Telegram Web
🥰124
🕊                        💖                       🕊

      [         የደብተራ ልጅ ነኝ  !          ]

🕊                        💖                       🕊

ደብተራ ማለት ፦

፩ ኛ. [  ደብተራ ብርሃን ማለት ነው ]

እግዚአብሔር በብርሃን ድንኳን ሊቀ ነቢያት ሙሴን በአምሳለ ንጉሥ ተገልጾ በብርሃን ድንኳን በሰባት የእሳት መጋረጃ ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረት በልቡናው ሥሎ ቃል በቃል ፭፻፸ [570] ጊዜ አነጋግሮታል። የደብተራ ልጅ ማለት የብርሃን ልጅ ማለት ነው። ወይም ሰማያዊ ወልደ ሰማያዊ ማለት ነው።


፪ ኛ. [   ደብተራ ኦሪት ናት   ]

ባስልኤል ፥ ኤልያብን ያህል ጠበብት ፣ ሙሴን ያህል ነቢይ ፣ አሮንን ያህል ካህን ፣ አስነሥቶ ያሳነጻት ናት። ታቦተ ሕጉ ያለባት ፣ አምልኮቱ የሚመሠከርባት ፣ ሕጉ የሚነገርባት ድንኳን ደብተራ ኦሪት ትባላለች። የደብተራ ልጅ ማለት የሕግ ልጅ የመቅደስ አገልጋይ ማለት ነው።ሕገ ኦሪትን ያወቀ እንደሙሴ እንደ አሮን  ያለ ማለት ነው።

፫ ኛ. [  ደብተራ ድንግል ማርያም ናት  ]

በአምሳላዊት ድንኳን በረድኤት ይገለጽ የነበረው እግዚአብሔር በንጽሕና በቅድስና በታነጸች በአማናዊት ደብተራ በእመቤታችን ማህጸን በኲነት ተገልጿልና ደብተራ ትባላለች።  የደብተራ ልጅ ማለትም የድንግል ማርያም የቃል ኪዳን ልጅ ማለት ነው። እንደ ጴጥሮስ እንደ ጳውሎስ መሆን ነዋ!

፬ኛ. ደብተራ መስቀል መድኅነ ዓለም ክርስቶስ የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል መሠዊያ ነውና ደብተራ ተብሏል ሕያው ደመ መለኮት የነጠበበት ቅዱስ መስቀል የከበረ ደብተራ ነው። የደብተራ ልጅ ማለትም የመስቀል ልጅ ማለት ነው። ወይም መስቀለኛ መስቀላዊ ማለት ነው።

፭ኛ. ደብተራ ርዕሱ ድንኳን ይባላል። በዘር በሩካቤ ያይደለ እንበለ ዘር እንበለ ሩካቤ የተወለደ የመድኅን አካሉ ደብተራ ተብሏል። ሠዋዒ፣ ተሠዋዒ፣ ተወካፌ መሥዋዕት፣ ነውና እንደ ብሉይ ሊቀ ካህናት ከአፍአ ወደ ውስጥ ደመ በግዕን ይዞ ለሥርኤት ወደ ደብተራ ኦሪት አልገባም። ራሱን በደብተራ ርዕሱ አቀረበ እንጂ። የደብተራ ልጅ ማለትም የክርስቶስ ልጅ ማለት ነው። በክርስቶስ የሚያምን የክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው።

፮ ኛ. [  ደብተራ ቤተ ክርስቲያን   ]

ክርስቲያኖች የሚሰበሰቡባት መቅደሰ ወንጌል ደብተራ ተብላለች አገልጋዮቿም ካህናተ ደብተራ ይባላሉ። የደብተራ ልጅ ማለትም የመቅደስ አገልጋይ ቅዳሴውን የሚቀድስ፣ ቅኔውን የሚቀኝ፣ ድጓውን የሚያዜም፣ ዝማሜውን የሚዘም  ብራናውን የራመመ ቀለሙን የቀመመ ማለት ነው። የረቀቀ የተራቀቀ ምጡቅ መርጌታ ማለትኮ ነው !

ከደብተራ ሙያ አንዱን ሳያውቁ መንቀፍ ወፍ ነዳሽ፣ ጉም አፋሽ መሆን ነው። ለደብተራነት ማዕር መድረስ ጭንቅ ነው እንጂ ልጅ መሆንስ ቢሹትም አይገኝ።

ደብተራ እያሉ መተንኮስ በይፋ ክርስትናን እና ክርስቲያኖችን በመጥላት የሚደረግ ስሑት ድንቁርና ነው። ጠንቋይን ለተከበረው ደብተራ መስጠት አይቻልም ጨለማ ከብርሃን ጋር ኅብረት የለውምና። ሀገር በቀል የዕውቀት ሐሳቦችን የደብተራ ዕውቀት ነው አንቀበልም አንሰማም ማለት ግን ኦርጂናል የጣሊያን አእምሮ ነው።

ደብተራ ዶክተሮች ሳይኖሩ ዶክተር ነበር። በተውሶ ጭፍን ግልበጣ የተሠራ አእምሮ እውነትን ካልጠላት የተማረ አይመስለውም ማለት ነው? ከውሸተኛ ተንኮለኛ ቁም ነገር አገኛለሁ ከማለት ዑቅያኖስ ሜዳ ሁኖ እህል ይዘራበታል ማለት ይቀላል። ወይም ሰሜን ተራራ ደልዳላ ሜዳ ይሆናል ማለት ይሻላል።

© ተጻፈ ከደብተራ ልጅ ገብረ መድኅን እንየው


[ ደብተራ በሚለው ስም ሰይጣናዊ የሆነ ሥራን የሚሠሩ ግለሰቦች የቤተክርስትያንና የምዕመናን ጠላቶች እንጂ ቤተክርስቲያንን መወከል የሚችሉ አይደሉም። ]



🕊                        💖                       🕊
4🔥1
                        †                          

እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🕊  †  መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ  †  🕊

🕊                        💖                     🕊

" በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። "

[ ሉቃ.፩፥፲፬ ]


† የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ ቅዱስ ዮሐንስ :-

- በብሥራተ መልዐክ የተጸነሰ
- በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
- በበርሃ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
- እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
- የጌታችንን መንገድ የጠረገ
- ጌታውን ያጠመቀና
- ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን :-

ነቢይ :
ሐዋርያ :
ሰማዕት :
ጻድቅ :
ገዳማዊ :
መጥምቀ መለኮት :
ጸያሔ ፍኖት :
ቃለ ዐዋዲ . . . ብላ ታከብረዋለች::


"ሰባኬ ወንጌል በጥዑም ልሣኑ ፣
ርስነ መለኰት ገሠሠት የማኑ ፣
ጸጉረ ገመል ተከድነ ዘባኑ ፣
ለዮሐንስ ሂሩቶ ንዜኑ ንዜኑ" ድጓ ዘዮሐንስ።

ትርጉም ፦

{ በጣፋጭ አንደበቱ ወንጌልን የሚሰብክ ፣
ቀኙ የሚያቃጥል መለኮትን የዳሰሰች ፣
ጀርባው በግመል ጸጉር የተሸፈነ ፣
የዮሐንስን ደግነት ፈጽመን እንናገራለን }


" እውነት እላችኋለሁ ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፡፡" [ ማቴ.፲፩፥፲፩ ]


እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ስለወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።


🕊                        💖                     🕊
2🙏2
🙏5
🕊                    💖                   🕊

[  ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ  !  ]

                        🕊                       

❝ ሰላም ለዮሐንስ ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ  ወስቡሕ ላእከ ወነቢይ ወሰማዕት ድንግል ካህን ጸያሒ ወሰባኪ መጥምቀ እግዚኡ ❞

[ ጌታውን ያጠመቀና ሰባኪ ፤ መንገድ ጠራጊ ፤ ካህን ድንግል ሰማዕት ፣ ነቢይና አገልጋይ ፤ ምስጉን ቅዱስና ንጹሕ ፤ ተገፍቶ የተገደለ ለኾነ ዮሐንስ ሰላምታ ይገባል። ]

[ አቤቱ ስላጠመቀኽ ስለ ዮሐንስ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ ከታናሽነቴ ዠምሮ እስከ ዛሬ አንተን የበደልኹኽን ኅጢአቴን ስለ ርሱ ብለኽ እኔን አገልጋይኽን አንጻኝ አሜን። ]

[ ተአምኆ ቅዱሳን ]

🕊

❝ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። ❞

[ ሉቃ.፩፥፲፬ ]


[ 🕊 እንኳን አደረሳችሁ 🕊 ]


🕊                        💖                       🕊
🙏31
1
🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

[ † እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]

🕊 ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 🕊   

ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: [ሉቃ.፩፥፮]

የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ [አድናቆት] ይገባል !
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ ፺ [90] የዘካርያስ ፻ [100] ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት [ኢሳ.፵፥፫] (40:3) , [ሚል.፫፥፩] (3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም ፳፮ [26] ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ፮ [6] ወራት ራሷን ሠወረች:: በ፮ [6] ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ በዚህች ቀን [ሰኔ ፴] (30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

+ የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
+ በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
+ በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
+ እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
+ የጌታችንን መንገድ የጠረገ
+ ጌታውን ያጠመቀና
+ ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::

ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::

†  🕊  አባ ጌራን ሕንዳዊ  🕊  †

ዳግመኛ በዚህች ቀን ሕንድ ካፈራቻቸው ታላላቅ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት ጻድቁ አባ ጌራን ይታሰባሉ:: የእኒህ ቅዱስ ታሪክ አሳዛኝ ነው:: ቅዱሱ በሕንድ ተወልደው: በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አድገው: ገና በወጣትነታቸው መንነው: ደሴት ውስጥ ወደሚገኝ አንድ በርሃ ገብተዋል:: ከገድላቸው ጽናት: ከቅድስናቸውም ብዛት የተነሳ በሃገረ ሕንድ ሰይጣን እንዳይገባ: ጠብ ክርክር እንዲጠፋ: ሰው ሁሉ በፍቅርና በሰላም እንዲኖር ማድረግ ችለው በጣም ተወዳጅ ነበሩ::

በዚህ የተበሳጨ ሰይጣን ግን ባልጠረጠሩት መንገድ መጣባቸው:: አንዲት ሴት ወደ እርሳቸው መጥታ [የንጉሡ ልጅ ነኝ በሚል] አስጠግተዋት ነበር:: አንድ ሌሊት ላይ ግን አውሬ ያባረራት በመምሰል ሩጣ ወደ ቤታቸው ገብታ አቀፈቻቸው:: በዚያ ቅጽበት ፍጡር ደካማ ነውና ታላቁ አባ ጌራን ተሰነካከሉ:: ከአፍታ በሁዋላ የሆነውን ሲያውቁ ደም አለቀሱ::

ልብሳቸውን ቀደው: እንባቸው እንደ ዥረት እየፈሰሰ አለቀሱ:: ራሳቸውን በትልቅ ድንጋይ እየቀጠቀጡት የጭንቅላታቸውና የደረታቸው አጥንቶች ተሰባበሩ:: እርሱ እግዚአብሔር መሐሪ ነውና ይቅር ብሎ: የቅድስና ስም ሰጥቶ በዚሕች ቀን ወደ ገነት አሳርጉዋቸዋል:: ለዚህ ነው መጽሐፉ "ጻድቅ ፯ [7] ጊዜ ይወድቃልና: ይነሣማል" ያለው:: [ምሳ.፳፬፥፲፮] (24:16)

አምላካችን ከቅዱሱ ቤተሰብና ከጻድቁ አባ ጌራን በረከት ይክፈለን::

🕊

[ † ሰኔ ፴  [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት [ልደቱ]
፪. ቅዱሳን ዘካርያስና ኤልሳቤጥ [ወላጆቹ]
፫. አባ ጌራን መስተጋድል [ሕንዳዊ]
፬. ቅዱሳት ደናግል ማርያና ማርታ [ከ፴፮ (36) ቱ ቅዱሳት አንስት-የአልዓዛር እህቶች]

[ †  ወርኀዊ በዓላት ]

፩. ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ [ሐዋርያ]
፪. አባ ሣሉሲ ክቡር
፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
፬. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት

" ደግሞም አንተ ሕጻን ሆይ የልዑል ነቢይ ትባላለህ:: መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና:: እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ:: ይሕም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው::" [ሉቃ.፩፥፸፮]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
🙏3
2025/07/09 05:49:30
Back to Top
HTML Embed Code: