#ድንግል_ሆይ ! በአፍና በመጽሐፍ ያይደል ፤ በልቤና በሕይወቴ ውስጥ #የእናትነት_ፍቅርሽን አውቀዋለሁ። ስለዚህም አንችን በእናትነት የሰጠኝን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ። በፊትሽ ያፈሰሱኩት እንባ ያልታበሰበት ጊዜ የለም። #ለነፍሴ_ነፍሷ ነሽ ብያለሁ ...
#የእመቤታችንን ፍቅሯን በልባችን ፣ ውዳሴዋን በአንደበታችን ያብዛልን።
በእመብርሃን ፣ በእመሕይዎት
ቃልኪዳን ይጠብቀን ፤ አሜን። 🙏🙏🙏🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#የእመቤታችንን ፍቅሯን በልባችን ፣ ውዳሴዋን በአንደበታችን ያብዛልን።
በእመብርሃን ፣ በእመሕይዎት
ቃልኪዳን ይጠብቀን ፤ አሜን። 🙏🙏🙏🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤12👍2
†
[ 🕊 የዐቢይ ጾም ሳምንታት 🕊 ]
💖
ዐቢይ ጾም በያዘው በ፶፭ ቀኑ ውስጥ ሰባት ቅዳሜና ስምንት እሑዶቸን ይዟል ፤ የእነዚህ የስምንቱ እሑዶች የተለያየ ስያሜ አላቸው፡፡ ስያሜአቸውንም የሰጣቸው የቤተ ክርስቲያናችን የዜማው ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ዘወረደ ፣ ቅድስት ፣ ምኩራብ ፣ ደብረዘይት ፣ ገብረ ኄር ፣ ኒቆዲሞስ ፣ መፃጉዕ ፣ ሆሣዕና ናቸው፡፡
🕊 💖 🕊
[ ፩ ኛ. ዘወረደ ፦ ]
በመጀመርያው ሳምንት ዘወረደ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት መውረዱን ፣ ከአመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን እና እኛን ማዳኑን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚወሳበትና የሚዘከርበት ወቅት ሲሆን ይህንንም የሚዘክሩ መዝሙሮች ይቀርባሉ ፤ ትምህርቶች ይሰጣሉ ፤ ይህንንም እያሰብን ጾሙን እንጾማለን፡፡
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ለሐዋርያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን በሥርዓቱ ጹመን እንዲንጠቀም እርዳን ፤ አሜን !
† † †
🕊 💖 🕊
[ 🕊 የዐቢይ ጾም ሳምንታት 🕊 ]
💖
ዐቢይ ጾም በያዘው በ፶፭ ቀኑ ውስጥ ሰባት ቅዳሜና ስምንት እሑዶቸን ይዟል ፤ የእነዚህ የስምንቱ እሑዶች የተለያየ ስያሜ አላቸው፡፡ ስያሜአቸውንም የሰጣቸው የቤተ ክርስቲያናችን የዜማው ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ዘወረደ ፣ ቅድስት ፣ ምኩራብ ፣ ደብረዘይት ፣ ገብረ ኄር ፣ ኒቆዲሞስ ፣ መፃጉዕ ፣ ሆሣዕና ናቸው፡፡
🕊 💖 🕊
[ ፩ ኛ. ዘወረደ ፦ ]
በመጀመርያው ሳምንት ዘወረደ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት መውረዱን ፣ ከአመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን እና እኛን ማዳኑን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚወሳበትና የሚዘከርበት ወቅት ሲሆን ይህንንም የሚዘክሩ መዝሙሮች ይቀርባሉ ፤ ትምህርቶች ይሰጣሉ ፤ ይህንንም እያሰብን ጾሙን እንጾማለን፡፡
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ለሐዋርያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን በሥርዓቱ ጹመን እንዲንጠቀም እርዳን ፤ አሜን !
† † †
🕊 💖 🕊
❤4👍1
ኪዳነ ምህረት
#መታሰቢያዬን_ለሚያደርጉ
#በስሜ_አቢያተ_ክርስቲያን_ለሚሠሩ
#የተራቆተውን_ለሚያለብሱ
#የተራበውን_ለሚያጠግቡ
#የተጠማውንም_ለሚያጠጡ
#የታመመውን_ለሚጐበኙ
#ያዘነውን_ለሚያረጋጉ
#የተከዘውንም_ደስ_ለሚያሰኙ
#ምስጋናዬን_ለሚጽፉ
#ልጆቹንም_በስሜ_ለሚሰይም
#በበዓሌም_ቀን_በማኅሌት_ለሚያመሰግን
#አቤቱ_ዐይን_ያላየውን_ጆሮ_ያልሰማውን_በሰውም_ልቡና_ያልታሰበውን_በጎ_ዋጋ_ስጣቸው
#በአማላጅነቴም የሚታመነውን ሁሉ
ከሲኦል ነጻ አድርገው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን
ረኃቡንና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው
#ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ
#የሰጠሁሽም_ቃል_ኪዳን እንዳይታበል በራሴ ማልኩልሽ አላት ።
#የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም
ጣዕሟን በአንደበታችን ፤ ፍቅሯን በልባችን ያሳድርልን
ጽኑ ቃል ኪዳኗ በአማላጅነቷ ከምናምን ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር 🙏🙏🙏
ለአመቱ በሰላም ያድርሰን 🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#መታሰቢያዬን_ለሚያደርጉ
#በስሜ_አቢያተ_ክርስቲያን_ለሚሠሩ
#የተራቆተውን_ለሚያለብሱ
#የተራበውን_ለሚያጠግቡ
#የተጠማውንም_ለሚያጠጡ
#የታመመውን_ለሚጐበኙ
#ያዘነውን_ለሚያረጋጉ
#የተከዘውንም_ደስ_ለሚያሰኙ
#ምስጋናዬን_ለሚጽፉ
#ልጆቹንም_በስሜ_ለሚሰይም
#በበዓሌም_ቀን_በማኅሌት_ለሚያመሰግን
#አቤቱ_ዐይን_ያላየውን_ጆሮ_ያልሰማውን_በሰውም_ልቡና_ያልታሰበውን_በጎ_ዋጋ_ስጣቸው
#በአማላጅነቴም የሚታመነውን ሁሉ
ከሲኦል ነጻ አድርገው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን
ረኃቡንና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው
#ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ
#የሰጠሁሽም_ቃል_ኪዳን እንዳይታበል በራሴ ማልኩልሽ አላት ።
#የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም
ጣዕሟን በአንደበታችን ፤ ፍቅሯን በልባችን ያሳድርልን
ጽኑ ቃል ኪዳኗ በአማላጅነቷ ከምናምን ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር 🙏🙏🙏
ለአመቱ በሰላም ያድርሰን 🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤18❤🔥1👍1
🕊
[ † እንኩዋን ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት † 🕊
ቅዱሳን ነቢያት እጅግ ብዙ ናቸው:: ከፈጣሪያቸው የተቀበሉት ጸጋም ብዙና ልዩ ልዩ ነው:: ያም ሆኖ ከሁሉም ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ይበልጣል:: መጽሐፍ እንደሚል ከእርሱም በፊት ቢሆን ከእርሱ በሁዋላ እንደ እርሱ ያለ ነቢይ አልተነሳምና:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ዓለም በተፈጠረ በ ፫ ሺህ ፮ መቶ [ 3,600 ] ዓመት እሥራኤል በረሃብ ምክንያት ፸፭ [ 75 ] ራሱን ወደ ምድረ ግብፅ ወረደ:: በዚያም ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ለ፪ መቶ ፲፭ [ 215 ] ዓመታት ተከብረው: ለ፪ መቶ ፲፭ [ 215 ] ዓመታት ደግሞ በባርነት: በድምሩ ለ፬ መቶ ፴ [ 430 ] ዓመታት በምድረ ግብፅ ኑረዋል::
- በባርነት ዘመናቸውም 'ራምሴና ጋምሴ' የሚባሉ ፪ [2] ከተሞችን [ዛሬ ፒራሚዶች የምንላቸውን] ገንብተዋል:: ግፋቸው እየበዛ ሲሔድ ግን ጩኸታቸው ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ:: ያድናቸውም ዘንድ አንድ ቅዱስ ሰው እንዲወለድ አደረገ:: ይኽም ሰው ሙሴ ይባላል::
- ወላጆቹ መታመናቸውን በፈጣሪያቸው ያደረጉ 'እንበረም'ና 'ዮካብድ' ሲሆኑ ከሌዊ ነገድ ናቸው:: ከሙሴ ውጪም አሮንና ማርያምን ወልደዋል:: ቅዱስ ሙሴ በተወለደበት ወራት ወንድ የእሥራኤል ሕጻናት ይፈጁ ነበር:: ጌታ ግን በገዳዮቹ ልቡና ርሕራሔን አምጥቶ አትርፎታል::
- በሁዋላም በ፫ [ 3 ] ወሩ ዓባይ ወንዝ ላይ ጥለውት ተርሙት [የፈርኦን ልጅ ናት] ወስዳ በቤተ መንግስት አሳድጋዋለች:: 'ሙሴ' ያለችውም እርሷ ናት:: 'ዕጉዋለ ማይ / እማይ ዘረከብክዎ' [ከውሃ የተገኘ] ለማለት ነው:: ወላጆቹ ያወጡለት ስም ግን 'ምልክአም' ይባላል:: ገና ሲወለድ ፊቱ እንደ መልአክ ያበራ ነበርና::
- ቅዱስ ሙሴ ፭ [ 5 ] ዓመት በሆነው ጊዜ ፈርኦንን በጥፊ በመማታቱ ለፍርድ ቀርቦ እሳትን በመብላቱ አንደበቱ ኮልታፋ ሆኖ ቀርቷል:: እናቱ ዮካብድ ሞግዚት ሆና ስላሳደገችው ፵ [40] ዓመት በሆነው ጊዜ የፈርኦንን ቤት ምቾትና የንጉሥ ልጅ መባልን ናቀ:: ቅዱስ ዻውሎስ እንደሚለው በአሕዛብ ቤት ካለ ምቾት ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራን ሊቀበል ወዷልና:: [ዕብ.፲፩፥፳፬] [11:24]
- አንድ ቀንም ለዕብራዊ ወገኑ ተበቅሎ ግብጻዊውን ገድሎት ወደ ምድያም ሸሸ:: በዚያም ለ፵ [40] ዓመታት የካህኑን ዮቶርን በጐች እየጠበቀ: ኢትዮዽያዊቱን ሲፓራን አግብቶ ኖረ:: ልጆንም አፈራ:: ፹ [80] ዓመት በሞላው ጊዜ እግዚአብሔር በደብረ ሲና ተናገረው:: ሕዝቡንም ከባርነት ቀንበር እንዲታደግ ላከው::
- ቅዱስ ሙሴም ከወንድሙ አሮንና ከአውሴ [ኢያሱ] ጋር ግብጻውያንን በ፱ [9] መቅሰፍት: በ፲ [10] ኛ ሞተ በኩር መታ:: እሥራኤልንም ነጻ አወጣ:: ሊቀ ነቢያት የሠራቸው ሥራዎች ተዘርዝረው የሚያልቁ አይደሉም::
- እርሱ ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ ሕዝቡን በደረቅ አሻግሯል::
- ግብጻውያንን ከነሠረገሎቻቸው በባሕር ውስጥ አስጥሟል::
- ለሕዝቡ መና ከደመና አውርዷል::
- ውሃን ከጨንጫ [ከዓለት] ላይ አፍልቁዋል::
- በብርሃን ምሰሶ መርቷቸዋል::
- በ፯ [7] ደመና ጋርዷቸዋል::
- ጠላቶቻቸውን ሁሉ ድል ነስቶላቸዋል::
- ስለዚህ ፈንታ ግን ወገኖቹ ብዙ አሰቃይተውታል:: እርሱ ግን ደግ: ቅንና የዋህ ሰው ነውና ብዙ ጊዜ ራሱን ለእነሱ አሳልፎ ሰጥቷል:: "ሙሴሰ የዋህ እምኩሎሙ ደቂቀ እሥራኤል" እንዲል:: [ዘኁ.፲፪፥፫] [12:3] ቅዱስ ሙሴ ለ፵ [40] ዓመታት ሕዝቡን ሲመራ ከእግዚአብሔር ጋር ለ፭ መቶ ፸ [570] ጊዜ ተነጋግሯል::
- ከጸጋው ብዛትም ፊቱ ብርሃን ስለ ነበር ሰዎች እርሱን ማየት አይችሉም ነበር:: ታቦተ ጽዮንንና 10ሩ ቃላትን ተቀብሎ ጽላቱ ቢሰበሩ ራሱ ሠርቶ በጌታ እጅ ቃላቱ ተጽፈውለታል:: "የቀረው የቅዱሱ ሕይወት በመጻሕፍተ ኦሪት [በብሔረ ኦሪት] ውስጥ የተጻፉ አይደሉምን?"
- እኔ ግን ደካማ ነኝና ይህቺ ትብቃኝ:: ቅዱስ: ክቡር: ታላቅ: ጻድቅ: ነቢይና ደግ ሰው ቅዱስ ሙሴ በ፻፳ [120] ዓመቱ ዐርፎ በደብረ ናባው ሊቃነ መላእክት ቅዱሳን ሚካኤል: ገብርኤልና ሳቁኤል ቀብረውታል:: መቃብሩንም ሠውረዋል:: [ይሁዳ.፩፥፱] [1:9]
አምላከ ሊቀ ነቢያት ደግነቱን አስቦ ከግራ ቁመት: ከገሃነመ እሳት ይሰውረን:: በረከቱንም አብዝቶ ያድለን::
🕊
[ † የካቲት ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት [በ፻፳ [120] ዓመቱ ደብረ ናባው ላይ ተቀብሯል]
፪. ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ [ኁለተኛው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት [ቀዳሜ ሰማዕት]
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ ዘብዴዎስ]
፫. ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ዘቆዽሮስ
፬. ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
፭. አባ ገሪማ ዘመደራ
፮. አባ ዸላሞን ፈላሢ
፯. አባ ለትጹን የዋህ
† " ሙሴ ካደገ በሁዋላ የፈርኦን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ:: ከግብጽም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለጠግነት እንዲሆን አስቧልና:: ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ:: ብድራቱን ትኩር ብሎ ተመልክቷልና::" † [ዕብ.፲፩፥፳፬] [11:24]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኩዋን ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት † 🕊
ቅዱሳን ነቢያት እጅግ ብዙ ናቸው:: ከፈጣሪያቸው የተቀበሉት ጸጋም ብዙና ልዩ ልዩ ነው:: ያም ሆኖ ከሁሉም ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ይበልጣል:: መጽሐፍ እንደሚል ከእርሱም በፊት ቢሆን ከእርሱ በሁዋላ እንደ እርሱ ያለ ነቢይ አልተነሳምና:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ዓለም በተፈጠረ በ ፫ ሺህ ፮ መቶ [ 3,600 ] ዓመት እሥራኤል በረሃብ ምክንያት ፸፭ [ 75 ] ራሱን ወደ ምድረ ግብፅ ወረደ:: በዚያም ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ለ፪ መቶ ፲፭ [ 215 ] ዓመታት ተከብረው: ለ፪ መቶ ፲፭ [ 215 ] ዓመታት ደግሞ በባርነት: በድምሩ ለ፬ መቶ ፴ [ 430 ] ዓመታት በምድረ ግብፅ ኑረዋል::
- በባርነት ዘመናቸውም 'ራምሴና ጋምሴ' የሚባሉ ፪ [2] ከተሞችን [ዛሬ ፒራሚዶች የምንላቸውን] ገንብተዋል:: ግፋቸው እየበዛ ሲሔድ ግን ጩኸታቸው ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ:: ያድናቸውም ዘንድ አንድ ቅዱስ ሰው እንዲወለድ አደረገ:: ይኽም ሰው ሙሴ ይባላል::
- ወላጆቹ መታመናቸውን በፈጣሪያቸው ያደረጉ 'እንበረም'ና 'ዮካብድ' ሲሆኑ ከሌዊ ነገድ ናቸው:: ከሙሴ ውጪም አሮንና ማርያምን ወልደዋል:: ቅዱስ ሙሴ በተወለደበት ወራት ወንድ የእሥራኤል ሕጻናት ይፈጁ ነበር:: ጌታ ግን በገዳዮቹ ልቡና ርሕራሔን አምጥቶ አትርፎታል::
- በሁዋላም በ፫ [ 3 ] ወሩ ዓባይ ወንዝ ላይ ጥለውት ተርሙት [የፈርኦን ልጅ ናት] ወስዳ በቤተ መንግስት አሳድጋዋለች:: 'ሙሴ' ያለችውም እርሷ ናት:: 'ዕጉዋለ ማይ / እማይ ዘረከብክዎ' [ከውሃ የተገኘ] ለማለት ነው:: ወላጆቹ ያወጡለት ስም ግን 'ምልክአም' ይባላል:: ገና ሲወለድ ፊቱ እንደ መልአክ ያበራ ነበርና::
- ቅዱስ ሙሴ ፭ [ 5 ] ዓመት በሆነው ጊዜ ፈርኦንን በጥፊ በመማታቱ ለፍርድ ቀርቦ እሳትን በመብላቱ አንደበቱ ኮልታፋ ሆኖ ቀርቷል:: እናቱ ዮካብድ ሞግዚት ሆና ስላሳደገችው ፵ [40] ዓመት በሆነው ጊዜ የፈርኦንን ቤት ምቾትና የንጉሥ ልጅ መባልን ናቀ:: ቅዱስ ዻውሎስ እንደሚለው በአሕዛብ ቤት ካለ ምቾት ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራን ሊቀበል ወዷልና:: [ዕብ.፲፩፥፳፬] [11:24]
- አንድ ቀንም ለዕብራዊ ወገኑ ተበቅሎ ግብጻዊውን ገድሎት ወደ ምድያም ሸሸ:: በዚያም ለ፵ [40] ዓመታት የካህኑን ዮቶርን በጐች እየጠበቀ: ኢትዮዽያዊቱን ሲፓራን አግብቶ ኖረ:: ልጆንም አፈራ:: ፹ [80] ዓመት በሞላው ጊዜ እግዚአብሔር በደብረ ሲና ተናገረው:: ሕዝቡንም ከባርነት ቀንበር እንዲታደግ ላከው::
- ቅዱስ ሙሴም ከወንድሙ አሮንና ከአውሴ [ኢያሱ] ጋር ግብጻውያንን በ፱ [9] መቅሰፍት: በ፲ [10] ኛ ሞተ በኩር መታ:: እሥራኤልንም ነጻ አወጣ:: ሊቀ ነቢያት የሠራቸው ሥራዎች ተዘርዝረው የሚያልቁ አይደሉም::
- እርሱ ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ ሕዝቡን በደረቅ አሻግሯል::
- ግብጻውያንን ከነሠረገሎቻቸው በባሕር ውስጥ አስጥሟል::
- ለሕዝቡ መና ከደመና አውርዷል::
- ውሃን ከጨንጫ [ከዓለት] ላይ አፍልቁዋል::
- በብርሃን ምሰሶ መርቷቸዋል::
- በ፯ [7] ደመና ጋርዷቸዋል::
- ጠላቶቻቸውን ሁሉ ድል ነስቶላቸዋል::
- ስለዚህ ፈንታ ግን ወገኖቹ ብዙ አሰቃይተውታል:: እርሱ ግን ደግ: ቅንና የዋህ ሰው ነውና ብዙ ጊዜ ራሱን ለእነሱ አሳልፎ ሰጥቷል:: "ሙሴሰ የዋህ እምኩሎሙ ደቂቀ እሥራኤል" እንዲል:: [ዘኁ.፲፪፥፫] [12:3] ቅዱስ ሙሴ ለ፵ [40] ዓመታት ሕዝቡን ሲመራ ከእግዚአብሔር ጋር ለ፭ መቶ ፸ [570] ጊዜ ተነጋግሯል::
- ከጸጋው ብዛትም ፊቱ ብርሃን ስለ ነበር ሰዎች እርሱን ማየት አይችሉም ነበር:: ታቦተ ጽዮንንና 10ሩ ቃላትን ተቀብሎ ጽላቱ ቢሰበሩ ራሱ ሠርቶ በጌታ እጅ ቃላቱ ተጽፈውለታል:: "የቀረው የቅዱሱ ሕይወት በመጻሕፍተ ኦሪት [በብሔረ ኦሪት] ውስጥ የተጻፉ አይደሉምን?"
- እኔ ግን ደካማ ነኝና ይህቺ ትብቃኝ:: ቅዱስ: ክቡር: ታላቅ: ጻድቅ: ነቢይና ደግ ሰው ቅዱስ ሙሴ በ፻፳ [120] ዓመቱ ዐርፎ በደብረ ናባው ሊቃነ መላእክት ቅዱሳን ሚካኤል: ገብርኤልና ሳቁኤል ቀብረውታል:: መቃብሩንም ሠውረዋል:: [ይሁዳ.፩፥፱] [1:9]
አምላከ ሊቀ ነቢያት ደግነቱን አስቦ ከግራ ቁመት: ከገሃነመ እሳት ይሰውረን:: በረከቱንም አብዝቶ ያድለን::
🕊
[ † የካቲት ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት [በ፻፳ [120] ዓመቱ ደብረ ናባው ላይ ተቀብሯል]
፪. ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ [ኁለተኛው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት [ቀዳሜ ሰማዕት]
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ ዘብዴዎስ]
፫. ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ዘቆዽሮስ
፬. ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
፭. አባ ገሪማ ዘመደራ
፮. አባ ዸላሞን ፈላሢ
፯. አባ ለትጹን የዋህ
† " ሙሴ ካደገ በሁዋላ የፈርኦን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ:: ከግብጽም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለጠግነት እንዲሆን አስቧልና:: ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ:: ብድራቱን ትኩር ብሎ ተመልክቷልና::" † [ዕብ.፲፩፥፳፬] [11:24]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤2👍2
ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡
የዘወረደ መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ
ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ ለእርሱም መገዛት ደስ ይበላችሁ። እግዚአብሔር ቸር ምሕረቱም ለዘላለም፣ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና። እኛስ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን፤ ወደ ደጁ በመገዛት፣ ወደ አደባባዮችም በምስጋና ግቡ፤ ጾምን እንጹም፤ ጓደኞቻችንን እናፍቅር፤ እርስ በርሳችንም እንፋቀር። ሰንበት ስለሰው ተሠርታለችና ሰንበትን እናክብር። እውነትንም እንሥራ፤ አቤቱ ምሕረትንና ፍርድን እቀኝልሃለሁ፤ እዘምራለሁ፤ ንጹሕ መንገድንም አስተውላለሁ።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡
የዘወረደ መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ
ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ ለእርሱም መገዛት ደስ ይበላችሁ። እግዚአብሔር ቸር ምሕረቱም ለዘላለም፣ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና። እኛስ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን፤ ወደ ደጁ በመገዛት፣ ወደ አደባባዮችም በምስጋና ግቡ፤ ጾምን እንጹም፤ ጓደኞቻችንን እናፍቅር፤ እርስ በርሳችንም እንፋቀር። ሰንበት ስለሰው ተሠርታለችና ሰንበትን እናክብር። እውነትንም እንሥራ፤ አቤቱ ምሕረትንና ፍርድን እቀኝልሃለሁ፤ እዘምራለሁ፤ ንጹሕ መንገድንም አስተውላለሁ።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤17👍1
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] "መንፈሳዊው መሰላል" ድርሳን ]
🕊
❝ የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር እንደ መሆኑ ፣ ከእርሱ ውጭ በራሱ ሕይወት ያለው ነገር የለም፡፡
ስለሆነም መንፈሳዊ ሕይወት ስንል ሰዎችና መላእክት ከእግዚአብሔር ሕይወትነት ያላቸው ሱታፌ ሲሆን ይህ ሱታፌም አንድ ቦታ ላይ የሚያቆምና የተገደበ ሳይሆን እያደገ የሚሄድ ነው፡፡
እግዚአብሔር ፍጻሜ የሌለውና “እስከዚህ ድረስ” ተብሎ የማይወሰን አምላክ እንደመሆኑ ፣ ከእርሱ ጋር ኅብረትና አንድነት ይኖራቸው ዘንድ በእርሱ ሕይወት የሚሳተፉ ሁሉ ጉዟቸው መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም፡፡ የመንፈሳዊ ጉዞ አስደሳችነቱም ይህ ነው ፤ ወደማይደረስበት ፣ ግን ደግሞ ከመጀመሪያው ጀምሮ አብሮ ወዳለ አምላክ የሚደረግ የማያቋርጥ ጉዞ !
ይህ ጉዞ ፣ ያዕቆብ ከምድር እስከ ሰማይ ተዘርግቶ ባየው መሰላል አንጻር ሥዕላዊ በሆነ ሁኔታ ተገልጦልናል፡፡ በመሰላሉ ላይ [ ከመሰላሉ ጫፍ ላይ ሳይሆን ከመሰላሉ በላይ ] እግዚአብሔር “ተቀምጦ” ነበር፡፡ መሰላሉ በመሬት ላይ የተዘረጋ መሆኑ እግዚአብሔር ወደ እርሱ የምንወጣበትን የቅድስና መሰላል ልንደርስበት በምንችለው በመሬት ላይ የዘረጋልን መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ፣ እግዚአብሔር ከመሰላሉ በላይ ቆሞ መታየቱ ደግሞ ከላይ ሆኖ “አይዟችሁ ፣ ወደ እኔ ኑ" እያለ በፍቅሩ የሚጠራንና የሚስበን እርሱው ራሱ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ስለዚህ ከታች ከመሬቱ ጀምሮ የሚጠራንና የሚስበን ፣ በመሰላሉ ላይ የትኛውም ደረጃ ላይ ብንደርስም አሁንም ከዚያ በላይ ወዳለው እንድንቀጥል የሚያደርገን ከመሰላሉ በላይ ያለው እርሱ ነው፡፡
እንደዚያ ሆኖም ግን እርሱ ከመሰላሉ በላይ [ ማለትም በባሕርዩ ሊደረስበት የማይችል ] ነው፡፡ እግዚአብሔር ማለት ይህ ነውና ፤ ከራሳችን በላይ ለራሳችን የቀረበ የውስጥና የቅርብ መጋቢና ተንከባካቢ አባት ፣ ሆኖም ግን በባሕርዩ የማይታወቅና የማይደረስበት ረቂቅ አምላክ ! ❞
[ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ በቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] "መንፈሳዊው መሰላል" ድርሳን ትርጓሜ ላይ የሰጡት አስተያየት ]
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] "መንፈሳዊው መሰላል" ድርሳን ]
🕊
❝ የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር እንደ መሆኑ ፣ ከእርሱ ውጭ በራሱ ሕይወት ያለው ነገር የለም፡፡
ስለሆነም መንፈሳዊ ሕይወት ስንል ሰዎችና መላእክት ከእግዚአብሔር ሕይወትነት ያላቸው ሱታፌ ሲሆን ይህ ሱታፌም አንድ ቦታ ላይ የሚያቆምና የተገደበ ሳይሆን እያደገ የሚሄድ ነው፡፡
እግዚአብሔር ፍጻሜ የሌለውና “እስከዚህ ድረስ” ተብሎ የማይወሰን አምላክ እንደመሆኑ ፣ ከእርሱ ጋር ኅብረትና አንድነት ይኖራቸው ዘንድ በእርሱ ሕይወት የሚሳተፉ ሁሉ ጉዟቸው መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም፡፡ የመንፈሳዊ ጉዞ አስደሳችነቱም ይህ ነው ፤ ወደማይደረስበት ፣ ግን ደግሞ ከመጀመሪያው ጀምሮ አብሮ ወዳለ አምላክ የሚደረግ የማያቋርጥ ጉዞ !
ይህ ጉዞ ፣ ያዕቆብ ከምድር እስከ ሰማይ ተዘርግቶ ባየው መሰላል አንጻር ሥዕላዊ በሆነ ሁኔታ ተገልጦልናል፡፡ በመሰላሉ ላይ [ ከመሰላሉ ጫፍ ላይ ሳይሆን ከመሰላሉ በላይ ] እግዚአብሔር “ተቀምጦ” ነበር፡፡ መሰላሉ በመሬት ላይ የተዘረጋ መሆኑ እግዚአብሔር ወደ እርሱ የምንወጣበትን የቅድስና መሰላል ልንደርስበት በምንችለው በመሬት ላይ የዘረጋልን መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ፣ እግዚአብሔር ከመሰላሉ በላይ ቆሞ መታየቱ ደግሞ ከላይ ሆኖ “አይዟችሁ ፣ ወደ እኔ ኑ" እያለ በፍቅሩ የሚጠራንና የሚስበን እርሱው ራሱ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ስለዚህ ከታች ከመሬቱ ጀምሮ የሚጠራንና የሚስበን ፣ በመሰላሉ ላይ የትኛውም ደረጃ ላይ ብንደርስም አሁንም ከዚያ በላይ ወዳለው እንድንቀጥል የሚያደርገን ከመሰላሉ በላይ ያለው እርሱ ነው፡፡
እንደዚያ ሆኖም ግን እርሱ ከመሰላሉ በላይ [ ማለትም በባሕርዩ ሊደረስበት የማይችል ] ነው፡፡ እግዚአብሔር ማለት ይህ ነውና ፤ ከራሳችን በላይ ለራሳችን የቀረበ የውስጥና የቅርብ መጋቢና ተንከባካቢ አባት ፣ ሆኖም ግን በባሕርዩ የማይታወቅና የማይደረስበት ረቂቅ አምላክ ! ❞
[ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ በቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] "መንፈሳዊው መሰላል" ድርሳን ትርጓሜ ላይ የሰጡት አስተያየት ]
🕊 💖 🕊
❤3👍1
†
† 🕊 ዘ ወ ረ ደ 🕊 †
[ የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት ! ]
💖
❝ የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንደዚህ በልጆቿ ስትደምቅ እናንተም ጉባኤውን ለመታደም ደስ ብሏችሁ ተሰባስባችሁ ስትመጡ ዐይቼ ሐሴት አደረግሁኝ ፤ ደስም አለኝ፡፡ ፊታችሁ እንዴት በደስታ እንደተመላ ስመለከት ጠቢቡ ፦ "ልብ ደስ ሲለው ፊት ይበራል" እንዳለው ልባችሁ ምን ያህል እንደተደሰተ ተገነዘብሁኝ፡፡ [ምሳ.፲፭፥፲፫] በመሆኑም ዛሬ ማለዳ የተነሳሁት ከወትሮ በተለየ ትጋት ነው፡፡ ይኸውም ይህን መንፈሳዊ ደስታ ከእናንተ ጋር እንድካፈልና ቀጣዩ ወራት ቁስለ ነፍሳችሁ ድኅነት የሚያገኝበት ወርሐ ጾም መኾኑን አበስራችሁ ዘንድ ነው፡፡ የሁላችንም ጌታ ልዑል እግዚአብሔር ልክ እንደ ደግ አባት ባለፉት ወራት ለሠራነው ኃጢአት ሥርየት እናገኝበት ዘንድ ሽቶ መድኃኒት የሚሆን ቅዱስ ጾምን አዘጋጅቶልናል፡፡
ስለዚህ የነፍሳችን ጠባቂ እግዚአብሔር የሕመማችንን ፈውስ የምናገኝበትን መድኃኒት ስላዘጋጀልን እያመሰገንን ወርሐ ጾሙን ደስ ብሎን ልንቀበለው ይገባናል፡፡ ከእኛ መካከል ጾም በመግባቱ አንድስ እንኳን የሚከፋው ወይም የሚበሳጭ ሊኖር አይገባም፡፡ ወርሐ ጾሙን እንዲህ ደስ ተሰኝተን መቀበላችንን ዐይተውም አሕዛብ ይፈሩ ፤ አይሁድም ይራዱ፡፡ በእኛና በእነርሱ መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ዐይተው የማሩ፡፡
የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በዓል የምትሠራው ምእመናን ራሳቸውን መግዛት እንዲችሉ ፣ በበጎ ምግባር ያጌጡ ያሸበረቁ እንዲሆኑ እንደሆነ እነርሱ ግን በዓላትን የሚያደርጉት በዘፈንና በስካር ይህንም በመሰለ በሌላ ጸያፍ ግብር ለመንከባለል እንደኾነ ለይተው ይወቁ፡፡ በእርግጥም በዓል ተከበረ የሚባለው ፦ ሰዎች ነፍሳቸውን ካዳኑበት ፣ ውስጣዊ ሰላምንና ፍቅረ ቢጽን [ወንድምን መውደድ] ገንዘብ ካደረጉበት ፣ ዕለት ዕለት ከሚያጋጥማቸው የነፍስ መታወክ ካረፉበት ፣ ያለ ሁካታና ጋጋታ እንዲሁም እንስሳትን በማረድ ከልክ በላይ ከኾነ መብልና መጠጥ ርቀው ያከበሩት እንደሆነ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በዓል ተከበረ የሚባለው ፦ አርምሞንና ጸጥታን ፣ ፍቅርንና ደስታን ፣ ሰላምንና ራስን መግዛትን ፣ እንዲሁም ሌሎች እዚህ መዘርዘር የማንችላቸውን ብዙ ምግባር ትሩፋቶችን ገንዘብ ያደረግንበት እንደ ኾነ ነው፡፡ ❞
[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
† 🕊 ዘ ወ ረ ደ 🕊 †
[ የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት ! ]
💖
❝ የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንደዚህ በልጆቿ ስትደምቅ እናንተም ጉባኤውን ለመታደም ደስ ብሏችሁ ተሰባስባችሁ ስትመጡ ዐይቼ ሐሴት አደረግሁኝ ፤ ደስም አለኝ፡፡ ፊታችሁ እንዴት በደስታ እንደተመላ ስመለከት ጠቢቡ ፦ "ልብ ደስ ሲለው ፊት ይበራል" እንዳለው ልባችሁ ምን ያህል እንደተደሰተ ተገነዘብሁኝ፡፡ [ምሳ.፲፭፥፲፫] በመሆኑም ዛሬ ማለዳ የተነሳሁት ከወትሮ በተለየ ትጋት ነው፡፡ ይኸውም ይህን መንፈሳዊ ደስታ ከእናንተ ጋር እንድካፈልና ቀጣዩ ወራት ቁስለ ነፍሳችሁ ድኅነት የሚያገኝበት ወርሐ ጾም መኾኑን አበስራችሁ ዘንድ ነው፡፡ የሁላችንም ጌታ ልዑል እግዚአብሔር ልክ እንደ ደግ አባት ባለፉት ወራት ለሠራነው ኃጢአት ሥርየት እናገኝበት ዘንድ ሽቶ መድኃኒት የሚሆን ቅዱስ ጾምን አዘጋጅቶልናል፡፡
ስለዚህ የነፍሳችን ጠባቂ እግዚአብሔር የሕመማችንን ፈውስ የምናገኝበትን መድኃኒት ስላዘጋጀልን እያመሰገንን ወርሐ ጾሙን ደስ ብሎን ልንቀበለው ይገባናል፡፡ ከእኛ መካከል ጾም በመግባቱ አንድስ እንኳን የሚከፋው ወይም የሚበሳጭ ሊኖር አይገባም፡፡ ወርሐ ጾሙን እንዲህ ደስ ተሰኝተን መቀበላችንን ዐይተውም አሕዛብ ይፈሩ ፤ አይሁድም ይራዱ፡፡ በእኛና በእነርሱ መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ዐይተው የማሩ፡፡
የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በዓል የምትሠራው ምእመናን ራሳቸውን መግዛት እንዲችሉ ፣ በበጎ ምግባር ያጌጡ ያሸበረቁ እንዲሆኑ እንደሆነ እነርሱ ግን በዓላትን የሚያደርጉት በዘፈንና በስካር ይህንም በመሰለ በሌላ ጸያፍ ግብር ለመንከባለል እንደኾነ ለይተው ይወቁ፡፡ በእርግጥም በዓል ተከበረ የሚባለው ፦ ሰዎች ነፍሳቸውን ካዳኑበት ፣ ውስጣዊ ሰላምንና ፍቅረ ቢጽን [ወንድምን መውደድ] ገንዘብ ካደረጉበት ፣ ዕለት ዕለት ከሚያጋጥማቸው የነፍስ መታወክ ካረፉበት ፣ ያለ ሁካታና ጋጋታ እንዲሁም እንስሳትን በማረድ ከልክ በላይ ከኾነ መብልና መጠጥ ርቀው ያከበሩት እንደሆነ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በዓል ተከበረ የሚባለው ፦ አርምሞንና ጸጥታን ፣ ፍቅርንና ደስታን ፣ ሰላምንና ራስን መግዛትን ፣ እንዲሁም ሌሎች እዚህ መዘርዘር የማንችላቸውን ብዙ ምግባር ትሩፋቶችን ገንዘብ ያደረግንበት እንደ ኾነ ነው፡፡ ❞
[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
❤2
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
[ የካቲት ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያደገ : የአረጋዊው ቅ/ዮሴፍ የመጨረሻ ልጅ : በንጽሕናውና ድንግልናው የተመሠከረለት : ከጸሎትና ገድል ብዛት እግሩ ያበጠ : የመጀመሪያው የኢየሩሳሌም ኤዺስ ቆዾስ ሲሆን ቁጥሩም ከ፸፪ [72] ቱ አርድዕት ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ይህ ቅዱስ ሐዋርያ በአባቶቻችን ሐዋርያት መካከል ትልቅ ሞገስ የነበረውና የጌታችን ወንድም ተብሎ የተጠራ ነው:: ቅዱስ ያዕቆብ ወላጅ አባቱ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ [የእመቤታችን ጠባቂ] ሲሆን በልጅነቱ ጥላው የሞተችው እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች:: በቤት ውስጥም ስምዖን: ዮሳና ይሁዳ የተባሉ ወንድሞችና ሰሎሜ የምትባል እህትም ነበረችው::
እናቱ ማርያም ከሞተች በሁዋላ ዕጉዋለ ማውታ [ደሃ አደግ] ሆኖ ነበር:: ነገር ግን በፈቃደ እግዚአብሔር አረጋዊ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከቤተ መቅደስ ሊጠብቃት [ሊያገለግላት)] ተቀብሎ ሲመጣ ያ ቤተሰብ ተቀየረ:: የበረከት: የምሕረትና የሰላም እመቤት የአምላክ እናቱ ገብታለችና ያ የሐዘን ቤት ደስታ ሞላው::
እመ ብርሃን ግን ገና ወደ ዮሴፍ ልጆች ስትደርስ አለቀሰች:: የአክስቷ ልጆች የሚንከባከባቸው አጥተው ቆሽሸው ነበር:: በተለይ ደግሞ ትንሹ ቅዱስ ያዕቆብ ያሳዝን ነበር:: እመ ብርሃን ማረፍ አልፈለገችም:: ወዲያው ማድጋ አንስታ ወደ ምንጭ ወርዳ ውሃ አምጥታ የሕጻኑን ገላ አጠበችው:: [በአምላክ እናት የታጠበ ሰውነት ምስጋና በጸጋ ይገባዋል!]
እመቤታችን ጌታ ከመወለዱ በፊት ለ፱ [9] ወራት: ከተወለደ በሁዋላ ደግሞ ለ፪ [2] ዓመታት ሕጻኑን ያዕቆብን ተንከባከበችው::
ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ግን ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን ይዛ ተሰዳለችና ተለያዩ:: ከስደት መልስ ግን ለ፳፭ [25] ዓመታት ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ጋር ሲያድግ ወላጅ እናቱ ትዝ ብላው አታውቅም:: አማናዊቷ እናት ከጐኑ ነበረችና::
ሊቃውንት እንደ ነገሩን እመቤታችን ለቅዱስ ያዕቆብ ያልሰጠችው ነገር ቢኖር ሐሊበ ድንግልናዌ [የድንግልና ወተትን] ብቻ ነው::
ስለዚህም :-
"እመ ያዕቆብ በጸጋ ማርያም ንግሥተ ኩሉ" ይላል መጽሐፍ:: [መልክዐ ስዕል]
ቅዱስ ያዕቆብ "የጌታ ወንድም" ተብሎ በተደጋጋሚ በሐዲስ ኪዳን ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ :-
፩. ለ፴ [30] ዓመታት ሳይነጣጠሉ አብረው በማደጋቸው፡፡
፪. የጌታችን የሥጋ አያቱ [የቅድስት ሐና] የእህት ልጅ በመሆኑ፡፡
፫. በዮሴፍ በኩልም የአንድ ቅድመ አያት ልጆች
በመሆናቸው፡፡
፬. ጌታችን ከትህትናው የተነሳ ደቀ መዛሙርቱን "ወንድሞች" ይላቸው ስለ ነበር ነው:: [ሥጋቸውን ተዋሕዶ ተገኝቷልና]
ራሱ ቅዱስ ያዕቆብ ግን "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ነኝ" ብሎ በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን ልዩነት ገልጧል:: [ያዕ.፩፥፩] (1:1) ቅዱስ ያዕቆብ ጌታችን ሲያስተምር ተከተለው::
¤ ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት ተቆጠረ
¤ ፫ [3] ዓመት ከ፫ [3] ወር ወንጌልን ተማረ
¤ ለመጀመሪያ ጊዜ ከድንግል ማርያምና ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ሆኖ "የጌታን ትንሳኤ ሳላይ እሕል አልቀምስም" ብሎ ማክፈልን አስተማረ
¤ መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ወንጌልን አስተማረ
¤ የኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ሊቀ ዻዻስ ሆኖ አገለገለ
¤ በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት የሐዋርያት
ሲኖዶሶችን በሊቀ መንበርነት መራ
¤ ሙታንን አስንስቶ: ድውያንን ፈውሶ: የመካኖችን ማሕጸን ከፍቶ: አጋንንትንም አስወጥቶ ብዙ ተእምራትን ሠራ:: እጅግ ብዙ አይሁዳውያንን ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሶ መልካሙን ገድል ተጋደለ::
በመጨረሻ ዘመኑ ያላመኑ የአይሁድ አለቆች ወደ ቤቱ ተሰብስበው "የናዝሬቱ ኢየሱስ ማነው የማንስ ልጅ ነው?" ሲሉ ጠየቁት:: እነርሱ ሰይጣን በሰለጠነበት ልቡናቸው "የዮሴፍ ልጅ ነው: የእኔም ወንድሜ ነው" እንዲላቸው ጠብቀው ነበር:: [ሎቱ ስብሐት ወአኮቴት!]
በልቡናቸው ያሰቡትን ተንኮል የተረዳው ሐዋርያ ወደ ቤቱ ጣራ ወጥቶ መናገር ጀመረ:: "ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ወልደ አብ ወልደ ማርያም: ሥግው ቃል: እግዚአብሔር ነው:: እኔም ፍጡሩና ባሪያው እንጂ እንደምታስቡት ወንድሙ አይደለሁም" አላቸው::
ንዴታቸውን መቆጣጠር ያልቻሉት አይሁድ ከላይ ወጥተው ወደ መሬት ወረወሩት:: በገድል የተቀጠቀጠ አካሉንም እየተፈራረቁ ደበደቡት:: አንዱ ግን ከእንጨት የተሠራ ትልቅ ገንዳ አምጥቶ የቅዱሱን ራስ ደጋግሞ መታው:: ጭንቅላቱም እንዳልነበር ሆነ:: ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ያዕቆብ ወደ ወደደው ክርስቶስ በዚህች ቀን ሔደ::
ቅዱሱ ሐዋርያ ያዕቆብ ቤቱን እንደ ቤተ መቅደስ አበው ሐዋርያት ይጠቀሙባት ነበር:: በመላ ዘመኑ የሚያገድፍ ነገር [ጥሉላት] ቀምሶ: ጸጉሩን ተላጭቶ: ገላውን ታጥቦና ልብሱን ቀይሮ አያውቅም::
"ወዝንቱ ጻድቅ እኅወ እግዚእነ::
ኢያብአ ውስተ አፉሁ ሥጋ ወወይነ::
ወኢገብረ ሎቱ ክልኤተ ክዳነ::" እንዲል::
ከጾም: ከጸሎትና ከመቆሙ ብዛትም እግሩ አብጦ አላራምድህ ብሎት ነበር:: ስለዚህም አበው "ጻድቁ [ገዳማዊው] ሐዋርያ" ይሉታል:: ቅዱሱ ሐዋርያ "የያዕቆብ መልዕክት" የሚለውን ባለ፭ [5] ምዕራፍ መልዕክት ጽፏል::
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን::
🕊
[ † የካቲት ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [የቅዱስ ዮሴፍ ልጅ : ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት አንዱ]
፪. ቅዱስ አባ መላልዮስ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት [በአንጾኪያ ሊቀ ዽዽስና ተሹሞ በአርዮሳውያን ብዙ ግፍ የደረሰበትና በስደት ያረፈ አባት ነው]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
፪. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት
፫. አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
፬. ማር ያዕቆብ ግብፃዊ
" የእግዚአብሔርና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ: ለተበተኑ ለአሥራ ሁለቱ ወገኖች:: ሰላም ለእናንተ ይሁን:: ወንድሞቼ ሆይ! የእምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት:: ትዕግስትም ምንም የሚጐድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም::" [ያዕ.፩፥፩]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
[ የካቲት ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ † 🕊
ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያደገ : የአረጋዊው ቅ/ዮሴፍ የመጨረሻ ልጅ : በንጽሕናውና ድንግልናው የተመሠከረለት : ከጸሎትና ገድል ብዛት እግሩ ያበጠ : የመጀመሪያው የኢየሩሳሌም ኤዺስ ቆዾስ ሲሆን ቁጥሩም ከ፸፪ [72] ቱ አርድዕት ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ይህ ቅዱስ ሐዋርያ በአባቶቻችን ሐዋርያት መካከል ትልቅ ሞገስ የነበረውና የጌታችን ወንድም ተብሎ የተጠራ ነው:: ቅዱስ ያዕቆብ ወላጅ አባቱ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ [የእመቤታችን ጠባቂ] ሲሆን በልጅነቱ ጥላው የሞተችው እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች:: በቤት ውስጥም ስምዖን: ዮሳና ይሁዳ የተባሉ ወንድሞችና ሰሎሜ የምትባል እህትም ነበረችው::
እናቱ ማርያም ከሞተች በሁዋላ ዕጉዋለ ማውታ [ደሃ አደግ] ሆኖ ነበር:: ነገር ግን በፈቃደ እግዚአብሔር አረጋዊ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከቤተ መቅደስ ሊጠብቃት [ሊያገለግላት)] ተቀብሎ ሲመጣ ያ ቤተሰብ ተቀየረ:: የበረከት: የምሕረትና የሰላም እመቤት የአምላክ እናቱ ገብታለችና ያ የሐዘን ቤት ደስታ ሞላው::
እመ ብርሃን ግን ገና ወደ ዮሴፍ ልጆች ስትደርስ አለቀሰች:: የአክስቷ ልጆች የሚንከባከባቸው አጥተው ቆሽሸው ነበር:: በተለይ ደግሞ ትንሹ ቅዱስ ያዕቆብ ያሳዝን ነበር:: እመ ብርሃን ማረፍ አልፈለገችም:: ወዲያው ማድጋ አንስታ ወደ ምንጭ ወርዳ ውሃ አምጥታ የሕጻኑን ገላ አጠበችው:: [በአምላክ እናት የታጠበ ሰውነት ምስጋና በጸጋ ይገባዋል!]
እመቤታችን ጌታ ከመወለዱ በፊት ለ፱ [9] ወራት: ከተወለደ በሁዋላ ደግሞ ለ፪ [2] ዓመታት ሕጻኑን ያዕቆብን ተንከባከበችው::
ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ግን ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን ይዛ ተሰዳለችና ተለያዩ:: ከስደት መልስ ግን ለ፳፭ [25] ዓመታት ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ጋር ሲያድግ ወላጅ እናቱ ትዝ ብላው አታውቅም:: አማናዊቷ እናት ከጐኑ ነበረችና::
ሊቃውንት እንደ ነገሩን እመቤታችን ለቅዱስ ያዕቆብ ያልሰጠችው ነገር ቢኖር ሐሊበ ድንግልናዌ [የድንግልና ወተትን] ብቻ ነው::
ስለዚህም :-
"እመ ያዕቆብ በጸጋ ማርያም ንግሥተ ኩሉ" ይላል መጽሐፍ:: [መልክዐ ስዕል]
ቅዱስ ያዕቆብ "የጌታ ወንድም" ተብሎ በተደጋጋሚ በሐዲስ ኪዳን ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ :-
፩. ለ፴ [30] ዓመታት ሳይነጣጠሉ አብረው በማደጋቸው፡፡
፪. የጌታችን የሥጋ አያቱ [የቅድስት ሐና] የእህት ልጅ በመሆኑ፡፡
፫. በዮሴፍ በኩልም የአንድ ቅድመ አያት ልጆች
በመሆናቸው፡፡
፬. ጌታችን ከትህትናው የተነሳ ደቀ መዛሙርቱን "ወንድሞች" ይላቸው ስለ ነበር ነው:: [ሥጋቸውን ተዋሕዶ ተገኝቷልና]
ራሱ ቅዱስ ያዕቆብ ግን "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ነኝ" ብሎ በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን ልዩነት ገልጧል:: [ያዕ.፩፥፩] (1:1) ቅዱስ ያዕቆብ ጌታችን ሲያስተምር ተከተለው::
¤ ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት ተቆጠረ
¤ ፫ [3] ዓመት ከ፫ [3] ወር ወንጌልን ተማረ
¤ ለመጀመሪያ ጊዜ ከድንግል ማርያምና ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ሆኖ "የጌታን ትንሳኤ ሳላይ እሕል አልቀምስም" ብሎ ማክፈልን አስተማረ
¤ መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ወንጌልን አስተማረ
¤ የኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ሊቀ ዻዻስ ሆኖ አገለገለ
¤ በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት የሐዋርያት
ሲኖዶሶችን በሊቀ መንበርነት መራ
¤ ሙታንን አስንስቶ: ድውያንን ፈውሶ: የመካኖችን ማሕጸን ከፍቶ: አጋንንትንም አስወጥቶ ብዙ ተእምራትን ሠራ:: እጅግ ብዙ አይሁዳውያንን ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሶ መልካሙን ገድል ተጋደለ::
በመጨረሻ ዘመኑ ያላመኑ የአይሁድ አለቆች ወደ ቤቱ ተሰብስበው "የናዝሬቱ ኢየሱስ ማነው የማንስ ልጅ ነው?" ሲሉ ጠየቁት:: እነርሱ ሰይጣን በሰለጠነበት ልቡናቸው "የዮሴፍ ልጅ ነው: የእኔም ወንድሜ ነው" እንዲላቸው ጠብቀው ነበር:: [ሎቱ ስብሐት ወአኮቴት!]
በልቡናቸው ያሰቡትን ተንኮል የተረዳው ሐዋርያ ወደ ቤቱ ጣራ ወጥቶ መናገር ጀመረ:: "ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ወልደ አብ ወልደ ማርያም: ሥግው ቃል: እግዚአብሔር ነው:: እኔም ፍጡሩና ባሪያው እንጂ እንደምታስቡት ወንድሙ አይደለሁም" አላቸው::
ንዴታቸውን መቆጣጠር ያልቻሉት አይሁድ ከላይ ወጥተው ወደ መሬት ወረወሩት:: በገድል የተቀጠቀጠ አካሉንም እየተፈራረቁ ደበደቡት:: አንዱ ግን ከእንጨት የተሠራ ትልቅ ገንዳ አምጥቶ የቅዱሱን ራስ ደጋግሞ መታው:: ጭንቅላቱም እንዳልነበር ሆነ:: ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ያዕቆብ ወደ ወደደው ክርስቶስ በዚህች ቀን ሔደ::
ቅዱሱ ሐዋርያ ያዕቆብ ቤቱን እንደ ቤተ መቅደስ አበው ሐዋርያት ይጠቀሙባት ነበር:: በመላ ዘመኑ የሚያገድፍ ነገር [ጥሉላት] ቀምሶ: ጸጉሩን ተላጭቶ: ገላውን ታጥቦና ልብሱን ቀይሮ አያውቅም::
"ወዝንቱ ጻድቅ እኅወ እግዚእነ::
ኢያብአ ውስተ አፉሁ ሥጋ ወወይነ::
ወኢገብረ ሎቱ ክልኤተ ክዳነ::" እንዲል::
ከጾም: ከጸሎትና ከመቆሙ ብዛትም እግሩ አብጦ አላራምድህ ብሎት ነበር:: ስለዚህም አበው "ጻድቁ [ገዳማዊው] ሐዋርያ" ይሉታል:: ቅዱሱ ሐዋርያ "የያዕቆብ መልዕክት" የሚለውን ባለ፭ [5] ምዕራፍ መልዕክት ጽፏል::
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን::
🕊
[ † የካቲት ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [የቅዱስ ዮሴፍ ልጅ : ከ፸፪ [72] ቱ አርድእት አንዱ]
፪. ቅዱስ አባ መላልዮስ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት [በአንጾኪያ ሊቀ ዽዽስና ተሹሞ በአርዮሳውያን ብዙ ግፍ የደረሰበትና በስደት ያረፈ አባት ነው]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
፪. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት
፫. አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
፬. ማር ያዕቆብ ግብፃዊ
" የእግዚአብሔርና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ: ለተበተኑ ለአሥራ ሁለቱ ወገኖች:: ሰላም ለእናንተ ይሁን:: ወንድሞቼ ሆይ! የእምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት:: ትዕግስትም ምንም የሚጐድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም::" [ያዕ.፩፥፩]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤1🙏1