🕊
[ † እንኳን ለቅዱሳን ቅዱስ ኄኖክ : ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ : ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ ኄኖክ † 🕊
† ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ቅዱስ ኄኖክ ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው:: አዳም: ሴት: ሔኖስ: ቃይናን: መላልኤል: ያሬድ ብለን ሰባተኛው ኄኖክ ነውና::
ቅዱሱ የማቱሳላ አባትም ነው:: አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረጉም ሞትን ያላየ: ብሔረ ሕያዋን የገባ የመጀመሪያው ሰው ሁኗል:: ለአዳም ልጆችም ተስፋ ድኅነት እንዳለ ማሳያ ሁኗል:: "በአቤል አፍርሆሙ: ወበኄኖክ አንቅሆሙ" እንዳለ ሊቁ::
ቅዱስ ኄኖክ በ፲፬፻፹፮ [1486] ዓ/ዓ የመጀመሪያውን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል [መጽሐፈ ኄኖክን] ከመጻፉ ባሻገር በብዙ ሥፍራ በክብር ተጠቅሶ ይገኛል::
🕊 † ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ † 🕊
† ይህ ቅዱስ ሐዋርያ አንድ የቤተ ክርስቲያናችን መብራት ነው:: ወደ ክርስትና የመጣው በ40ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ሲሆን አሳምኖ ለቅድስና ያበቃው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ነው::
በጊዜውም በነበረው ትጋትና ተጋድሎ ፍሬ አፍርቷል:: ሆዱንም እጅግ ያመው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ሲጠራው "የምወድህ ልጄ" እያለ ነበር:: በኤፌሶንም ጵጵስናን ሹሞ ፪ መልዕክታትን ልኮለታል:: ቅዱስ ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያንን ለብዙ ዘመናት አገልግሎ በሰማዕትነት ዐርፏል::
ዛሬ ሥጋው ከኤፌሶን ወደ ቁስጥንጥንያ የፈለሰበት ነው፡፡ ጊዜውም ፫፻፴ [330] ዎቹ መጀመሪያ ላይ እንደሆነ ይታመናል፡፡
"መድኃኒታችን እግዚአብሔር: ተስፋችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳዘዘው ትእዛዝ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ: በእምነት እውነተኛ ልጄ ለሆነ ለጢሞቴዎስ:: ከእግዚአብሔር ከአባታችን: ከክርስቶስ ኢየሱስም ከጌታችን: ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን . . ." [፩ጢሞ. ፩፥፩]
🕊 † ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት † 🕊
† ከታላላቅ ሊቃናት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሱርያል ክብሩ ብዙ ቢሆንም ብዙ ምዕመናን አያውቁትም:: የመላእክት መዓርግ ሲነገር ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤል ብሎ ቀጥሎ የሚመጣው ሱርያል ነው::
በሦስቱ ሰማያት ካሉት ዘጠኙ ዓለመ መላእክት የአንዱ [የሥልጣናት] መሪ [አለቃ] ነው:: መልአኩ እጅግ ርሕሩሕ እና ተራዳኢ ነውና አንዘንጋው:: ለኖኅ መርከብን ያሳራው: ከጥፋት ውኃም ያዳነው ይህ ቅዱስ መልአክ ነው::
በገድለ ሰማዕታትም ላይ እንደተጠቀሰው የሰማዕታት ረዳትና አዳኝም ነው:: ቅዱስ ሱርያል በሌላ ስሙ "እሥራልዩ" ይባላል:: "የእሥራኤል ረዳት" እንደ ማለት:: ዛሬ ደግሞ የሊቀ መልአኩ ቅዳሴ ቤቱ ነው::
† የይቅርታ ጌታ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ አይተወን . . . አይጣለን !
[ † ጥር ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ [ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት]
፪. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ [ፍልሠቱ]
፫. ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
፭. ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት [ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
፪. አቡነ መባዐ ጽዮን
፫. አባ መቃርስ ርዕሰ መነኮሳት
፬. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት [ንጉሠ ኢትዮጵያ]
፭. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
፮. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
† " የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ:: " † [፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለቅዱሳን ቅዱስ ኄኖክ : ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ : ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ ኄኖክ † 🕊
† ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ቅዱስ ኄኖክ ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው:: አዳም: ሴት: ሔኖስ: ቃይናን: መላልኤል: ያሬድ ብለን ሰባተኛው ኄኖክ ነውና::
ቅዱሱ የማቱሳላ አባትም ነው:: አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረጉም ሞትን ያላየ: ብሔረ ሕያዋን የገባ የመጀመሪያው ሰው ሁኗል:: ለአዳም ልጆችም ተስፋ ድኅነት እንዳለ ማሳያ ሁኗል:: "በአቤል አፍርሆሙ: ወበኄኖክ አንቅሆሙ" እንዳለ ሊቁ::
ቅዱስ ኄኖክ በ፲፬፻፹፮ [1486] ዓ/ዓ የመጀመሪያውን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል [መጽሐፈ ኄኖክን] ከመጻፉ ባሻገር በብዙ ሥፍራ በክብር ተጠቅሶ ይገኛል::
🕊 † ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ † 🕊
† ይህ ቅዱስ ሐዋርያ አንድ የቤተ ክርስቲያናችን መብራት ነው:: ወደ ክርስትና የመጣው በ40ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ሲሆን አሳምኖ ለቅድስና ያበቃው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ነው::
በጊዜውም በነበረው ትጋትና ተጋድሎ ፍሬ አፍርቷል:: ሆዱንም እጅግ ያመው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ሲጠራው "የምወድህ ልጄ" እያለ ነበር:: በኤፌሶንም ጵጵስናን ሹሞ ፪ መልዕክታትን ልኮለታል:: ቅዱስ ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያንን ለብዙ ዘመናት አገልግሎ በሰማዕትነት ዐርፏል::
ዛሬ ሥጋው ከኤፌሶን ወደ ቁስጥንጥንያ የፈለሰበት ነው፡፡ ጊዜውም ፫፻፴ [330] ዎቹ መጀመሪያ ላይ እንደሆነ ይታመናል፡፡
"መድኃኒታችን እግዚአብሔር: ተስፋችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳዘዘው ትእዛዝ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ: በእምነት እውነተኛ ልጄ ለሆነ ለጢሞቴዎስ:: ከእግዚአብሔር ከአባታችን: ከክርስቶስ ኢየሱስም ከጌታችን: ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን . . ." [፩ጢሞ. ፩፥፩]
🕊 † ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት † 🕊
† ከታላላቅ ሊቃናት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሱርያል ክብሩ ብዙ ቢሆንም ብዙ ምዕመናን አያውቁትም:: የመላእክት መዓርግ ሲነገር ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤል ብሎ ቀጥሎ የሚመጣው ሱርያል ነው::
በሦስቱ ሰማያት ካሉት ዘጠኙ ዓለመ መላእክት የአንዱ [የሥልጣናት] መሪ [አለቃ] ነው:: መልአኩ እጅግ ርሕሩሕ እና ተራዳኢ ነውና አንዘንጋው:: ለኖኅ መርከብን ያሳራው: ከጥፋት ውኃም ያዳነው ይህ ቅዱስ መልአክ ነው::
በገድለ ሰማዕታትም ላይ እንደተጠቀሰው የሰማዕታት ረዳትና አዳኝም ነው:: ቅዱስ ሱርያል በሌላ ስሙ "እሥራልዩ" ይባላል:: "የእሥራኤል ረዳት" እንደ ማለት:: ዛሬ ደግሞ የሊቀ መልአኩ ቅዳሴ ቤቱ ነው::
† የይቅርታ ጌታ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ አይተወን . . . አይጣለን !
[ † ጥር ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ [ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት]
፪. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ [ፍልሠቱ]
፫. ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
፭. ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት [ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
፪. አቡነ መባዐ ጽዮን
፫. አባ መቃርስ ርዕሰ መነኮሳት
፬. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት [ንጉሠ ኢትዮጵያ]
፭. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
፮. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
† " የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ:: " † [፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
#ቹሩ_መድኃኔዓለም
#አቤቱ__ጌታዬ_ሆይ ወደ አንተ ስጣራ ስማኝ የልመናዬንም ቃል አድምጥ እንደ በደለው ልጅ #በመጸጸት አቤቱ በሰማይም በፊትህም በደልሁህ እላለሁ ሉቃ 15:18 በእውነት ሰውን የምትወድ አንተ በፊትህ ተቀበለኝ #ጸሎቴንም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ተቀበለኝ እንደ ቀራጩ ሰው በንስሀ ይቅር በለኝ ጌታዬ ብዬ ለመንኩህ እኔ #ኃጢአተኛ ነኝ ባንተ ዘንድ ግን ብዙ ይቅርታና ምህረት #አለ::
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#አቤቱ__ጌታዬ_ሆይ ወደ አንተ ስጣራ ስማኝ የልመናዬንም ቃል አድምጥ እንደ በደለው ልጅ #በመጸጸት አቤቱ በሰማይም በፊትህም በደልሁህ እላለሁ ሉቃ 15:18 በእውነት ሰውን የምትወድ አንተ በፊትህ ተቀበለኝ #ጸሎቴንም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ተቀበለኝ እንደ ቀራጩ ሰው በንስሀ ይቅር በለኝ ጌታዬ ብዬ ለመንኩህ እኔ #ኃጢአተኛ ነኝ ባንተ ዘንድ ግን ብዙ ይቅርታና ምህረት #አለ::
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
†
[ 🕊 ገ ድ ለ ቅ ዱ ሳ ን 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]
[ ክፍል ሰማንያ አንድ ]
🕊
[ አባ ወቅሪስን ስለ ትዕግሥትና ራስን ስለ መካድ አስተማረው ! ]
🕊
❝ ዳግመኛም አባ ወቅሪስ እንዲህ አለ ፦ “ በቀኑ ሙቀቱ በጣም ከፍተኛ በሆነበት ሰዓት [ቀትር] ላይ አባ መቃርዮስን ላየው ሄድሁ፡፡ በጥም እየተቃጠልሁ ነበርና ፦ 'አባቴ ሆይ ፣ በጣም ተጠምቻለሁ' አልሁት፡፡ እርሱም እንዲህ አለኝ፡- “በጥላው ዐረፍ ማለት ይብቃህ ፣ በዚህ ሰዓት ላይ በመንገድ እየተቃጠሉ ጥላ እንኳ ማግኘት የማይችሉ ብዙ ሰዎች አሉና፡፡”
ከእነዚህ ቃላት በኋላ ከእርሱ ጋር ስለ መልካም ምግባር ሕይወት ተነጋገርኩ፡፡ እርሱም እንዲህ አለኝ ፦ “ልጄ ሆይ ፣ በእውነት ሰውነቴን በዳቦና በውኃ ሳልሞላ ፣ ትንሽ ሽለብ እስኪያደርገኝ ድረስ ከግድግዳ ጠጋ ከምል በስተቀር ዕንቅልፍ ሳላጠግብ ሃያ ዓመት አሳልፌያለሁ፡፡ ❞
🕊
የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡
ይቆየን !
💖 🕊 💖
[ 🕊 ገ ድ ለ ቅ ዱ ሳ ን 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]
[ ክፍል ሰማንያ አንድ ]
🕊
[ አባ ወቅሪስን ስለ ትዕግሥትና ራስን ስለ መካድ አስተማረው ! ]
🕊
❝ ዳግመኛም አባ ወቅሪስ እንዲህ አለ ፦ “ በቀኑ ሙቀቱ በጣም ከፍተኛ በሆነበት ሰዓት [ቀትር] ላይ አባ መቃርዮስን ላየው ሄድሁ፡፡ በጥም እየተቃጠልሁ ነበርና ፦ 'አባቴ ሆይ ፣ በጣም ተጠምቻለሁ' አልሁት፡፡ እርሱም እንዲህ አለኝ፡- “በጥላው ዐረፍ ማለት ይብቃህ ፣ በዚህ ሰዓት ላይ በመንገድ እየተቃጠሉ ጥላ እንኳ ማግኘት የማይችሉ ብዙ ሰዎች አሉና፡፡”
ከእነዚህ ቃላት በኋላ ከእርሱ ጋር ስለ መልካም ምግባር ሕይወት ተነጋገርኩ፡፡ እርሱም እንዲህ አለኝ ፦ “ልጄ ሆይ ፣ በእውነት ሰውነቴን በዳቦና በውኃ ሳልሞላ ፣ ትንሽ ሽለብ እስኪያደርገኝ ድረስ ከግድግዳ ጠጋ ከምል በስተቀር ዕንቅልፍ ሳላጠግብ ሃያ ዓመት አሳልፌያለሁ፡፡ ❞
🕊
የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡
ይቆየን !
💖 🕊 💖
†
[ 🕊 ፍኖተ ቅዱሳን 🕊 ]
[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትሕትና ! ]
------------------------------------------
❝ በአፉ ዐረፋ እስኪያስደፍቀው ድረስ ርኩስ መንፈስ ያደረበት አንድ ሰው አንድን መነኵሴ ፊቱን በጥፊ መታው፡፡ መነኵሴውም ሌላኛውን ፊቱን አዙሮ ሰጠው:: በዚህ ጊዜ ጋኔኑ የመነኲሴው ትሕትናው ስላቃጠለው ወዲያውኑ ከሰውዬው ወጥቶ ጠፋ፡፡ ❞
-------------------------------------------
❝ አጋንንት ለምን ይህን ያህል አጽንተው ይዋጉናል?" ብለው አንድን አረጋዊ ጠየቁት፡፡ እርሱም ፦ "መሣሪያዎቻችንን አሽቀንጥረን ስለ ጣልናቸው ነው ፤ መሣሪያዎቻችን ማለቴም ክብርን መናቅን ፣ ትሕትናን ፣ ድህነትንና ጽናትን ማለቴ ነው" አላቸው፡፡ ❞
--------------------------------------------
🕊
የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡
† † †
💖 🕊 💖
[ 🕊 ፍኖተ ቅዱሳን 🕊 ]
[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትሕትና ! ]
------------------------------------------
❝ በአፉ ዐረፋ እስኪያስደፍቀው ድረስ ርኩስ መንፈስ ያደረበት አንድ ሰው አንድን መነኵሴ ፊቱን በጥፊ መታው፡፡ መነኵሴውም ሌላኛውን ፊቱን አዙሮ ሰጠው:: በዚህ ጊዜ ጋኔኑ የመነኲሴው ትሕትናው ስላቃጠለው ወዲያውኑ ከሰውዬው ወጥቶ ጠፋ፡፡ ❞
-------------------------------------------
❝ አጋንንት ለምን ይህን ያህል አጽንተው ይዋጉናል?" ብለው አንድን አረጋዊ ጠየቁት፡፡ እርሱም ፦ "መሣሪያዎቻችንን አሽቀንጥረን ስለ ጣልናቸው ነው ፤ መሣሪያዎቻችን ማለቴም ክብርን መናቅን ፣ ትሕትናን ፣ ድህነትንና ጽናትን ማለቴ ነው" አላቸው፡፡ ❞
--------------------------------------------
🕊
የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡
† † †
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለጌታችን አማኑኤል ክርስቶስ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ 🕊 † ተአምረ እግዚእ † 🕊 ]
† " ተአምር " የሚለውን ቃል በቁሙ "ምልክት" ብሎ መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ [በላይ] : ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ [ሲፈጸም] ተአምር ይባላል::
ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው:: ስለዚህም ነው "ኤልሻዳይ - ከሐሌ ኩሉ - ሁሉን ቻይ" እያልን የምንጠራው::
እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ [ኦሪትን ተመልከት] እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ [፩ ነገሥት] እንደ ነበር ይታወቃል::
እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: [ ማቴ.፲፥፰ , ፲፯፥፳ , ማር.፲፮፥፲፯, ሉቃ. ፲፥፲፯, ዮሐ.፲፬፥፲፪ ]
እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: [ሐዋ. ፫፥፮ , ፭፥፩ , ፭፥፲፪ , ፰፥፮ , ፱፥፴፫-፵፫ , ፲፬፥፰ , ፲፱፥፲፩]
[ 🕊 † ተአምራተ እግዚእ † 🕊 ]
† ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ብዙ ተአምራትን ሰርቷል:: እያንዳንዱ ግን ቢጻፍ ዓለም ለራሷ ባልበቃች ነበር:: ከእነዚህ መካከልም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው በዚህ ዕለት በ፯ እንጀራ እና በጥቂት ዓሣ ሴቶችና ሕፃናትን ሳይጨምር ፬ ሺህ ሰዎችን በቸርነቱ አበርክቶ አጥግቡዋል:: ደቀ መዛሙርቱም ፯ ቅርጫት ማዕድ አንስተዋል::
ጌታችን በከሃሊነቱ የተራቡትን ሲያጠግብ እንዲሁ አይደለም:: በጊዜው የነበሩ አይሁድ ጠማሞች ነበሩና እነሱን ምላሽ በሚያሳጣ መንገድ ነበር እንጂ:: አይሁድ ላለማመን ብዙ ጥረት ነበራቸውና::
በዚህ ዕለትም እንጀራውን አበርክቶ ሲያበላቸው :-
፩. ጊዜው አመሻሽ ላይ ነበር:: ምክንያት :- ጧት ላይ ቢሆን ከቤታችን የበላነው ሳይጐድል ብለው ከማመን ይርቁ ነበርና::
፪. ከውሃ ዳር አድርጐታል:: መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::
፫. ሳር የበዛበት ቦታ ላይ አድርጐታል:: ምክንያቱም መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::
፬. ከከተማ አርቆ ምድረ በዳ ላይ አድርጐታል:: ያማ ባይሆን "ፈጣን: ፈጣን ደቀ መዛሙርቱ ተሯሩጠው እየገዙ አቀረቡለት" ባሉ ነበርና::
† ለመድኃኒታችን ክርስቶስ አምልኮና ምስጋና ይሁን !
አማኑኤል አምላካችን ጣዕመ ፍቅሩን ያሳድርብን::
🕊
[ † ጥር ፳፰ [ 28 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሰማዕት [ስለ ሃይማኖት ፯ ጊዜ ሙቶ የተነሳ , ፯ አክሊል የወረደለት ]
፪. ቅዱስ አካውህ መነኮስ
፫. ፰ መቶ "800" ሰማዕታት
፬. ቅዱስ ዮሴፍ አይሁዳዊ [የእመቤታችን ወዳጅ]
፮. ቅድስት ሳቤላ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. አባቶቻችን አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ
፪. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ
፫. ቅዱስ እንድራኒቆስና አትናስያ
፬. ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ
† " ጌታ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ :- ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስከ አሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለ ሌላቸው አዝንላቸዋለሁ:: በመንገድም እንዳይዝሉ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም' አላቸው::
ደቀ መዛሙርቱም :- 'ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ ይህን ያህል እንጀራ በምድረ በዳ ከወዴት እናገኛለን?' አሉት:: ጌታ ኢየሱስም:- 'ስንት እንጀራ አላችሁ?' አላቸው:: እነርሱም:- 'ሰባት: ጥቂትም ትንሽ ዓሣ' አሉት::
ሕዝቡም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ:: ሰባቱንም እንጀራ: ዓሣውንም ይዞ አመሰገነ:: ቆርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ:: ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ:: ሁሉም በሉና ጠገቡ:: የተረፈውንም ቁርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሱ:: የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ::" † [ ማቴ.፲፭፥፴፪ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለጌታችን አማኑኤል ክርስቶስ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ 🕊 † ተአምረ እግዚእ † 🕊 ]
† " ተአምር " የሚለውን ቃል በቁሙ "ምልክት" ብሎ መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ [በላይ] : ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ [ሲፈጸም] ተአምር ይባላል::
ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው:: ስለዚህም ነው "ኤልሻዳይ - ከሐሌ ኩሉ - ሁሉን ቻይ" እያልን የምንጠራው::
እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ [ኦሪትን ተመልከት] እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ [፩ ነገሥት] እንደ ነበር ይታወቃል::
እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: [ ማቴ.፲፥፰ , ፲፯፥፳ , ማር.፲፮፥፲፯, ሉቃ. ፲፥፲፯, ዮሐ.፲፬፥፲፪ ]
እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: [ሐዋ. ፫፥፮ , ፭፥፩ , ፭፥፲፪ , ፰፥፮ , ፱፥፴፫-፵፫ , ፲፬፥፰ , ፲፱፥፲፩]
[ 🕊 † ተአምራተ እግዚእ † 🕊 ]
† ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ብዙ ተአምራትን ሰርቷል:: እያንዳንዱ ግን ቢጻፍ ዓለም ለራሷ ባልበቃች ነበር:: ከእነዚህ መካከልም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው በዚህ ዕለት በ፯ እንጀራ እና በጥቂት ዓሣ ሴቶችና ሕፃናትን ሳይጨምር ፬ ሺህ ሰዎችን በቸርነቱ አበርክቶ አጥግቡዋል:: ደቀ መዛሙርቱም ፯ ቅርጫት ማዕድ አንስተዋል::
ጌታችን በከሃሊነቱ የተራቡትን ሲያጠግብ እንዲሁ አይደለም:: በጊዜው የነበሩ አይሁድ ጠማሞች ነበሩና እነሱን ምላሽ በሚያሳጣ መንገድ ነበር እንጂ:: አይሁድ ላለማመን ብዙ ጥረት ነበራቸውና::
በዚህ ዕለትም እንጀራውን አበርክቶ ሲያበላቸው :-
፩. ጊዜው አመሻሽ ላይ ነበር:: ምክንያት :- ጧት ላይ ቢሆን ከቤታችን የበላነው ሳይጐድል ብለው ከማመን ይርቁ ነበርና::
፪. ከውሃ ዳር አድርጐታል:: መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::
፫. ሳር የበዛበት ቦታ ላይ አድርጐታል:: ምክንያቱም መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::
፬. ከከተማ አርቆ ምድረ በዳ ላይ አድርጐታል:: ያማ ባይሆን "ፈጣን: ፈጣን ደቀ መዛሙርቱ ተሯሩጠው እየገዙ አቀረቡለት" ባሉ ነበርና::
† ለመድኃኒታችን ክርስቶስ አምልኮና ምስጋና ይሁን !
አማኑኤል አምላካችን ጣዕመ ፍቅሩን ያሳድርብን::
🕊
[ † ጥር ፳፰ [ 28 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሰማዕት [ስለ ሃይማኖት ፯ ጊዜ ሙቶ የተነሳ , ፯ አክሊል የወረደለት ]
፪. ቅዱስ አካውህ መነኮስ
፫. ፰ መቶ "800" ሰማዕታት
፬. ቅዱስ ዮሴፍ አይሁዳዊ [የእመቤታችን ወዳጅ]
፮. ቅድስት ሳቤላ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. አባቶቻችን አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ
፪. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ
፫. ቅዱስ እንድራኒቆስና አትናስያ
፬. ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ
† " ጌታ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ :- ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስከ አሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለ ሌላቸው አዝንላቸዋለሁ:: በመንገድም እንዳይዝሉ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም' አላቸው::
ደቀ መዛሙርቱም :- 'ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ ይህን ያህል እንጀራ በምድረ በዳ ከወዴት እናገኛለን?' አሉት:: ጌታ ኢየሱስም:- 'ስንት እንጀራ አላችሁ?' አላቸው:: እነርሱም:- 'ሰባት: ጥቂትም ትንሽ ዓሣ' አሉት::
ሕዝቡም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ:: ሰባቱንም እንጀራ: ዓሣውንም ይዞ አመሰገነ:: ቆርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ:: ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ:: ሁሉም በሉና ጠገቡ:: የተረፈውንም ቁርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሱ:: የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ::" † [ ማቴ.፲፭፥፴፪ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖