩ ሦስት ማለት ነው፡፡ #አብ ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣# ወልድም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣ #መንፈስቅዱስም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው።
#የእግዚአብሔር የአንድነትና የሦስትነት ባለቤት ስለሆነ #ሥላሴ ይባላል ።
#የአብረሃሙ_ስላሴ ከክፉ ይጠብቀን
ሀሳብ ምኞታችን ተሳክቶ በደስታ እንድንኖር ይርዳን አሜን
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤13❤🔥2🙏2
🕊
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
[ የካቲት ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
[ † 🕊 በዓለ ስምዖን 🕊 † ]
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ጌታ በተወለደ በ፵ [40] ቀኑ ራሱ የሠራውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል:: እንደ ሥርዓቱም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አገልጋዩዋ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ አቅርበዋል::
ለ፪፻፹፬ [284] ዓመታት የአዳኙን [የመሢሁን] መምጣት ይጠብቅ የነበረው አረጋዊው ስምዖን በዚህች ዕለት ስላየውና ስለታቀፈው ዕለቱ በዓለ ስምዖን ይባላል:: [ሉቃ.፪፥፳፪] (2:22) ከዘጠኙ የጌታ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ከዓለም ፍጥረት በ፭ ሺህ ፪ መቶ [5,200] ዓመታት [ማለትም ከክርስቶስ ልደት ፫፻ [300] ዓመታት በፊት] በጥሊሞስ የሚሉት ንጉሥ በግሪክ ነገሠ::
በጊዜውም በኃይለኝነቱ ሁሉን አስገብሮት ነበርና "ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጬ: እንደ ገል ቀጥቅጬ ገዛሁት:: ምን የቀረኝ ነገር አለ?" ሲል ተናገረ:: ባሮቹም "አንድ ነገር ቀርቶሃል:: በምድረ እሥራኤል ጥበብን የተሞሉ ፵፮ [46] መጻሕፍት አሉ:: እነርሱን አስተርጉም" አሉት::
ያን ጊዜ እሥራኤላውያንን አስገብሯቸው ነበርና ፵፮ [46] ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ፸፪ [72] ምሑራን [ተርጉዋሚዎች] ጋር እንዲያመጡለት አዛዦቹን ላከ:: እነርሱም ፵፮ [46] ቱን መጻሕፍተ ብሉይ ኪዳን ከ፸፪ [72] ምሑራን ጋር አመጡለት::
አይሁድ ክፋተኞች መሆናቸውን ሰምቷልና ፴፮ [36] ድንኩዋን አዘጋጅቶ: ጥንድ ጥንድ ሆነው እንዲሠሩ: ሲተረጉሙ እንዳይመካከሩ ፴፮ [36] ጠባቂዎችን ሾመባቸው:: ይህ ነገር ለጊዜው ከንጉሡ ቢመስልም ጥበቡ ግን ከእግዚአብሔር ነው::
ምንያቱም በጊዜ ሒደት መጻሕፍተ ብሉያት በአደጋ እንደሚጠፉ ያውቃልና ሳይበረዙ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ለእኛ እንዲደርሱ ነው:: ስለዚህም ከክርስቶስ ልደት ፪፻፹፬ [284] ዓመት በፊት ፵፮ [46] ቱም ሁሉም መጻሕፍት [ብሉያት] ከእብራይስጥ ወደ ጽርዕ ልሳን በ፸ [70] ው ሊቃናት አማካኝነት ተተረጐሙ:: [በእርግጥ ከዚያ አስቀድሞ መጻሕፍት [ብሉያት] ወደ ሃገራችን መምጣቸውና ወደ ግዕዝ ልሳን መተርጐማቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው]
ወደ ዋናው ጉዳያችን ስንመለስ ከ፸ [70] ው ሊቃናት መካከል በእድሜው አረጋዊ የሆነ [እንደ ትውፊቱ ከሆነ ፪፻፲፮ [216] ዓመት የሆነው] ስምዖን የሚሉት ምሑረ ኦሪት ነበር:: በፈቃደ እግዚአብሔር ለእርሱ መጽሐፈ ትንቢተ ኢሳይያስ ደርሶት እየተረጐመ ምዕራፍ ፯ [7] ላይ ደረሰ::
ቁጥር ፯ [ 7 ] ላይ ሲደርስ ግን "ናሁ ድንግል ትጸንስ: ወትወልድ ወልደ" የሚል አይቶ "አሁን እንኳን የአሕዛብ ንጉሥ የእሥራኤልስ ቢሆን ድንግል በድንግልና ጸንሳ ትወልዳለች ብለው እንዴት ያምነኛል!" ሲል አሰበ:: "በዚያውስ ላይ ኢሳይያስ በምናሴ የተገደለው ስለዚህ አይደል!" ብሎ ቃሉን ሊለውጠው ወሰነ::
አመሻሽ ላይም 'ድንግል' የሚለውን 'ወለት-ሴት ልጅ' ብሎ ቀየረው:: እርሱ ሲያንቀላፋ ቅዱስ መልአክ ወርዶ 'ድንግል' ብሎ አስተካከለው:: ከእንቅልፉ ሲነቃ ግራ ተጋብቶ እንደ ገና ፍቆ ቀየረው::
አሁንም መልአኩ 'ድንግል' ሲል ቀየረበት:: ፫ [3] ጊዜ እንዲህ ከሆነ በኋላ ግን መልአኩ ተገልጦ ገሰጸው:: በዚያውም ላይ "ይህችን ድንግልና መሲሑን ልጇን ሳታየውና ሳትታቀፈው ሞትን አታይም" ብሎት ተሰወረው:: አረጋዊ ስምዖን ከዚያች ዕለት በኋላ የመድኅን ክርስቶስን መምጣት ሲጠብቅ ለ፪፻፹፬ [284] ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ኖረ:: አካሉም አለቀ::
ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በሆነበት በዚያ ሰሞን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ::
ሕግን የሠራ ጌታ እርሱ 'ፈጻሜ ሕግ' ይባል ዘንድ የርግብ ግልገሎችን [ዋኖሶችን] ይዘው በተወለደ በ ፵ [40] ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት:: በዚህች ቀንም ቅዱስ መልአክ መጥቶ ቅዱስ ስምዖንን ከአልጋው ቀሰቀሰው:: ተስፋ የሚያደርገው አዳኙ [መሲሑ] እንደ መጣም ነገረው::
ይህን ጊዜ አረጋዊው አካሉ ታድሶ እንደ ፪ [30] ዓመት ወጣት እመር ብሎ ከአልጋው ተነሳ:: እንደ በቅሎ እየሠገረም ወደ መቅደስ ወጣ:: በዚያ መሲሑን [ፈጣሪውን] ሲመለከት እንደ እንቦሳ ዘለለ:: ቀረብ ብሎም ሕጻን ጌታን ከድንግል እናቱ እጅ ተቀበለው::
ከደስታው ብዛት የተነሳም "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ: በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ሲል ጸለየ:: ትንቢትንም ተናገረ:: በዚያችው ዕለትም ዐርፎ ተቀበረ::
[ † 🕊 ሐና ነቢይት 🕊 † ]
ዳግመኛ በዚህች ቀን አረጋዊቷን ነቢይት ቅድስት ሐናን እናስባለን:: ይህች ቅድስት ትውልዷ ከነገደ አሴር ሲሆን አባቷ ፋኑኤል ይባላል:: በትውፊት ትምሕርት ሐና የተዳረችው በልጅነቷ [በ፲፪ [12] /፲፭ [15] / ዓመቷ] ነው:: ለ፯ [7] ዓመታት ከልጅነት ባሏ ጋር ኖራ ዕድሜዋ ፲፱ [19] ፳፪ [22] ሲደርስ ሞተባት::
እንደ እሥራኤል ልማድ ሌላ እንድታገባ ብትጠየቅም 'እንቢ' ብላ መበለት ሆነች:: ራሷንም ለእግዚአብሔር አሳልፋ ሰጠች:: በቤተ መቅደስም ለ፹፬ [84] ዓመታት ለፈጣሪዋ ተገዛች:: ፈጽማ ትጸልይና ትጾም ነበርና በእነዚህ ሁሉ ዓመታት ውጪውን አልተመለከተችም::
ለእርሷ ፻፫ [103] ፻፮ [106] ዓመት ሲሆን መድኃኒታችን ተወለደ:: በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ተመልክታም ጌታን ባረከች:: ደስ እያላትም ትንቢትን ተናገረች:: ወደ ቤቷ ገብታም ነፍሷን ሰጠች:: [ሉቃ.፪፥፴፮-፴፰] [2:36-38)
ቸሩ መድኃኒታችን ተርፎ ከሚቀረው ዘመን ዕድሜ ለንስሃ: ዘመን ለፍሥሐ አይንሳን:: ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
[ † የካቲት ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
፪. ቅድስት ሐና ነቢይት [የፋኑኤል ልጅ]
፫. ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
፬. አባ ኤልያስ ገዳማዊ [በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
፪. ኪሩቤል [ አርባዕቱ እንስሳ ]
፫. አባ ብሶይ [ ቢሾይ ]
፬. አቡነ ኪሮስ
፭. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
፮. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት ]
አረጋዊ ስምዖንን ከድካም አልጋ ያነሳ አምላከ ቅዱሳን እኛንም ድካመ ነፍስን ከሚያመጣ የበደል ምኝታ በቸርነቱ ያንሳን::
" እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕጻኑን ጌታ ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው:: እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ :- 'ጌታ ሆይ! አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ:: ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና:: ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን: ለሕዝብሕም ለእስራኤል ክብር ነው:: 'ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር::" [ሉቃ.፪፥፳፯] (2:27)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
[ የካቲት ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
[ † 🕊 በዓለ ስምዖን 🕊 † ]
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ጌታ በተወለደ በ፵ [40] ቀኑ ራሱ የሠራውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል:: እንደ ሥርዓቱም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አገልጋዩዋ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ አቅርበዋል::
ለ፪፻፹፬ [284] ዓመታት የአዳኙን [የመሢሁን] መምጣት ይጠብቅ የነበረው አረጋዊው ስምዖን በዚህች ዕለት ስላየውና ስለታቀፈው ዕለቱ በዓለ ስምዖን ይባላል:: [ሉቃ.፪፥፳፪] (2:22) ከዘጠኙ የጌታ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ከዓለም ፍጥረት በ፭ ሺህ ፪ መቶ [5,200] ዓመታት [ማለትም ከክርስቶስ ልደት ፫፻ [300] ዓመታት በፊት] በጥሊሞስ የሚሉት ንጉሥ በግሪክ ነገሠ::
በጊዜውም በኃይለኝነቱ ሁሉን አስገብሮት ነበርና "ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጬ: እንደ ገል ቀጥቅጬ ገዛሁት:: ምን የቀረኝ ነገር አለ?" ሲል ተናገረ:: ባሮቹም "አንድ ነገር ቀርቶሃል:: በምድረ እሥራኤል ጥበብን የተሞሉ ፵፮ [46] መጻሕፍት አሉ:: እነርሱን አስተርጉም" አሉት::
ያን ጊዜ እሥራኤላውያንን አስገብሯቸው ነበርና ፵፮ [46] ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ፸፪ [72] ምሑራን [ተርጉዋሚዎች] ጋር እንዲያመጡለት አዛዦቹን ላከ:: እነርሱም ፵፮ [46] ቱን መጻሕፍተ ብሉይ ኪዳን ከ፸፪ [72] ምሑራን ጋር አመጡለት::
አይሁድ ክፋተኞች መሆናቸውን ሰምቷልና ፴፮ [36] ድንኩዋን አዘጋጅቶ: ጥንድ ጥንድ ሆነው እንዲሠሩ: ሲተረጉሙ እንዳይመካከሩ ፴፮ [36] ጠባቂዎችን ሾመባቸው:: ይህ ነገር ለጊዜው ከንጉሡ ቢመስልም ጥበቡ ግን ከእግዚአብሔር ነው::
ምንያቱም በጊዜ ሒደት መጻሕፍተ ብሉያት በአደጋ እንደሚጠፉ ያውቃልና ሳይበረዙ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ለእኛ እንዲደርሱ ነው:: ስለዚህም ከክርስቶስ ልደት ፪፻፹፬ [284] ዓመት በፊት ፵፮ [46] ቱም ሁሉም መጻሕፍት [ብሉያት] ከእብራይስጥ ወደ ጽርዕ ልሳን በ፸ [70] ው ሊቃናት አማካኝነት ተተረጐሙ:: [በእርግጥ ከዚያ አስቀድሞ መጻሕፍት [ብሉያት] ወደ ሃገራችን መምጣቸውና ወደ ግዕዝ ልሳን መተርጐማቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው]
ወደ ዋናው ጉዳያችን ስንመለስ ከ፸ [70] ው ሊቃናት መካከል በእድሜው አረጋዊ የሆነ [እንደ ትውፊቱ ከሆነ ፪፻፲፮ [216] ዓመት የሆነው] ስምዖን የሚሉት ምሑረ ኦሪት ነበር:: በፈቃደ እግዚአብሔር ለእርሱ መጽሐፈ ትንቢተ ኢሳይያስ ደርሶት እየተረጐመ ምዕራፍ ፯ [7] ላይ ደረሰ::
ቁጥር ፯ [ 7 ] ላይ ሲደርስ ግን "ናሁ ድንግል ትጸንስ: ወትወልድ ወልደ" የሚል አይቶ "አሁን እንኳን የአሕዛብ ንጉሥ የእሥራኤልስ ቢሆን ድንግል በድንግልና ጸንሳ ትወልዳለች ብለው እንዴት ያምነኛል!" ሲል አሰበ:: "በዚያውስ ላይ ኢሳይያስ በምናሴ የተገደለው ስለዚህ አይደል!" ብሎ ቃሉን ሊለውጠው ወሰነ::
አመሻሽ ላይም 'ድንግል' የሚለውን 'ወለት-ሴት ልጅ' ብሎ ቀየረው:: እርሱ ሲያንቀላፋ ቅዱስ መልአክ ወርዶ 'ድንግል' ብሎ አስተካከለው:: ከእንቅልፉ ሲነቃ ግራ ተጋብቶ እንደ ገና ፍቆ ቀየረው::
አሁንም መልአኩ 'ድንግል' ሲል ቀየረበት:: ፫ [3] ጊዜ እንዲህ ከሆነ በኋላ ግን መልአኩ ተገልጦ ገሰጸው:: በዚያውም ላይ "ይህችን ድንግልና መሲሑን ልጇን ሳታየውና ሳትታቀፈው ሞትን አታይም" ብሎት ተሰወረው:: አረጋዊ ስምዖን ከዚያች ዕለት በኋላ የመድኅን ክርስቶስን መምጣት ሲጠብቅ ለ፪፻፹፬ [284] ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ኖረ:: አካሉም አለቀ::
ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በሆነበት በዚያ ሰሞን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ::
ሕግን የሠራ ጌታ እርሱ 'ፈጻሜ ሕግ' ይባል ዘንድ የርግብ ግልገሎችን [ዋኖሶችን] ይዘው በተወለደ በ ፵ [40] ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት:: በዚህች ቀንም ቅዱስ መልአክ መጥቶ ቅዱስ ስምዖንን ከአልጋው ቀሰቀሰው:: ተስፋ የሚያደርገው አዳኙ [መሲሑ] እንደ መጣም ነገረው::
ይህን ጊዜ አረጋዊው አካሉ ታድሶ እንደ ፪ [30] ዓመት ወጣት እመር ብሎ ከአልጋው ተነሳ:: እንደ በቅሎ እየሠገረም ወደ መቅደስ ወጣ:: በዚያ መሲሑን [ፈጣሪውን] ሲመለከት እንደ እንቦሳ ዘለለ:: ቀረብ ብሎም ሕጻን ጌታን ከድንግል እናቱ እጅ ተቀበለው::
ከደስታው ብዛት የተነሳም "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ: በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ሲል ጸለየ:: ትንቢትንም ተናገረ:: በዚያችው ዕለትም ዐርፎ ተቀበረ::
[ † 🕊 ሐና ነቢይት 🕊 † ]
ዳግመኛ በዚህች ቀን አረጋዊቷን ነቢይት ቅድስት ሐናን እናስባለን:: ይህች ቅድስት ትውልዷ ከነገደ አሴር ሲሆን አባቷ ፋኑኤል ይባላል:: በትውፊት ትምሕርት ሐና የተዳረችው በልጅነቷ [በ፲፪ [12] /፲፭ [15] / ዓመቷ] ነው:: ለ፯ [7] ዓመታት ከልጅነት ባሏ ጋር ኖራ ዕድሜዋ ፲፱ [19] ፳፪ [22] ሲደርስ ሞተባት::
እንደ እሥራኤል ልማድ ሌላ እንድታገባ ብትጠየቅም 'እንቢ' ብላ መበለት ሆነች:: ራሷንም ለእግዚአብሔር አሳልፋ ሰጠች:: በቤተ መቅደስም ለ፹፬ [84] ዓመታት ለፈጣሪዋ ተገዛች:: ፈጽማ ትጸልይና ትጾም ነበርና በእነዚህ ሁሉ ዓመታት ውጪውን አልተመለከተችም::
ለእርሷ ፻፫ [103] ፻፮ [106] ዓመት ሲሆን መድኃኒታችን ተወለደ:: በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ተመልክታም ጌታን ባረከች:: ደስ እያላትም ትንቢትን ተናገረች:: ወደ ቤቷ ገብታም ነፍሷን ሰጠች:: [ሉቃ.፪፥፴፮-፴፰] [2:36-38)
ቸሩ መድኃኒታችን ተርፎ ከሚቀረው ዘመን ዕድሜ ለንስሃ: ዘመን ለፍሥሐ አይንሳን:: ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
[ † የካቲት ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
፪. ቅድስት ሐና ነቢይት [የፋኑኤል ልጅ]
፫. ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
፬. አባ ኤልያስ ገዳማዊ [በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
፪. ኪሩቤል [ አርባዕቱ እንስሳ ]
፫. አባ ብሶይ [ ቢሾይ ]
፬. አቡነ ኪሮስ
፭. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
፮. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት ]
አረጋዊ ስምዖንን ከድካም አልጋ ያነሳ አምላከ ቅዱሳን እኛንም ድካመ ነፍስን ከሚያመጣ የበደል ምኝታ በቸርነቱ ያንሳን::
" እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕጻኑን ጌታ ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው:: እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ :- 'ጌታ ሆይ! አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ:: ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና:: ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን: ለሕዝብሕም ለእስራኤል ክብር ነው:: 'ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር::" [ሉቃ.፪፥፳፯] (2:27)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3👍1
#የኃጢአት ምኞትህን የሚዛን ልክ በልብህ ውስጥ ያመጣጥን ዘንድ ማንኛውንም ዓይነት #መንፈሳዊ ሥራ በመሥራት የክፋታቸውንና የአደጋቸውን መጠን ቀንስ። #የምኞት ኃጢአት እስክታስወግደው ድረስ #መልካም ፈቃድ በልብህ ውስጥ ቀስ በቀስ እንደሚያብብ እርግጠኛ ሁን። #መንፈስ_ቅዱስ በውስጥህ እንደሚሰራ ሲታወቅህ ችላ አትበለው፤ ከእርሱ ጋር ሥራ እንጂ #በምኞትህ ልትቀጥል አትሞክር።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
••• #_ሰናይ__ቀን🙏 ...
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
••• #_ሰናይ__ቀን🙏 ...
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6👍5🙏3🥰1
🕊
[ † እንኳን ለአባታችን ታላቁ ቅዱስ በርሱማ ሶርያዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ † 🕊 ታላቁ አባ በርሱማ 🕊 † ]
† ታላቁ [THE GREAT ይሉታል] አባ በርሱማ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ምንኩስናና ገዳማዊ ሕይወትን ያስፋፋ አባት ነው::
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ምድረ ሶርያን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች የቅድስና ሕይወትን ያስፋፋው ቅዱስ በርሱማ ለቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ከሆኑላት አበው አንዱ ነው:: እርሱ ከተጋድሎው ብዛት ለ54 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ቆይቷል::
በእነዚህ ዘመናትም ግድግዳ ላይ ጠጋ ብሎ ከማረፉ በቀር መቀመጥን እንኩዋ አልመረጠም:: በመዓልትም በሌሊትም በፍቅር አብዝቶ ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ በመጸለዩ የብዙዎቹን ነፍስ ወደ ሕይወት ማርኩዋል::
ገዳማትን ከማስፋፋትና ደቀ መዛሙርትን ከማብዛቱ ባለፈ በስብከተ ወንጌልም የተመሰከረለት አባት ነበር:: በ፬፻፴፩ (431) ፬፻፳፫ (423) ዓ/ም በኤፌሶን በተደረገው የቅዱሳን ጉባኤ ላይ ከተገኙ ሊቃውንትም አንዱ ነው:: በቅድስና ሕይወቱ የተገረመው የቁስጥንጥንያው ንጉሥ [ትንሹ ቴዎዶስዮስ] የንግሥና ቀለበቱን እና ማኅተሙን ሸልሞታል::
ቅዱሱም የዋዛ አልነበረምና በንጉሡ ማኅተም እያተመ "ተፋቀሩ" የሚሉ ብዙ አዋጆችን ወደ መላው ዓለም ልኩዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ፬፻፵፫ (443) ዓ/ም በኬልቄዶን ፮፻፴፮ [636] ሰነፍ ዻዻሳት ጉባኤ አድርገው አባ ዲዮርስቆሮስን እንደ ገደሉት ሲሰማም ወደ ቤተ መንግስት ሒዶ ከሃዲዎቹን [መርቅያንና ሚስቱ ብርክልያን] በአደባባይ ዘልፏቸዋል::
ስለ አዘነባቸውም ተቀስፈዋል:: ታላቁ ቅዱስ አባ በርሱማ ፀሐይን ማቆሙን ጨምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::
† ቸር አምላኩ ከበረከቱ ይክፈለን::
[ † የካቲት ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮዽያዊ] የመነኮሱበት በዓል
፫. ቅዱስ ዻውሎስ ሶርያዊ [ሰማዕት]
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. "318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፪. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፫. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮዽያዊ]
፬. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]
† " ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን ? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" † [ሚክ.፮፥፮] (6:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለአባታችን ታላቁ ቅዱስ በርሱማ ሶርያዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ † 🕊 ታላቁ አባ በርሱማ 🕊 † ]
† ታላቁ [THE GREAT ይሉታል] አባ በርሱማ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ምንኩስናና ገዳማዊ ሕይወትን ያስፋፋ አባት ነው::
በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ምድረ ሶርያን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች የቅድስና ሕይወትን ያስፋፋው ቅዱስ በርሱማ ለቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ከሆኑላት አበው አንዱ ነው:: እርሱ ከተጋድሎው ብዛት ለ54 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ቆይቷል::
በእነዚህ ዘመናትም ግድግዳ ላይ ጠጋ ብሎ ከማረፉ በቀር መቀመጥን እንኩዋ አልመረጠም:: በመዓልትም በሌሊትም በፍቅር አብዝቶ ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ በመጸለዩ የብዙዎቹን ነፍስ ወደ ሕይወት ማርኩዋል::
ገዳማትን ከማስፋፋትና ደቀ መዛሙርትን ከማብዛቱ ባለፈ በስብከተ ወንጌልም የተመሰከረለት አባት ነበር:: በ፬፻፴፩ (431) ፬፻፳፫ (423) ዓ/ም በኤፌሶን በተደረገው የቅዱሳን ጉባኤ ላይ ከተገኙ ሊቃውንትም አንዱ ነው:: በቅድስና ሕይወቱ የተገረመው የቁስጥንጥንያው ንጉሥ [ትንሹ ቴዎዶስዮስ] የንግሥና ቀለበቱን እና ማኅተሙን ሸልሞታል::
ቅዱሱም የዋዛ አልነበረምና በንጉሡ ማኅተም እያተመ "ተፋቀሩ" የሚሉ ብዙ አዋጆችን ወደ መላው ዓለም ልኩዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ፬፻፵፫ (443) ዓ/ም በኬልቄዶን ፮፻፴፮ [636] ሰነፍ ዻዻሳት ጉባኤ አድርገው አባ ዲዮርስቆሮስን እንደ ገደሉት ሲሰማም ወደ ቤተ መንግስት ሒዶ ከሃዲዎቹን [መርቅያንና ሚስቱ ብርክልያን] በአደባባይ ዘልፏቸዋል::
ስለ አዘነባቸውም ተቀስፈዋል:: ታላቁ ቅዱስ አባ በርሱማ ፀሐይን ማቆሙን ጨምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::
† ቸር አምላኩ ከበረከቱ ይክፈለን::
[ † የካቲት ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮዽያዊ] የመነኮሱበት በዓል
፫. ቅዱስ ዻውሎስ ሶርያዊ [ሰማዕት]
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. "318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፪. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፫. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮዽያዊ]
፬. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]
† " ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን ? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" † [ሚክ.፮፥፮] (6:6)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍2
#ቤተክርስቲያንን__አይችሏት ??
#ከቤተ_ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች። #ቤተ_ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም። ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? #አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው?
#የተማሩና_ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። #ሊነቅሏት ግን አልቻሉም። ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። #ቤተ_ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። #ቤተ_ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። #እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፣ እንግዲህ ማን #ሊነቀንቃት ይችላል? "
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#መልካም_ዕለተ_ሰንበት🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ከቤተ_ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች። #ቤተ_ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም። ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? #አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው?
#የተማሩና_ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። #ሊነቅሏት ግን አልቻሉም። ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። #ቤተ_ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። #ቤተ_ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። #እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፣ እንግዲህ ማን #ሊነቀንቃት ይችላል? "
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#መልካም_ዕለተ_ሰንበት🙏
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤16🙏3👍1
🕊
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። ✞✞✞
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ: ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕትና አባ ኤስድሮስ ገዳማዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ያእቆብ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ [ የእልፍዮስ ልጅ ] ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት አንዱ [ ማቴ.፲፥፩ ] ብዙ አሕጉር አስተምሮ በዚህ ቀን በሰማዕትነት ወደ ፈጣሪው ሔዷል::
ቅዱስ ዮስጦስ በ፫ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ምድራዊ የንግሥና ዙፋንን ንቆ በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ከሚስቱ ቅድስት ታውክልያና ከአንድ ልጁ ቅዱስ አቦሊ ጋር ሰማያዊ ክብርን ተቀዳጅቷል::
አባ ኤስድሮስ ግብፃዊ ሲሆኑ ሹመትን ጠልተው ፈርማ በሚባል ገዳም ለ፷ [ 60 ] ዓመታት በበርሃ ውስጥ ከ፲፰ ሺህ [ 18,000 ] በላይ ድርሳናትን ፅፈዋል:: ይሕም በዓለም ታሪክ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚው ያደርጋቸዋል:: ከድርሳናቱ መካከል ፪ ሺህ [ 2,000 ] ያህሉ ዛሬም ድረስ በግብፅ በርሃ ውስጥ ይገኛሉ::
ከስንክሳር
🕊 † አባ ፌሎ † 🕊
በዚች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማእትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሰዋ ለፀሀይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉስ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ስቃይን አሰቃይቶ እራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግስተ ሰማያት የሰማእትነትን አክሊል ተቀበለ ።
በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር።
🕊 † አባ ኤስድሮስ † 🕊
በዚችም እለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድርስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለፀጉች ናቸው።
ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸውከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩት።
ግልፅ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሄድና አለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሁትና የሚተጋ ሆነ።
በሀገሮችም ያለ ሰዎች ሰለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾመት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ ። በሌሊትም ወጥቶ ሽሽ ወደ ፈረማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኮሰ።
ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በወስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሳፃትንም ደረሰ ከዕርሳቸውም ስለ ነገስታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መፃህፍቶችን ብሉያትና ሀዲሳትን ተረጉመ።
የመፅሀፍታቹም ቁጥራቸው አስራ ስምንት ሺህ ነው። እነዚህም ድርሳናት ተግሳፃት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው። ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያስፈልቃቸው ሆኗልና።
ይህንንም በጎ ስራውን ሲፈፅሙ መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሄርንም አግልግሎ በሰላም አረፈ።
[ † የካቲት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ወልደ እልፍዮስ ]
፪. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት
፫. አባ ኤስድሮስ ጻድቅ [ ዘሃገረ ፈርማ ]
፬. አባ ፌሎ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ስምዖን
፮. ቅዱስ ኒቆላዎስ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕፀ-መስቀል
፪. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፬. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
" . . . ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ በእናንተ ላይ ከሚሆነው: ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ይናፍቁዋቹሀል:: ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን::" [፪ኛ ቆሮ.፱፥፲፬ ]
" ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ: ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ:: " [ኤፌ.፭፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። ✞✞✞
[ † እንኩዋን ለቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ: ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕትና አባ ኤስድሮስ ገዳማዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ያእቆብ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ [ የእልፍዮስ ልጅ ] ከ፲፪ [12]ቱ ሐዋርያት አንዱ [ ማቴ.፲፥፩ ] ብዙ አሕጉር አስተምሮ በዚህ ቀን በሰማዕትነት ወደ ፈጣሪው ሔዷል::
ቅዱስ ዮስጦስ በ፫ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ምድራዊ የንግሥና ዙፋንን ንቆ በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ከሚስቱ ቅድስት ታውክልያና ከአንድ ልጁ ቅዱስ አቦሊ ጋር ሰማያዊ ክብርን ተቀዳጅቷል::
አባ ኤስድሮስ ግብፃዊ ሲሆኑ ሹመትን ጠልተው ፈርማ በሚባል ገዳም ለ፷ [ 60 ] ዓመታት በበርሃ ውስጥ ከ፲፰ ሺህ [ 18,000 ] በላይ ድርሳናትን ፅፈዋል:: ይሕም በዓለም ታሪክ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚው ያደርጋቸዋል:: ከድርሳናቱ መካከል ፪ ሺህ [ 2,000 ] ያህሉ ዛሬም ድረስ በግብፅ በርሃ ውስጥ ይገኛሉ::
ከስንክሳር
🕊 † አባ ፌሎ † 🕊
በዚች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማእትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሰዋ ለፀሀይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉስ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ስቃይን አሰቃይቶ እራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግስተ ሰማያት የሰማእትነትን አክሊል ተቀበለ ።
በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር።
🕊 † አባ ኤስድሮስ † 🕊
በዚችም እለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድርስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለፀጉች ናቸው።
ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸውከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩት።
ግልፅ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሄድና አለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሁትና የሚተጋ ሆነ።
በሀገሮችም ያለ ሰዎች ሰለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾመት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ ። በሌሊትም ወጥቶ ሽሽ ወደ ፈረማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኮሰ።
ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በወስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሳፃትንም ደረሰ ከዕርሳቸውም ስለ ነገስታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መፃህፍቶችን ብሉያትና ሀዲሳትን ተረጉመ።
የመፅሀፍታቹም ቁጥራቸው አስራ ስምንት ሺህ ነው። እነዚህም ድርሳናት ተግሳፃት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው። ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያስፈልቃቸው ሆኗልና።
ይህንንም በጎ ስራውን ሲፈፅሙ መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሄርንም አግልግሎ በሰላም አረፈ።
[ † የካቲት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ወልደ እልፍዮስ ]
፪. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት
፫. አባ ኤስድሮስ ጻድቅ [ ዘሃገረ ፈርማ ]
፬. አባ ፌሎ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ስምዖን
፮. ቅዱስ ኒቆላዎስ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕፀ-መስቀል
፪. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፬. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
" . . . ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ በእናንተ ላይ ከሚሆነው: ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ይናፍቁዋቹሀል:: ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን::" [፪ኛ ቆሮ.፱፥፲፬ ]
" ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ: ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ:: " [ኤፌ.፭፥፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ከቡር አሜን †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3👍2
አምላኬ፥ በቀን ወደ አንተ እጣራለሁ፥ አልመለስህልኝም፤ በሌሊትም እንኳ ዕረፍት የለኝም።
፤ በእስራኤል የተመሰገንህ አንተ ግን በቅድስና ትኖራለህ።
፤ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ፥ ተማመኑ አንተም አዳንሃቸው።
፤ ወደ አንተ ጮኹ አመለጡም፥ አንተንም ተማመኑ አላፈሩም።
፤ እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ።
፤ የሚያዩኝ ሁሉ ይላግጡብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ።
፤ በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው።
፤ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ።
፤ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ።
፤ ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።
መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 22ቁ 2-11
#መልካም_ቀን🙏
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
፤ በእስራኤል የተመሰገንህ አንተ ግን በቅድስና ትኖራለህ።
፤ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ፥ ተማመኑ አንተም አዳንሃቸው።
፤ ወደ አንተ ጮኹ አመለጡም፥ አንተንም ተማመኑ አላፈሩም።
፤ እኔ ግን ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ።
፤ የሚያዩኝ ሁሉ ይላግጡብኛል፤ ራሳቸውን እየነቀነቁ በከንፈሮቻቸው እንዲህ ይላሉ።
፤ በእግዚአብሔር ተማመነ፥ እርሱንም ያድነው፤ ቢወድደውስ ያድነው።
፤ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ።
፤ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ።
፤ ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።
መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 22ቁ 2-11
#መልካም_ቀን🙏
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤10👍2🙏2