ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው ፤ በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን ፤ ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥
፤ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።
ወ.ሮ ሰዎች ምዕ. 8፣36_39
#_ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
፤ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።
ወ.ሮ ሰዎች ምዕ. 8፣36_39
#_ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6😢4🙏3👍1
🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትንሣኤውንም እናምናለን ! ]
🕊 💖 🕊
❝ እኛ ግን የዳንበትን አዳኛችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለውን ሕማሙን በፈቃዱ ስለእኛ በሥጋ ያደረገውን ሞቱን እናስተምራለን ፤ ትንሣኤውንም እናምናለን ወደ ሰማይ ማረጉንም እናስተምራለን ፤ በሙታን በሕያዋን ይፈርድ ዘንድ የሚመጣበትን ዳግመኛ ምጽአቱን ፤ እርሱ የሚያወርሳት ለዘለዓለም የማታልፍ መንግሥተ ሰማያት እንዳለች እናምናለን። [ ማቴ.፲፥፳፰-፮ ። ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ]
በኦሪት የተጻፈውን ቃል ምክንያት አድርገው ለእግዚአብሔር ቀድሞ ሥጋ እንደ ነበረው የሚናገሩ ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን በእኛ አምሳል እንፍጠር አለ በእኛ አምሳል ያለውም ስለሰው ሥጋ ነው የሚሉ አሉ። [ዘፍ.፩፥፳፮ ]
ነገር ግን እንዲህ አይደለም እርሱ ስለ ውሳጣዊ ሰውነታችን [ ነፍስ ] ተናገረ እንጂ እርሱ ሁልጊዜ በመታደስ ጸንቶ ይኖራልና። አፍአዊ ሰውነታችን [ ሥጋ ] ይሞት ዘንድ እስኪነሣ ድረስም ይፈርስ ይበሰብስ ዘንድ እንዳለው ነገሩ የታወቀ ነው ፤ ውሳጣዊው ግን አይሞትም አይፈርስም አይበሰብስም። [ ፪ቆሮ.፬፥፲፮ ]
የበቃ ቢሆን ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስዱታል ፤ መውጣት ሳይኖር ሁል ጊዜ በዚያ ይኖራል።የበቃ ባይሆን ግን ወደገሀነም ይወስዱታል ፤ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለም በዚያ ይኖራል። [ ማቴ.፳፭፥፵፮ ]
ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ በጎ ሥራን ቢሠራ እግዚአብሔርን እንደሚመስል እግዚአብሔር ገልጦልን ይኸን ቃል እንተረጕማለን ፤ ምድራዊ አዳምን መምሰል ገንዘብ እንደ አደረግን ሰማያዊ ክርስቶስን መምሰልን ገንዘብ እናደርጋለን ተብሎ እንደ ተጻፈ። [ ፩ቆሮ.፲፭፥፮-፵፱ ]
ውሳጣዊ ሰውነት ግን የማይለወጥ ዕውቀት ያለው ነፍስ ነው ፤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በሥጋ ተሰውሮ ያለ ነፍስን በቸርነቱ እግዚአብሔርን የሚመስል አድርጎ ፈጠረው ፤ እግዚአብሔር ጥንቱን ሥጋ አይደለምና አይወሰንምና ጌታ እሳት ነው ፤ ብርሃንም ነው ፤ ማንም ማን አይቀርበውም ፤ ሕሊናም መርምሮ አያገኘውም አይመረመርም ከላይ ሆኖ ሰማይን ፡ ይሸፍናል ፤ ከታች ሆኖ ምድርን ይሸፍናል።
ፍጥረት ሁሉ ፤ ሰማያት በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ፤ ምድርም ፤ በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ከብቱም አውሬውም ሁሉ የሚንቀሳቀሱትም ወፎችም ፤ የምድረ በዳ ዛፎችም ሁሉ ባሕርም ፤ ፈሳሾችም በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ በእርሱ ጸንተው ይኖራሉ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሮአልና። [ መዝ.፻፵፰፥፩—፲፬ ። ዮሐ.፩፥፫ ቆላ.፩፥፲፭-፲፰ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትንሣኤውንም እናምናለን ! ]
🕊 💖 🕊
❝ እኛ ግን የዳንበትን አዳኛችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለውን ሕማሙን በፈቃዱ ስለእኛ በሥጋ ያደረገውን ሞቱን እናስተምራለን ፤ ትንሣኤውንም እናምናለን ወደ ሰማይ ማረጉንም እናስተምራለን ፤ በሙታን በሕያዋን ይፈርድ ዘንድ የሚመጣበትን ዳግመኛ ምጽአቱን ፤ እርሱ የሚያወርሳት ለዘለዓለም የማታልፍ መንግሥተ ሰማያት እንዳለች እናምናለን። [ ማቴ.፲፥፳፰-፮ ። ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ]
በኦሪት የተጻፈውን ቃል ምክንያት አድርገው ለእግዚአብሔር ቀድሞ ሥጋ እንደ ነበረው የሚናገሩ ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን በእኛ አምሳል እንፍጠር አለ በእኛ አምሳል ያለውም ስለሰው ሥጋ ነው የሚሉ አሉ። [ዘፍ.፩፥፳፮ ]
ነገር ግን እንዲህ አይደለም እርሱ ስለ ውሳጣዊ ሰውነታችን [ ነፍስ ] ተናገረ እንጂ እርሱ ሁልጊዜ በመታደስ ጸንቶ ይኖራልና። አፍአዊ ሰውነታችን [ ሥጋ ] ይሞት ዘንድ እስኪነሣ ድረስም ይፈርስ ይበሰብስ ዘንድ እንዳለው ነገሩ የታወቀ ነው ፤ ውሳጣዊው ግን አይሞትም አይፈርስም አይበሰብስም። [ ፪ቆሮ.፬፥፲፮ ]
የበቃ ቢሆን ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስዱታል ፤ መውጣት ሳይኖር ሁል ጊዜ በዚያ ይኖራል።የበቃ ባይሆን ግን ወደገሀነም ይወስዱታል ፤ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለም በዚያ ይኖራል። [ ማቴ.፳፭፥፵፮ ]
ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ በጎ ሥራን ቢሠራ እግዚአብሔርን እንደሚመስል እግዚአብሔር ገልጦልን ይኸን ቃል እንተረጕማለን ፤ ምድራዊ አዳምን መምሰል ገንዘብ እንደ አደረግን ሰማያዊ ክርስቶስን መምሰልን ገንዘብ እናደርጋለን ተብሎ እንደ ተጻፈ። [ ፩ቆሮ.፲፭፥፮-፵፱ ]
ውሳጣዊ ሰውነት ግን የማይለወጥ ዕውቀት ያለው ነፍስ ነው ፤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በሥጋ ተሰውሮ ያለ ነፍስን በቸርነቱ እግዚአብሔርን የሚመስል አድርጎ ፈጠረው ፤ እግዚአብሔር ጥንቱን ሥጋ አይደለምና አይወሰንምና ጌታ እሳት ነው ፤ ብርሃንም ነው ፤ ማንም ማን አይቀርበውም ፤ ሕሊናም መርምሮ አያገኘውም አይመረመርም ከላይ ሆኖ ሰማይን ፡ ይሸፍናል ፤ ከታች ሆኖ ምድርን ይሸፍናል።
ፍጥረት ሁሉ ፤ ሰማያት በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ፤ ምድርም ፤ በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ከብቱም አውሬውም ሁሉ የሚንቀሳቀሱትም ወፎችም ፤ የምድረ በዳ ዛፎችም ሁሉ ባሕርም ፤ ፈሳሾችም በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ በእርሱ ጸንተው ይኖራሉ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሮአልና። [ መዝ.፻፵፰፥፩—፲፬ ። ዮሐ.፩፥፫ ቆላ.፩፥፲፭-፲፰ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
🕊 💖 🕊
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ ! ]
❝ ሰላም ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ማኅደረ ስብሐት ምዕዋደ መላእክት እም ኩሉ ሕዝብ ❞
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] የምስጋና ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላምታ ይገባል። ] [አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]
" በመላእክት ፊት እዘምርልኻለሁ ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ። " [መዝ.፻፴፯፥፪ ]
🕊 💖 🕊
ቤተ ክርስቲያንን “ ቅድስት ” አላት ስለምን ቢሉ ?
የቅድስት ሥላሴ አንድነት ሦስትነት ይነገርባታልና ፤ አንድም ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ አክብሯታልና። አንድም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ለምእመናን ይሰጥባታልና፡፡ አንድም በኀጢአት የረከሰ ሰው በንስሓ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆባት ይቀደስባታልና።
“ ማኅደረ ስብሐት ” [ የምስጋና ማደሪያ ] አላት ፦
የልዑል እግዚአብሔር ምስጋና በጸሎተ ኪዳን ፣ በስብሐተ ነግህ ፣ በጸሎተ ቅዳሴ ፣ በማሕሌት ፣ በሰዓታት ፣ በሰባቱ ጊዜያት ኹሉ ይነገርባታልና።
“ የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] ” አላት ፦
የመንግሥቱ ወንጌል በሚነገርበት ፣ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ በሚፈተትበት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የጸለዩትን ጸሎት ለማሳረግ በቀን ስድስት መቶ በሌሊት ስድስት መቶ መላእክት ይጠብቋታልና።
“ እመ ኵሉ ሕዝብ ” የሕዝብ ኹሉ እናት ይላታል ፦
እናት ልጆቿን እንድታሳድግ ፣ እንድትጠብቅ ፣ ወደ ቀና ጐዳና መርታ እንድታደርስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ይልቁኑ በሥጋውና በደሙ እናድግባታለን ፤ በርቱዕ ትምህርቷ ከክሕደት እንጠበቅባታለን ፤ በመጨረሻም ወደ አምሳያዋ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት መርታ ታደርስናለችና። [ ገላ.፬፥፳፮-፳፯ ] ❞
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
💖 🕊 💖
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ ! ]
❝ ሰላም ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ማኅደረ ስብሐት ምዕዋደ መላእክት እም ኩሉ ሕዝብ ❞
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] የምስጋና ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላምታ ይገባል። ] [አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]
" በመላእክት ፊት እዘምርልኻለሁ ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ። " [መዝ.፻፴፯፥፪ ]
🕊 💖 🕊
ቤተ ክርስቲያንን “ ቅድስት ” አላት ስለምን ቢሉ ?
የቅድስት ሥላሴ አንድነት ሦስትነት ይነገርባታልና ፤ አንድም ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ አክብሯታልና። አንድም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ለምእመናን ይሰጥባታልና፡፡ አንድም በኀጢአት የረከሰ ሰው በንስሓ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆባት ይቀደስባታልና።
“ ማኅደረ ስብሐት ” [ የምስጋና ማደሪያ ] አላት ፦
የልዑል እግዚአብሔር ምስጋና በጸሎተ ኪዳን ፣ በስብሐተ ነግህ ፣ በጸሎተ ቅዳሴ ፣ በማሕሌት ፣ በሰዓታት ፣ በሰባቱ ጊዜያት ኹሉ ይነገርባታልና።
“ የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] ” አላት ፦
የመንግሥቱ ወንጌል በሚነገርበት ፣ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ በሚፈተትበት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የጸለዩትን ጸሎት ለማሳረግ በቀን ስድስት መቶ በሌሊት ስድስት መቶ መላእክት ይጠብቋታልና።
“ እመ ኵሉ ሕዝብ ” የሕዝብ ኹሉ እናት ይላታል ፦
እናት ልጆቿን እንድታሳድግ ፣ እንድትጠብቅ ፣ ወደ ቀና ጐዳና መርታ እንድታደርስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ይልቁኑ በሥጋውና በደሙ እናድግባታለን ፤ በርቱዕ ትምህርቷ ከክሕደት እንጠበቅባታለን ፤ በመጨረሻም ወደ አምሳያዋ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት መርታ ታደርስናለችና። [ ገላ.፬፥፳፮-፳፯ ] ❞
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
💖 🕊 💖
❤2
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🕊
▷ " ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ! "
[ 💖 አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ]
[ 🕊 ]
-------------------------------------------------
❝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ፥ አቤቱ ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች ፤ መቼ እደርሳለሁ ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ ?
ዘወትር። አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ❞
[ መዝ . ፵፪ ፥ ፩ - ፫ ]
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🕊
▷ " ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ! "
[ 💖 አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ]
[ 🕊 ]
-------------------------------------------------
❝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ፥ አቤቱ ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች ፤ መቼ እደርሳለሁ ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ ?
ዘወትር። አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ❞
[ መዝ . ፵፪ ፥ ፩ - ፫ ]
🕊 💖 🕊
❤4
ሰኔ____21
እንኳን #ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ ሰኔ ጐልጐታና ሕንጸተ ቤተ ቤተክርስቲያን (ሕንጸታ) በሰላም አደረሳችኹ
#ድንግል_ሆይ_ዝም_አትበይ🙏😢😢
ጨለማችን ጨልሟል ውስጣችን ቃል በሌለው #ኃዘን ውስጥ ወድቋል ። አሰገራሚው መድኃኒት በውስጥሸ የተገኘ ፡ ምድርን የሸፈነ ፀሐይ የተገለጠብሽ #የዳዊት ልጅ እናታችን ማርያም ሆይ ዝም አትበይ በእውነት ዝም አትበይ ። ትላንት ልመናሽ እንደጋረደን ዛሬም #ቃል_ኪዳንሽ ጥላ ይሁነን ።
#ድንግል_ሆይ....የመጣብንን እሳት ፡ከፊታችን
የቆመውን ደንቃራ በቃህ እንዲለው #በልጅሽ ፈት ቁሚልን ።
#እናታችን__ሆይ ...አለማችን የዶኪማስን ቤት ሆኗል ፡ ሠርጉ ወደ ሙሾ ጠጁም ወደ መርዝነት ተቀይሯልና ....እንደ ልማድሽ ልጄ ሆይ በይልን ።
ከቀኝ ከግራ የሌለው የቃል ኪዳን ሕዝብሽን ሞት እንዳይበላው መድኃኒት ተብሎ ከተጠራው ልጅሽ ለምኚልን ። አንቺ #በሥላሴ ፊት ሞገስ ያለሽ ሙሽራ ማርያም ሆይ ሠዓሊ ለነ እያልን በፊትሽ የመረረ #እንባችንን እናፈሳላን ። ሚረዳን የልጅሽ እጅ ሚፈውሰንም እርሱ ብቻ ነውና ዝም አትበይ ።
ኢየሩሳሌምን ስለ ዳዊት የጋረድካት ጌታ ሆይ ስለ እናትህ ብለህ የሚሮጠውን መልአከ ሞት ያዘው። ደምህ ይጋርደን #ሐጢአታችንን_አታስብብን
የእናታችን እረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን 🙏🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
እንኳን #ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ ሰኔ ጐልጐታና ሕንጸተ ቤተ ቤተክርስቲያን (ሕንጸታ) በሰላም አደረሳችኹ
#ድንግል_ሆይ_ዝም_አትበይ🙏😢😢
ጨለማችን ጨልሟል ውስጣችን ቃል በሌለው #ኃዘን ውስጥ ወድቋል ። አሰገራሚው መድኃኒት በውስጥሸ የተገኘ ፡ ምድርን የሸፈነ ፀሐይ የተገለጠብሽ #የዳዊት ልጅ እናታችን ማርያም ሆይ ዝም አትበይ በእውነት ዝም አትበይ ። ትላንት ልመናሽ እንደጋረደን ዛሬም #ቃል_ኪዳንሽ ጥላ ይሁነን ።
#ድንግል_ሆይ....የመጣብንን እሳት ፡ከፊታችን
የቆመውን ደንቃራ በቃህ እንዲለው #በልጅሽ ፈት ቁሚልን ።
#እናታችን__ሆይ ...አለማችን የዶኪማስን ቤት ሆኗል ፡ ሠርጉ ወደ ሙሾ ጠጁም ወደ መርዝነት ተቀይሯልና ....እንደ ልማድሽ ልጄ ሆይ በይልን ።
ከቀኝ ከግራ የሌለው የቃል ኪዳን ሕዝብሽን ሞት እንዳይበላው መድኃኒት ተብሎ ከተጠራው ልጅሽ ለምኚልን ። አንቺ #በሥላሴ ፊት ሞገስ ያለሽ ሙሽራ ማርያም ሆይ ሠዓሊ ለነ እያልን በፊትሽ የመረረ #እንባችንን እናፈሳላን ። ሚረዳን የልጅሽ እጅ ሚፈውሰንም እርሱ ብቻ ነውና ዝም አትበይ ።
ኢየሩሳሌምን ስለ ዳዊት የጋረድካት ጌታ ሆይ ስለ እናትህ ብለህ የሚሮጠውን መልአከ ሞት ያዘው። ደምህ ይጋርደን #ሐጢአታችንን_አታስብብን
የእናታችን እረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን 🙏🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤18
† † †
[ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን ፥ አደረሳችሁ ! ]
🕊 ሰኔ ጎለጎታ 🕊
💖
" ምሕረትን የምትለምኚ ድንግል እናቱ ፤
አንድያው ልጅሽ አያጥፋን በከንቱ ! "
"በእንቲአነ በሊዮ ሰአሊተ ምሕረት እሙ ፤
ኢታማስን ግብረ እዴከ እንተ ለሐኮ ቀዲሙ ! " [ አርኬ ]
[ ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
† † †
💖 🕊 💖
[ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን ፥ አደረሳችሁ ! ]
🕊 ሰኔ ጎለጎታ 🕊
💖
" ምሕረትን የምትለምኚ ድንግል እናቱ ፤
አንድያው ልጅሽ አያጥፋን በከንቱ ! "
"በእንቲአነ በሊዮ ሰአሊተ ምሕረት እሙ ፤
ኢታማስን ግብረ እዴከ እንተ ለሐኮ ቀዲሙ ! " [ አርኬ ]
[ ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
† † †
💖 🕊 💖
❤4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
†
[ ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ ]
" አባቱን የሚረግም ፥ እናቱንም የማይባርክ ትውልድ አለ። ለራሱ ንጹሕ የሆነ የሚመስለው ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ። ከፍ ከፍ ያሉ ዓይኖች ያሉት ፥ ሽፋሽፍቶቹም ወደ ላይ የሚያዩ ትውልድ አለ።" [ ምሳ.፴፥፲፩]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
[ ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ ]
" አባቱን የሚረግም ፥ እናቱንም የማይባርክ ትውልድ አለ። ለራሱ ንጹሕ የሆነ የሚመስለው ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ። ከፍ ከፍ ያሉ ዓይኖች ያሉት ፥ ሽፋሽፍቶቹም ወደ ላይ የሚያዩ ትውልድ አለ።" [ ምሳ.፴፥፲፩]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
❤4
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
🕊 እንኳን አደረሳችሁ 🕊
† ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †
ትናንት ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሐዋርያት ወረደ:: ፊልዽስዩስ በምትባል ሃገር በዼጥሮስ እጅ የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን አነጸ ብለን ነበር:: በዚህች ዕለት ደግሞ አእላፍ መላዕክትን: ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዟት ወረደ::
ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት ፪ [2] ነገሮችን አሳየ :-
፩. አስቀድሞ ቤተ ክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዓተ ቤተ ክርረስቲያንን አሳየ::
፪. ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስን ከመካከል አቁሞ "አርሳይሮስ" ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት [ፓትርያርክ] ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት "አክዮስ" እያሉ ፫ [3] ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ
"ይደልዎ": በዐማርኛው ደግሞ "ይገባዋል: ያሥምርለት"እንደ ማለት ነው::
ጌታችን ይሕን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ::
¤ አማናዊት ማሕደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ:
¤ ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ:
¤ ቅዱስ_እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ሆኖ:
¤ ሐዋርያት ድንግልን ከበው:
¤ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቁመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ::
በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው::
"ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን እነጹ:: ይህችን ዕለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::" ብሏቸው ከድንግል እናቱ ከመላዕክቱ ጋር
ዐረገ::
🕊 † ሰኔ ጐልጐታ † 🕊
ዳግመኛ በዚህ ቀን ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ይታሰባል:: ይኸውም ከሕንድ አውራጃዎች በአንዱ ወንጌልን ሰብኮ እኩሎቹ ሲያምኑ እኩሎቹ እንቢ አሉ:: ቅዱስ ቶማስም ያመኑትን
"ከጣዖት አምልኮና ከዝሙት ሸሹ" ብሎ መከራቸው:: ምክሩን ከሰሙት አንዱ በዚያው ምሽት ሊጠጣ ወደ መሸታ ቤት ይገባል:: ሰው ሁሉ ከወጣ በኋላ ባለ መሸተኛዋ ሴት እንደለመደችው አብረው እንዲተኙ ስትጠይቀው "እንዴት ሐዋርያው ከዝሙት ሽሹ እያለ እንዲህ ትይኛለሽ?" በሚል ሰይፍ አውጥቶ አንገቷን ቆረጣት::
እርሱ መልካም ያደረገ መስሎታል:: የሠራው ሥራ [መግደሉ] ግን አሕዛባዊ ግብር ነው:: በማግስቱ ቅዱስ ቶማስ ነገሩን ሰምቶ ሰዎችን ሰበሰበና "ይህንን የአውሬ ድርጊት የፈጸመ ማነው?" ሲል ጠየቀ:: ፈጻሚው ግን አልታወቅም በሚል ዝም አለ:: ወዲያው ቅዱሱ ሐዋርያ ዳቦ አንስቶ ቆረሰና "ለበረከት እያነሳችሁ ውሰዱ" አለ:: ሰውየው ተራውን ጠብቆ ሊያነሳ ሲል እጁ ሰለለች::
ሐዋርያው "ምነው ልጄ! ምን ሆንክ?" አለው:: እሱም እንዳላመለጠ ሲያውቅ እውነቱን ተናዘዘ:: ቅዱስ ቶማስ ግን ሕዝቡ ሁሉ እንደተሰበሰበ ያን ወጣት ገስጾ "አስከሬኑን አምጡልኝ" አለ:: የወጣቱን እጅ ፈውሶ "በል . . . የገደልኩሽ እኔ: የሚያስነሳሽ ግን ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው . . . ብለህ አንገቷን ቀጥለው" አለው::
እንዳለው ቢያደርግ የሞተችው አፈፍ ብላ ተነሳች:: ይህንን ተአምር ያዩ አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል::
ከሐዋርያው በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ አበው ጎርጎርዮሳት
፪፡ አባ ምዕመነ ድንግል
፫፡ አባ ዓምደ ሥላሴ
፬፡ አባ አሮን ሶርያዊ
፭፡ አባ መርትያኖስ
፮፡ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል
" ስለ ጽዮን ዝም አልልም . . . አሕዛብም ጽድቅሽን: ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ:: የእግዚአብሔርም አፍ በሚጠራበት በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ:: በእግዚአብሔር እጅ የክብር አክሊል በአምላክሽም እጅ የመንግሥት ዘውድ ትሆኛለሽ:: " [ኢሳ.፷፪፥፩-፫] (62:1-3)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
🕊 እንኳን አደረሳችሁ 🕊
† ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †
ትናንት ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሐዋርያት ወረደ:: ፊልዽስዩስ በምትባል ሃገር በዼጥሮስ እጅ የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን አነጸ ብለን ነበር:: በዚህች ዕለት ደግሞ አእላፍ መላዕክትን: ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዟት ወረደ::
ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት ፪ [2] ነገሮችን አሳየ :-
፩. አስቀድሞ ቤተ ክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዓተ ቤተ ክርረስቲያንን አሳየ::
፪. ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስን ከመካከል አቁሞ "አርሳይሮስ" ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት [ፓትርያርክ] ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት "አክዮስ" እያሉ ፫ [3] ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ
"ይደልዎ": በዐማርኛው ደግሞ "ይገባዋል: ያሥምርለት"እንደ ማለት ነው::
ጌታችን ይሕን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ::
¤ አማናዊት ማሕደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ:
¤ ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ:
¤ ቅዱስ_እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ሆኖ:
¤ ሐዋርያት ድንግልን ከበው:
¤ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቁመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ::
በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው::
"ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን እነጹ:: ይህችን ዕለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::" ብሏቸው ከድንግል እናቱ ከመላዕክቱ ጋር
ዐረገ::
🕊 † ሰኔ ጐልጐታ † 🕊
ዳግመኛ በዚህ ቀን ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ይታሰባል:: ይኸውም ከሕንድ አውራጃዎች በአንዱ ወንጌልን ሰብኮ እኩሎቹ ሲያምኑ እኩሎቹ እንቢ አሉ:: ቅዱስ ቶማስም ያመኑትን
"ከጣዖት አምልኮና ከዝሙት ሸሹ" ብሎ መከራቸው:: ምክሩን ከሰሙት አንዱ በዚያው ምሽት ሊጠጣ ወደ መሸታ ቤት ይገባል:: ሰው ሁሉ ከወጣ በኋላ ባለ መሸተኛዋ ሴት እንደለመደችው አብረው እንዲተኙ ስትጠይቀው "እንዴት ሐዋርያው ከዝሙት ሽሹ እያለ እንዲህ ትይኛለሽ?" በሚል ሰይፍ አውጥቶ አንገቷን ቆረጣት::
እርሱ መልካም ያደረገ መስሎታል:: የሠራው ሥራ [መግደሉ] ግን አሕዛባዊ ግብር ነው:: በማግስቱ ቅዱስ ቶማስ ነገሩን ሰምቶ ሰዎችን ሰበሰበና "ይህንን የአውሬ ድርጊት የፈጸመ ማነው?" ሲል ጠየቀ:: ፈጻሚው ግን አልታወቅም በሚል ዝም አለ:: ወዲያው ቅዱሱ ሐዋርያ ዳቦ አንስቶ ቆረሰና "ለበረከት እያነሳችሁ ውሰዱ" አለ:: ሰውየው ተራውን ጠብቆ ሊያነሳ ሲል እጁ ሰለለች::
ሐዋርያው "ምነው ልጄ! ምን ሆንክ?" አለው:: እሱም እንዳላመለጠ ሲያውቅ እውነቱን ተናዘዘ:: ቅዱስ ቶማስ ግን ሕዝቡ ሁሉ እንደተሰበሰበ ያን ወጣት ገስጾ "አስከሬኑን አምጡልኝ" አለ:: የወጣቱን እጅ ፈውሶ "በል . . . የገደልኩሽ እኔ: የሚያስነሳሽ ግን ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው . . . ብለህ አንገቷን ቀጥለው" አለው::
እንዳለው ቢያደርግ የሞተችው አፈፍ ብላ ተነሳች:: ይህንን ተአምር ያዩ አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል::
ከሐዋርያው በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ አበው ጎርጎርዮሳት
፪፡ አባ ምዕመነ ድንግል
፫፡ አባ ዓምደ ሥላሴ
፬፡ አባ አሮን ሶርያዊ
፭፡ አባ መርትያኖስ
፮፡ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል
" ስለ ጽዮን ዝም አልልም . . . አሕዛብም ጽድቅሽን: ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ:: የእግዚአብሔርም አፍ በሚጠራበት በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ:: በእግዚአብሔር እጅ የክብር አክሊል በአምላክሽም እጅ የመንግሥት ዘውድ ትሆኛለሽ:: " [ኢሳ.፷፪፥፩-፫] (62:1-3)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3
እናቴ ማርያም
"#የኃጢአቴ ቁስል ያላንቺ ጸሎት እንዳይድን ልዑል እግዚአብሔር ያውቃልና፣ #ኃጢአቴ ከዓለም ሁሉ ኃጢአት እንዲበልጥ ተረዳ፣ ንጽሕናሽ ደግሞ ከቅዱሳን ሁሉ ንጽሕና #እንዲበልጥ እንዲበዛ ዐወቀ። ስለዚህም #ፍቅርሽን በልቡናዬ ጨመረ። ጽኑ ቁስል ያለ ጽኑ ዕፁብ ድንቅ መድኃኒት እንዳይጠግ ያውቃልና።
...የእግዚአብሔር የጥበቡ ርቀት ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ? ...ደግነቱና ይቅርታውንስ ማን ይናገራል #በኃጢአት ቁስለኞች ፊት መድኃኒት አዘጋጀ። ተቀብተው በእርሱ እንዲድኑ ነው።
ድንግል ሆይ፤ የእኔን አመንዝራነቴን እናገራለሁ ያንቺን ንጽሕና የልጅሽኝ ቸርነት #አወራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስሕተት ያንቺን ማማለድ የልጅሽንም መታገስ #እናገራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስንፍና ያንቺን ምክር የልጅሽንም ይቅርታ እናገራለሁ።"
የፍቅሯ ኃይል ካረፈበት፣ የስሟም አጠራር ከአንደበቱ ከማይጠፋ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገኘ የልመና ቃል
(አርጋኖነ ማርያም ዘአርብ)
#መልካም__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
"#የኃጢአቴ ቁስል ያላንቺ ጸሎት እንዳይድን ልዑል እግዚአብሔር ያውቃልና፣ #ኃጢአቴ ከዓለም ሁሉ ኃጢአት እንዲበልጥ ተረዳ፣ ንጽሕናሽ ደግሞ ከቅዱሳን ሁሉ ንጽሕና #እንዲበልጥ እንዲበዛ ዐወቀ። ስለዚህም #ፍቅርሽን በልቡናዬ ጨመረ። ጽኑ ቁስል ያለ ጽኑ ዕፁብ ድንቅ መድኃኒት እንዳይጠግ ያውቃልና።
...የእግዚአብሔር የጥበቡ ርቀት ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ? ...ደግነቱና ይቅርታውንስ ማን ይናገራል #በኃጢአት ቁስለኞች ፊት መድኃኒት አዘጋጀ። ተቀብተው በእርሱ እንዲድኑ ነው።
ድንግል ሆይ፤ የእኔን አመንዝራነቴን እናገራለሁ ያንቺን ንጽሕና የልጅሽኝ ቸርነት #አወራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስሕተት ያንቺን ማማለድ የልጅሽንም መታገስ #እናገራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስንፍና ያንቺን ምክር የልጅሽንም ይቅርታ እናገራለሁ።"
የፍቅሯ ኃይል ካረፈበት፣ የስሟም አጠራር ከአንደበቱ ከማይጠፋ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገኘ የልመና ቃል
(አርጋኖነ ማርያም ዘአርብ)
#መልካም__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤16