Telegram Web
1
#ሐምሌ 5

በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት
#የቅዱስ_ጴጥሮስ እና #የቅዱስ_ጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው። በረከታቸው ይደርብን አሜን!!

ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
የዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው። ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው።

በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሣ በማጥመድ አድጐ፣ ሚስት አግብቶ ዕድሜው ሃምሳ ስድስት ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው። በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ፣ በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል። ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል።

(ማቴ. ፲፮፥፲፯ ፣ ዮሐ. ፳፩፥፲፭)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሠራው ስሕተት ንስሐ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል። ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በኋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል። ምንም የእርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል።
በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል።

#መልካም__ቀን🙏

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
🙏82
                        †                           

🕊   💖  ዼጥሮስ ወዻውሎስ  💖   🕊

                         🕊                         

[  እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ   ]

ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕትነትን ከመቀበሉ ጥቂት አስቀድሞ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ከመከረው ምክር እነሆ

❝ በእግዚአብሔር ፊት በሕያዋንና በሙታንም ሊፈርድ ባለው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት በመገለጡና በመንግሥቱም እመክርሃለሁ ...

ቃሉን ስበክ !
በጊዜውም አለጊዜውም ጽና !
ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ ዝለፍና ገሥጽ ምከርም።

ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና ፤ ነገር ግን ጆሮቻቸውን የሚያሳክክ ስለ ሆነ ፥ እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ።

እውነትንም ከመስማት ጆሮቻቸውን ይመልሳሉ ወደ ተረትም ፈቀቅ ይላሉ

አንተ ግን
ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ !
መከራን ተቀበል !
የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ !
አገልግሎትህን ፈጽም
!

በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና የምሄድበትም ጊዜ ደርሶአል።

መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ ሩጫውን ጨርሼአለሁ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም። ❞

[ ፪ኛ ጢሞቴዎስ ፬ ፥ ፩ ]

እንኳን አደረሳችሁ የቅዱስ ጴጥሮስ እና የቅዱስ ጳውሎስ በረከታቸው ይደርብን !

†     🕊   እንኳን  አደረሰን    🕊    †


🕊                        💖                       🕊
2025/07/12 09:45:11
Back to Top
HTML Embed Code: