Telegram Web
                       †                            

†    🕊    ቅዱስ ቄርሎስ    🕊    †


❝ ቅዱስ ቄርሎስ መላ ዘመኑን ከጥፋት ተራሮች ጋር እየተዋጋ አሳለፈ።

ስለዚህም ምክንያት ቤተክርስቲያን ስላከበራት ፤ ከፍ ከፍ ስላደረጋት ፤ አንድነቷ እንዲጠበቅ ስላደረገላት " በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር እንዳይቻላት" የዚህን ታላቅ አባት ሥራ ዘወትር ታስታውሳለች። ❞

[ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ መግቢያ ]


🕊                        💖                     🕊
🙏2
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊


▷     "  ከሐጢዓት ስለመውጣት  " 

💖 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖  ]

[           🕊      🕊              ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬


❝ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።

ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም ፤ ❞

[  ዕብ . ፮ ፥ ፲፪ - ፫  ]



🕊                       💖                   🕊
🥰1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
                         †                         


❝ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።

የልቤ ችግር ብዙ ነው ፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ። ድካሜንና መከራዬን እይ ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ። ❞

[  መዝ . ፳፭ ፥ ፲፮   ]



         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
6🙏2
🕊

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

[ ✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን ፲፪ [ 12 ] ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]


🕊 ✞ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ✞ 🕊

ነቢይ ማለት ከእግዚብሔር ተመርጦ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን] : መጻዕያትን [ለወደፊቱ የሚደረገውን] የሚያውቁ ሰዎች ሲሆኑ ሕዝቡን እንዲመሩ: እንዲገስጹም ይላካሉ:: ሕይወታቸውም በቅድስና የተለበጠ ነው:: ነቢያትን በቁጥር መግለጽ ከባድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን እንድንረዳቸው እንዲህ ትከፍላቸዋለች::

=>  በኩረ ነቢያት አዳም
=>  ሊቀ ነቢያት ሙሴ
=>  ርዕሰ ነቢያት ኤልያስ
=>  ልበ አምላክ ዳዊት
=>  ፲፭ [15] ቱ ነቢያት [ከአዳም ጀምሮ እስከ ሳሙኤል]

=> ፬ [4] ቱ ዐበይት ነቢያት [ኢሳይያስ: ኤርምያስ: ሕዝቅኤልና ዳንኤል]

፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት ደግሞ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ናቸው:: በዚህች ቀን ታዲያ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት በአንድነት ይታሠባሉ:: እነዚህም :-

፩. ቅዱስ ሆሴዕ [ኦዝያ]
፪. ቅዱስ አሞጽ
፫. ቅዱስ ሚክያስ
፬. ቅዱስ ኢዩኤል
፭. ቅዱስ አብድዩ
፮. ቅዱስ ዮናስ
፯. ቅዱስ ናሆም
፰. ቅዱስ እንባቆም
፱. ቅዱስ ሶፎንያስ
፲. ቅዱስ ሐጌ
፲፩. ቅዱስ ዘካርያስ እና
፲፪. ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው::

ቅዱሳኑ ደቂቀ ነቢያት የተባሉት

፩. የነቢያት ልጆች በመሆናቸው
፪. የጻፏቸው ሐረገ ትንቢቶች በንጽጽር ከዐበይቱ [ከነኢሳይያስ] ስለሚያንስ ነው::

በምግባር: በትሩፋት: በአገልግሎት ግን ያው ናቸው:: ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እሊህን ነቢያት "እለ አውኀዙ ተነብዮ በእንተ ስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ይሏቸዋል:: [ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መውረድ: መወለድና የማዳን ሥራ የትንቢት ጐርፍን ያፈሰሱ እንደ ማለት ነው ::]

ቅዱሳኑ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ባሻገር ዓለማችን ላይ ከነበሩበት ዘመን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሊደረጉ ያላቸውን ነገሮችም ተናግረዋል:: የነበሩበት ዘመን በአማካኝ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፱ መቶ [900] እስከ ፭ [500] ነው:: በትንቢት ደረጃም እንደነ ሆሴዕና ዘካርያስ ፲፬ [14] ምዕራፎችን: እንደነ አብድዩም አንዲት ምዕራፍ ብቻም የጻፉ አሉ::

በሕይወታቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ያሻቸው ናቸውና በየጊዜው ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገሩ የእርሱን ድምጽ ለእሥራኤል [አንዳንዴም ለአሕዛብ] ያደርሱ ነበር:: ፊት አይተው የማያዳሉ ናቸውና ሕዝቡንም ሆነ ነገሥታቱን ስለ ኃጢአታቸው ይገሰጹ ነበር:: በዚህም ምክንያት ከነገሥታቱና ከሕዝቡ አለቆች መከራ ደርሶባቸዋል:: አልፎም ያለ አበሳቸው ሕዝቡ በኃጢአቱ ሲማረክ አብረውት ወርደዋል::

በመጨረሻ ሕይወታቸውም አንዳንዶቹን ክፉዎች ሲገድሏቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል:: ዛሬ ነቢያት ከእነርሱ ባሕርይ በተገኘችና ብዙ ትንቢትን በተናገሩላት በእመቤታችን ምክንያት ክርስቶስ ድኅነትን ፈጽሞላቸው በተድላ ገነት ይኖራሉ:: ስለ እኛም ይማልዳሉ::

" ናጥሪ እንከ ትሕትና ዘምስለ ንጽሕና"

[ እንግዲህ እንደ ነቢያት ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናድርግ ]

"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ"

[ ነቢያት መንፈስን ንጹሕ በማድረግ እግዚአብሔርን አይተውታልና: ፊት ለፊትም ተያይተዋልና ]

/ቅዳሴ ማርያም/

ከአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት በረከት ይክፈለን::

🕊

[ † ሐምሌ ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. "12ቱ" ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት
፪. ቅዱስ ሶፎንያስ ነቢይ [ዕረፍቱ]
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አቡቂርና ዮሐንስ [ቅዳሴ ቤታቸው]

[ †  ወርኀዊ በዓላት ]

፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጉዋድ [ወንጌላዊው]
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት]

" ለእናንተም ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉ መረመሩት:: በእነርሱም የነበረ የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራ ከእርሱም በሁዋላ ስለሚመጣው ክብር አስቀድሞ እየመሠከረ በምን ወይም እንዴት ባለ ዘመን እንዳመለከተ ይመረምሩ ነበር:: " [፩ዼጥ.፩፥፲]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
1👍1🙏1
8
#ወዳጆቼ

#ይህ_ብርድ አንድ ታላቅ ውለታ አያስታውስህም
ብርድ ሲበርድህ የብርድ መከላከያ ነገር ትፈልጋለህ (ብርድ ልብስ)
#ለስጋህ እንዲህ አደረክ
#ነፍስህ ስትበረድስ ምን ታለብሳት?
አዳምና ሔዋን
#በኀጢአት ብርድ በወደቁ ጊዜ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ #የኀጢአት_ብርድን አስወገደላቸው።
ታዲያ ወዳጄ በነፍስ ተበርደህ ከሆነ መፍትሄው
#ክርስቶስን መልበስ ነው

"፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን
#ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም #ለሥጋ አታስቡ።

(ወደ ሮሜ ሰዎች 13: 14)

#መልካም__ቀን 🙏

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
      •➢ 👇  ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
12🙏5
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊


▷     "  የጥንካሬ ዓይነቶች  " 

💖 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖  ]

[           🕊                  🕊              ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬


❝ ከደስታም ጋር በሁሉ ለመጽናትና ለመታገሥ እንደ ክብሩ ጉልበት መጠን በኃይል ሁሉ እየበረታችሁ ፥ በቅዱሳንም ርስት በብርሃን እንድንካፈል ያበቃንን አብን እያመሰገናችሁ ፥ በነገር ሁሉ ደስ ልታሰኙ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን። ❞

[  ቆላ . ፩ ፥ ፲፪   ]



🕊                       💖                   🕊
🥰2
                        †                           

🕊   💖  ዼጥሮስ ወዻውሎስ  💖   🕊

                         🕊                         

[  እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ   ]


❝ ስማቸው ጴጥሮስና እንድርያስ ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ፣ ፊልጶስና በርተሎሜዎስ ፣ ቶማስና ማቴዎስ ፣ ታዴዎስና ናትናኤል ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ማትያን በመባል ለሚጠሩ ለ ፲፪ ቱ የመድኅን ሐዋርያት ሰላምታ ይገባል። ❞

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

❝ አቤቱ በስምኽ የሰበኩ ፤ በታላቅ መከራ በረኀብና በጥም ፤ በብርድና በመራቆት ፤ በመውዛትና በመድከም ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ዘንድ ተፈርዶባቸው መከራን በመቀበል በምድር ኹሉ ውስጥ የቃልኽን መዝገብ ስለዘሩ ስለነዚኽ ደቀ መዛሙርትኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በእሳት በመከራ የተቀበለ አለ ፤ በጦርም የተወጋ አለ ፤ በሰይፍም የተቆረጠ አለ ፤ በመንኰራኲርም የተፈጨ አለ ፤ በደንጊያም የተወገረ ፤ በበትርም የተቀጠቀጠ አለ ፤ ስለነርሱ ብለኽ ማረኝ አስበኝም ፤ ስለሥቃያቸው ስለመቸገራቸውና ስለደማቸው ብለኽ የእኔን የአገልጋይኽን የዕዳ መጽሐፌን ቅደድ ፤ አሜን። ❞

[   ተአምኆ ቅዱሳን   ]

ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን ፣
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ።


†     🕊   እንኳን  አደረሰን    🕊    †


🕊                        💖                       🕊
                                   
🙏1
🥰2
2025/07/11 21:35:21
Back to Top
HTML Embed Code: