Telegram Web
#ኪዳነምህረት_እናቴ 16 🙏🙏

#የብርሃን_እናቱ_ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡ መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድህነታችን ተሰራ #ድንግል_ሆይ እውነተኛው የህይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል #ብፅዕናሽን እንናገራለን ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና #እንወድሻለን ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡ ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡

#ዝምተኛይቱ_ድንግል_ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ።

#አንችን_ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው #ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ #እናመሰግንሻለን። ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን🙏

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
11🙏5❤‍🔥2🥰1
                          †                          

     [   🕊  መዝሙረ ተዋሕዶ   🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ኦርቶዶክሳዊ የተቀደሰ ያሬዳዊ ዝማሬ ሰዓት  ]

[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]

🕊

በስመ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚዘጋጅ ንጹሕ መስዋዕት ነው ፥ በአበው ጸሎት ይዘጋጃል ፥ ከስጋዊና ከደማዊ ሀሳብ የራቀ ነው ፥ ልቦናን ወደ ንስሐ ይጠራል ፥ ከኃጢአትና ከክፉ ሥራ የመለየት ኃይል አለው ፥ ክፉ መንፈስን ከሰው ልብ ያርቃል ፥ መረጋጋትን ልቦናን ዘልቆ የሚሰማ ውስጣዊ ሰላምን ይሰጣል ፥ በአሚነ ሥላሴ ያጸናል ፥ የክርስቶስን የባህርይ አምላክነትና መሐሪነት ይመሰክራል ፥ የእመቤታችንን ፍቅር በልቦና ያሳድራል ፥ በእናትነቷና በምልጃዋ እንድንታመን ያደርጋል ፥ በቅዱሳን ጸሎትና በቃል ኪዳናቸው ያጸናል ፥ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን እናውቅ ዘንድ መንገድ ይመራናል ፥ ፈሪሐ  እግዚአብሔርንና ፍቅረ እግዚአብሔርን ያጎናጽፈናል፡፡

†                       †                       †

ተወዳጆችሆይ ፦ በተቀደሰ ሰማያዊ ያሬዳዊ ዜማ ነብሳችንን እናስጊጣት፡፡ ከደጋጎቹ አባቶቻችን ጋር ከዓለም ርኩሰት በተለየ የተቀደሰ ዝማሬ አምላካችን እግዚአብሔርን እናመሥግን፡፡ ለስጋዊ ጆሮዎች ከሚመች ከረከሰ የተሃድሶ የኑፋቄ እርሾ ልቦናችንን እንጠብቅ፡፡ ገንዘብን ስለመውደድ ከሆነ ከሥጋዊ ሥራ ፈጽሞ እንለይ፡፡

🍒

🕊 ከጦመ በኋላ ተራበ ! 🕊  ]

[  " ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው ፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። "  ]

{ ማቴ.፬፥፩ }  


†                       †                       †
💖                    🕊                    💖
👍2
😢8💔5❤‍🔥2
🕊                   

[ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ]

✞ እንኩዋን ለዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ ✞
                   
🕊                       💖                   🕊

[ ዐቢይ ጾም  " የጌታ ጾም " ]

  🍒

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ምዕመናን እንዲጾሟቸው የሠራቻቸው ፯ [ 7 ] አጽዋማት አሏት:: " ጾም " ማለት "መከልከል" ነው::

የምንከለከለው ደግሞ ከኃጢአትና ከክፋት ሲሆን አንድም ሰውነትን ወደዚያ ከሚወስዱ መባልዕት መከልከልን ይመለከታል::

ጾም ለክፉ ሥራ ከሚያነሣሱ የምግብ ዓይነቶች መከልከል ወይም ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መወሰን [ መታቀብ ] ማለት ነው፡፡ ለሰውነት የሚያምረውንና የሚያስጎመዠውን ነገር ሁሉ ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ብሎ መተው ነው፡፡

ጾም ከመንፈሳዊ ተጋድሎዎች አንዱ ነው፡፡ ለሥጋም መንፈሳዊ ልጓም ነው፡፡ ጸዋሚ ሰው ፈቃደ ሥጋውን እየገታ ነፍሱን የሚያለማምድበት ስንቅ ነው፡፡ "ጾም ቁስለ ነፍስን የምትፈውስ ፤ ኃይለ ፍትወትን የምታደክም ፤ የበጎ ምግባራት ሁሉ መጀመሪያ ፤ ከእግዚአብሔር ጸጋን የምታሰጥ ፤ የወንጌል ሥራ መጀመሪያ ፤ የጽሙዳን ክብራቸው ፤ የድንግልና የንጽሕና ጌጣቸው ፤ የንጽሕና መገለጫ ፤ የጸሎት ምክንያት እናት ፤ የዕንባ መገኛ መፍለቂያዋ ፤ አርምሞን የምታስተምር ፤ ለበጎ ሥራ ሁሉ የምታነቃቃ ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ መድኃኒተ ነፍስ ናት፡፡" [ማር ይስሐቅ አንቀጽ ፬፥፮]

ጾም ተድላ ሥጋን የምታጠፋ ፥ የሥጋን ጾር የምታደክም ፥ ቁስለ ነፍስን የምታደርቅ ፥ ለጎልማሶች ጸጥታንና ዕርጋታን የምታስተምር ፥ ከግብረ እንስሳዊ የምትከለክል ፥ ሰው መላእክትን መስሎ የሚኖርባትና ኃይል መንፈሳዊን የሚጎናጸፍባት ደገኛ መሣሪያ ናት፡፡ ከኃጢአት ፆር ከፍትወት አንዱንም አንዱን ድል ለመንሳት ለማጥፋት ፥ የዲያብሎስን ረቂቅ ፍላጻ ለመመከት በጾም መድከም የሥራ ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነች የታወቀ ነው፡፡ ጾም ምህረት መለመኛ ፥ የንስሐ መገለጫ ፥ ከመከራ የሚሠወሩባት ፥ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቃ ርስት መንግሥተ ሰማያት የምታስገባ "ኆኅተ ጽድቅ - የጽድቅ በር" ሆና የተሰጠች ቀዳማዊት ሕግ ናት፡፡

🕊       💖      🕊

[ ዐቢይ ጾም [ ጾመ እግዚእ ] ]


ከ፯ [7] ቱ አጽዋማት አንዱ የሆነው ይህ ጾም

፩. ዐቢይ [ ታላቁ ] ጾም
፪. የጌታ ጾም
፫. ጾመ ሑዳድ
፬. የድል ጾም
፭. የካሳ ጾም
፮. አርባ ጾም
፯. የፍቅር ጾም . . .
በሚሉ መጠሪያዎችም ይታወቃል::

የጾሙ መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት ደግሞ =

፩. ጾመ ሕርቃል
፪. ጾመ በረከት ዘሐዋርያት
፫. ሰሙነ ዘወረደም ይባላል::

የጾሙ የመጀመሪያው ሳምንት [ዘወረደ] የሚጾመው እስከ ፲፪ [ 12 ] ሰዓት ሲሆን ከቅድስት [ ከ፪ [ 2 ] ኛው ሳምንት እስከ ተጽኢኖ [ የኒቆዲሞስ ዓርብ ] ድረስ ደግሞ እስከ ፲፩ [ 11 ] ሰዓት ይጾማል::

በሰሙነ ሕማማት ግን የምንጾመው "እስከ ይሠርቅ ኮከብ" [ እስከ ምሽት ፩ [ 1 ] ሰዓት ] ድረስ ይሆናል::

ነገር ግን ሁሉም እንደ መጠኑ ነውና ከመምሕረ ንስሃ ጋር ሊጨዋወቱት ይገባል:: በዓቢይ ጾም ለቻለ ቂጣ በጨው እየበላ : ውሃ እየተጐነጨ ሊጾም ይገባል:: በእነዚህ ፶፭ [ 55 ] ቀናትም ከዕለተ ሆሳዕና በቀር ከበሮ አይጐሰምም:: ጸናጽል አይጸነጸልም:: ተድላ ደስታም አይደረግም::

አብዝቶ መብላት : ሳቅ ማብዛትና ጌጥን ማብዛትም እንዲሁ አይገባም:: ለቻለ ደግሞ በሌሊት ሰዓታቱን ፡ በነግህ ኪዳንና ስብሐተ ነግሁን : በመዓልት ቅዳሴውን : በሰርክ [ ምሽት ] ደግሞ ምሕላውን ሊሳተፍ ይገባል::

በእነዚህ ፶፭ [ 55 ] ቀናት ፈቃደ ሥጋ ሊደክም : ፈቃደ ነፍስ ልትሰለጥን ግድ ነውና:: ከሌላው ጊዜ በተሻለ ወቅቱ ምጽዋትና ጸሎት የሚደረግበት ነው:: በዚያውም ላይ ነገሮችን እያመቻቹ በእነዚህ ዕለታት ቅዱስ ቃሉን መስማት [ማንበብ] ይገባል:: በትዳር ውስጥ ላሉም መኝታን መለየት ግድ ነው::


ጾሙን የሰላም : የፍቅር : የምሕረት : የፀጋ : የበረከት ያድርግልን:: ጾሞ ለማበርከትም ያብቃን፡፡

" አሁንስ ይላል እግዚአብሔር በፍጹም ልባችሁ በጾምም በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ:: ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ:: አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ: ቁጣው የዘገየ: ምሕረቱም የበዛ: ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ:: " [ትን. ኢዩኤል.፪፥፲፪ (2:12) ]


ወስብሐት ለእግዚአብሔር : ወለወላዲቱ ድንግል : ወለመስቀሉ ክቡር !

         [       ይቆየን ! ]

†                       †                         †
💖                    🕊                     💖
❤‍🔥8🥰3
ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተመረጥሽ #እመቤታችን_ሆይ! አንቺን አናመልክም ነገር ግን ከሁሉ በበለጠ እጅግ በላቀ ምስጋና ክብርሽን እንገልጣለን።

#የተመረጥሽ_ድንግል_እመቤቴ_ማርያም ሆይ ሁልግዜ #በዓይን_ልቦናዬ አይሻለሁ . . . በሃሳቤም በየስፍራው ሁሉ አገኝሻለሁ ልጅሽም የዓለም መድሀኒት ነው ። በተኛሁም ጊዜ እኔን ለመጠበቅ የነቃሽ ነሽ ፣ከመኝታዬም ስነቃ እኔን ለማንሳት የተዘጋጀሽ ነሽ ስቀመጥም እኔን #ለመምከር ትደረሻለሽ ፣ በቆምሁም ጊዜ በቀኜ ትቆሚያለሽ ፣ በተናገርሁም ጊዜ አንደቤቴን ለማጣፈጥ ታከናውኛለሽ ፣ በዝምታዬም ጊዜ ለመጠበቄ ማሞገሻ ነሽ ፣ ሀሴትም ባደረግሁ ጊዜ ተድላ ደስታዬ ነሽ
በእውነት ምን ብዬ እንዴት ልገልጥሽ ይቻለኛል።
ዝክርሽን ዘክሬ በበረከትሽ እንድጎበኝ ፈጣሪ ይርዳኝ።
የእናታችን የኪዳነምህረት እረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን 🙏🙏🙏

#እንኳን_ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የኪዳን በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🙏🙏🙏


@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
9🙏3❤‍🔥1
🕊

[ † እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የኪዳን በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]

† ፯ [ 7 ] ቱ ኪዳናት †

'ተካየደ' ማለት 'ተስማማ: ተማማለ' እንደ ማለት ሲሆን 'ኪዳን' በቁሙ 'ውል: ስምምነት' እንደ ማለት ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::

እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ ፯ [7] እንደ ሆኑ ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን ፯ [7] ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::

"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" [መዝ.፹፰፥፫] [88:3]

፩. " ኪዳነ አዳም "

አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው:: ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ:: [ዘፍ.፫፥፩] [3:1]

አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን ተቀበሉ:: [ቀሌምንጦስ: ገላ.፬፥፬]

፪. " ኪዳነ ኖኅ "

ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት ፲ [10] ትውልድ ዓለም በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ" እንዲል:: [ዘፍ.፱፥፲፪] [9:12]

፫. " ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "

መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ፲፭ [15] ዓመቱ መንኖ: አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት ነበር::

እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: [ዘፍ.፲፬፥፲፯ ፣ ዕብ.፯፥፩]

፬. " ኪዳነ አብርሃም "

ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: [ዘፍ.፲፪፥፩] የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን ሰጠው:: [ዘፍ.፲፯፥፩-፲፬]

፭. " ኪዳነ ሙሴ "

ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ: የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት [የዋህ] ሰው ነው:: በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ፵ [40] ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: [ዘጸ.፳፥፩ 20:1, ፴፩፥፲፰ (31:18)]

፮. " ኪዳነ ዳዊት "

ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" [መዝ.፻፴፩፥፲፩] [131:11] ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሰሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: [መዝ.፹፰፥፴፭]

፯. " ኪዳነ ምሕረት "

በብሉይ ኪዳን የነበሩ ፮ [6] ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ::

በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ: ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት [የምሕረት ኪዳን] የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::

የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ: ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት::

የእርሷ ኪዳን ፮ [6] ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::

እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ! በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ ፪ [2] ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር እንኖራለን::

" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ: ኃጢአተነ: ወጌጋየነ:
ማርያም እሙ ለእግዚእነ:
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ::"

"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"

የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት: ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ አማላጅ ናት::

በዚህች ዕለት የካቲት ፲፮ [16] ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል:: በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳት አያይም ብሏታል::

ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም: የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::

🕊

[  † የካቲት ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. ኪዳነ ምሕረት [የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም]
፪. ቅድስት ኤልሳቤጥ [የመጥምቁ ዮሐንስ እናት / የእመቤታችን አክስት / የሶፍያ ልጅ]
፫. ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ [የቅ/ላሊበላ ወንድም]

[   † ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
፪. አባ አቡናፍር ገዳማዊ
፫. አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
፬. አባ ዳንኤል ጻድቅ

" . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:- አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት::" [ሉቃ.፩፥፴፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
4👍4
16🥰4❤‍🔥2
                         †                         

🕊   እ ን ኳ ን   አ ደ ረ ሳ ች ሁ   🕊

🌼▬▬▬  🌼  ▬▬▬🌼

❝ ሚ ሠናይ ከመ ጼና ጽጌ ልሑይ ፣
በኲሉ ጊዜ ምሒረ ነዳይ ፣
በእንተ ኪዳንኪ ድንግል ለበላዔ ሰብእ ጊጉይ ፣
ሶበ ዐብየ እምኀጢአቱ ክበደ መድሎቱ ለማይ ፣
ለተአምርኪ በሰማይ ተገብረ ግናይ ❞

❝ አንቲ ውእቱ ለእግዚአብሔር አትሮኑሱ
ለአዳም ክብረ ሞገሱ
በኪዳንኪ ኃጥኣን መንግሥተ ሰማያት ይወርሱ ❞

🕊

[ ኹል ጊዜ ለደኻ መራራት መመጽወት እንደ ለመለመ አበባ ያማረ ነው [ ምን ያምር ? ] ድንግል በቃል ኪዳንሽ ምክንያት ከበላዔ ሰብእ ኀጢአት የውሃ ሚዛን በልጦ በመታየቱ ለተአምርሽ በሰማይ ምስጋና ኾነ። ]

[ የእግዚአብሔር አትሮንሱ [ ዙፋኑ ] የአዳም የግርማው ክብር አንቺ ነሽ ፤ ኃጥኣንም በቃል ኪዳንሽ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ። ]

[  አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ  ]


[       🕊    ክብርት ሰንበት    🕊      ]


🕊                        💖                       🕊
4
2025/07/12 13:59:57
Back to Top
HTML Embed Code: