የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መንግስት የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሰጠ
በኢትዮጵያ ለዐይነ ስውራን ትምህርት መሠረተ ልማት የሚውል የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም መሰጠቱ ታወቀ።
ድጋፉ የተሰጠው የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ፕሬዚደንት ሼክ ሞሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን በሰጡት መመሪያ ሲሆን የድጋፍ ስምምነቱን ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር መደረጉም ታውቋለል።
ድጋፉ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬስት መንግሥት ዓለማቀፍ በጎ አድራጎት ተግባራትን ለማስተባበር በዘረጋው ማዕቀፍ፣ ኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ (Erth Zayed Philanthropies) ሥር የሚተገበር ኾኖ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር የሚፈጸም ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት እ ኤ አ.ሜይ 2024 በአዲስ አበባ ተመርቆ በይፋ ሥራ የጀመረው ሼክ ፋቲማ ቢንት ሙባረክ የዓይነ ሥውራን ትምሕርት ቤትን ስኬታማ ጅማሮና ተሞክሮ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የድጋፍ ሰነዱን የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ሚስተር ሞሐመድ ሐጂ አልኩሪ ፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ምኒስትር ደኤታ ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያንና የኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ የበላይ ጠባቂ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አሕመድ አሊ(ዶ/ር) በተገኙበት ተፈርሟል።
1.2 ሚሊዮን ዜጎች የማየት ውሱንነትን በሚያስከትሉ የጤና እክሎች በተጠቁባት፤ ከነዚህም መካከል 332,000 ዓይነ ሥውራን ድጋፉ በተለይ የትምሕርትና የጤና አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ባልተዳረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ያለውን ሰብዓዊ ችግር ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተገልጿል።
መሠረታዊ አገልግሎት በበቂ ሁኔታ በማይገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የሚያጠቃው ነገር ግን በሕክምና ሊድን በሚችለው ትራኮማ በሽታ የተጠቂዎች ቁጥር ኢትዮጵያ ከዓለም ከቀዳሚዎቹ ተርታ ትገኛለች።
በትምሕርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት የአዳዲስ የልዩ ፍላጎት ትምሕርት ቤቶች ግንባታ እንዲከናወን ዕቅድ የተያዘ ሲኾን፣ በዘመናዊ መርጃ መሣሪያዎች የሚደራጁ፣ሙያ-ተኮር ሥርዓተ-ትምሕርት የሚዘጋጅላቸው ኾነው፣ ዓይነ ሥውራን ተማሪዎችን በክኅሎትና በዕውቀት በማብቃት ለከፍተኛ ትምሕርትና የሥራ ዓለም የሚያዘጋጁ የልኅቀት ማዕከላት በመኾን ያገለግላሉ ተብሏል።
ሼክ ጣይብ ቢን ሞሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን (Sheikh Theyab bin Mohamed bin Zayed Al Nahyan)እንደተናገሩት“አገራችን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ እጇን ትዘረጋለች። በኢትዮጵያ ለሚገኙ ዓይነ-ሥውራን እና የዓይን ጤናቸው ለታወከ ተማሪዎች የምናደርገው ይህ ድጋፍ የዚህ ማሳያ ነው። ዓላማችን እነዚህ መሠረታዊ አገልግሎት የተጓደለባቸው ተማሪዎች በተሻለ ከባቢ ተምረው፣ የተሻለ ትምሕርት አግኝተው ሕልማቸውን ዕውን እንዲያደርጉ ማገዝ ነው። በአገራችንና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን መልካም የትብብር መንፈስ ይህ ጅማሬ ፍሬያማ እንደሚያደርገው እምነታችን ከፍ ያለ ነው።” ብለዋል።
ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያን (Sheikh Shakhbout bin Nahyan Al Nahyan) በበኩላቸው “ዘላቂ ልማትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ መሠረት እንደኾኑ እንደ ሀገር ቀድመን ተረድተናል።ይህም ድጋፍ ማኅበረሰቦችን ከችግር ለማላቀቅ፣ ኢኮኖሚው ዕድሎችን እንዲፈጥር ለማስቻልና መሠረታዊ አገልግሎትን ለዜጎች ለማዳረስ ያለን ቁርጠኛ አቋም ማሳያ ይኾናል።ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለን ትብብርም የአፍሪካ አገራት ትምሕርት ወጣቶችን ማብቂያና ዘላቂ ልማትን ማሳለጫ መኾኑን ተረድተው በትምሕርት ልማት ላይ እንዲያተኩሩ ያለንን የትኩረት አቅጣጫ ይገልጽልናል" ብለዋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በበኩላቸው “የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ጥራት ያለው ትምሕርትን ለሁሉም ዜጎቻችን ለማዳረስ የያዝነውን ግብ ለማገዝ የተደረገልን ድጋፍ በመንግሥታችንና በኢትዮጵያውያን ስም ምስጋና ማቅረብ እወዳለሁ። ይህ ድጋፍና አጋርነት ዓይነ-ሥውራን ተማሪዎች ተገቢና በቂ ዕድሎችን አግኝተው ስኬታማ እንዲኾኑ ከማገዙም በላይ ሁሉን-ዐቀፍ ማኅበረሰባዊ ዕድገት እንድናመጣ ትልቅ ግምት የምንሰጠው ድርሻ አለው” ብለዋል።
የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ጄኔራል ሞሀመድ ሀጅ አልኩሪ በበኩላቸው፣ “ትምሕርት መሠረታዊ የሰው ልጆች መብት ነው። ልጆችም ልዩ ፍላጎቶቻቸው ተሟልተውላቸው የመማር ዕድል ሊመቻችላቸው ይገባል። የትምሕርት መሠረተ ልማትና ሥርዓተ ትምሕርትን በማሻሻል አካታችና ሁሉን ጠቃሚ ልማት እንዲመጣ መሠረት በመጣል ላይ ነን። ይህም ድጋፍ ትምሕርት ለትውልዶች የዕድልና የዕድገት ምንጭ ለመኾኑ ማሳያ ከመኾኑ ባሻገር ዓለማቀፍ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ ያለውን ትልቅ ሚና በድጋሚ የሚያረጋግጥ ነው” ብለዋል።
በኢትዮጵያ ለዐይነ ስውራን ትምህርት መሠረተ ልማት የሚውል የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም መሰጠቱ ታወቀ።
ድጋፉ የተሰጠው የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ፕሬዚደንት ሼክ ሞሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን በሰጡት መመሪያ ሲሆን የድጋፍ ስምምነቱን ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር መደረጉም ታውቋለል።
ድጋፉ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬስት መንግሥት ዓለማቀፍ በጎ አድራጎት ተግባራትን ለማስተባበር በዘረጋው ማዕቀፍ፣ ኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ (Erth Zayed Philanthropies) ሥር የሚተገበር ኾኖ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር የሚፈጸም ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት እ ኤ አ.ሜይ 2024 በአዲስ አበባ ተመርቆ በይፋ ሥራ የጀመረው ሼክ ፋቲማ ቢንት ሙባረክ የዓይነ ሥውራን ትምሕርት ቤትን ስኬታማ ጅማሮና ተሞክሮ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የድጋፍ ሰነዱን የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ሚስተር ሞሐመድ ሐጂ አልኩሪ ፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ምኒስትር ደኤታ ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያንና የኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ የበላይ ጠባቂ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አሕመድ አሊ(ዶ/ር) በተገኙበት ተፈርሟል።
1.2 ሚሊዮን ዜጎች የማየት ውሱንነትን በሚያስከትሉ የጤና እክሎች በተጠቁባት፤ ከነዚህም መካከል 332,000 ዓይነ ሥውራን ድጋፉ በተለይ የትምሕርትና የጤና አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ባልተዳረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ያለውን ሰብዓዊ ችግር ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተገልጿል።
መሠረታዊ አገልግሎት በበቂ ሁኔታ በማይገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የሚያጠቃው ነገር ግን በሕክምና ሊድን በሚችለው ትራኮማ በሽታ የተጠቂዎች ቁጥር ኢትዮጵያ ከዓለም ከቀዳሚዎቹ ተርታ ትገኛለች።
በትምሕርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት የአዳዲስ የልዩ ፍላጎት ትምሕርት ቤቶች ግንባታ እንዲከናወን ዕቅድ የተያዘ ሲኾን፣ በዘመናዊ መርጃ መሣሪያዎች የሚደራጁ፣ሙያ-ተኮር ሥርዓተ-ትምሕርት የሚዘጋጅላቸው ኾነው፣ ዓይነ ሥውራን ተማሪዎችን በክኅሎትና በዕውቀት በማብቃት ለከፍተኛ ትምሕርትና የሥራ ዓለም የሚያዘጋጁ የልኅቀት ማዕከላት በመኾን ያገለግላሉ ተብሏል።
ሼክ ጣይብ ቢን ሞሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን (Sheikh Theyab bin Mohamed bin Zayed Al Nahyan)እንደተናገሩት“አገራችን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ እጇን ትዘረጋለች። በኢትዮጵያ ለሚገኙ ዓይነ-ሥውራን እና የዓይን ጤናቸው ለታወከ ተማሪዎች የምናደርገው ይህ ድጋፍ የዚህ ማሳያ ነው። ዓላማችን እነዚህ መሠረታዊ አገልግሎት የተጓደለባቸው ተማሪዎች በተሻለ ከባቢ ተምረው፣ የተሻለ ትምሕርት አግኝተው ሕልማቸውን ዕውን እንዲያደርጉ ማገዝ ነው። በአገራችንና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን መልካም የትብብር መንፈስ ይህ ጅማሬ ፍሬያማ እንደሚያደርገው እምነታችን ከፍ ያለ ነው።” ብለዋል።
ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያን (Sheikh Shakhbout bin Nahyan Al Nahyan) በበኩላቸው “ዘላቂ ልማትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ መሠረት እንደኾኑ እንደ ሀገር ቀድመን ተረድተናል።ይህም ድጋፍ ማኅበረሰቦችን ከችግር ለማላቀቅ፣ ኢኮኖሚው ዕድሎችን እንዲፈጥር ለማስቻልና መሠረታዊ አገልግሎትን ለዜጎች ለማዳረስ ያለን ቁርጠኛ አቋም ማሳያ ይኾናል።ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለን ትብብርም የአፍሪካ አገራት ትምሕርት ወጣቶችን ማብቂያና ዘላቂ ልማትን ማሳለጫ መኾኑን ተረድተው በትምሕርት ልማት ላይ እንዲያተኩሩ ያለንን የትኩረት አቅጣጫ ይገልጽልናል" ብለዋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በበኩላቸው “የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ጥራት ያለው ትምሕርትን ለሁሉም ዜጎቻችን ለማዳረስ የያዝነውን ግብ ለማገዝ የተደረገልን ድጋፍ በመንግሥታችንና በኢትዮጵያውያን ስም ምስጋና ማቅረብ እወዳለሁ። ይህ ድጋፍና አጋርነት ዓይነ-ሥውራን ተማሪዎች ተገቢና በቂ ዕድሎችን አግኝተው ስኬታማ እንዲኾኑ ከማገዙም በላይ ሁሉን-ዐቀፍ ማኅበረሰባዊ ዕድገት እንድናመጣ ትልቅ ግምት የምንሰጠው ድርሻ አለው” ብለዋል።
የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ጄኔራል ሞሀመድ ሀጅ አልኩሪ በበኩላቸው፣ “ትምሕርት መሠረታዊ የሰው ልጆች መብት ነው። ልጆችም ልዩ ፍላጎቶቻቸው ተሟልተውላቸው የመማር ዕድል ሊመቻችላቸው ይገባል። የትምሕርት መሠረተ ልማትና ሥርዓተ ትምሕርትን በማሻሻል አካታችና ሁሉን ጠቃሚ ልማት እንዲመጣ መሠረት በመጣል ላይ ነን። ይህም ድጋፍ ትምሕርት ለትውልዶች የዕድልና የዕድገት ምንጭ ለመኾኑ ማሳያ ከመኾኑ ባሻገር ዓለማቀፍ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ ያለውን ትልቅ ሚና በድጋሚ የሚያረጋግጥ ነው” ብለዋል።
በሕክምና መቶኛ ዓመቱንና በማስተማር ሰባኛ ዓመቱን እያከበረ ያለው ጎንደር ዩንቨርስቲ ና ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 40ኛ ዙር የሕክምና ተማሪዎቹን አስመረቀ
ጎንደር ዩኒቨርሲቲው ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 254 ወንድ እና 112 ሴት የሕክምና ተማሪዎቹን ያስመረቀው ለ40ኛ ጊዜ መሆኑንና ይኸም ዩኒቨርስቲው የተመሠረተበትን ምዕተዓመት እያከበረ ባለበት ጊዜ በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
ተቋሙ ህክምና ተማሪዎች 40ኛ ዙርና 21ኛ ዙር የፋርማሲ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲና ሰብ ስፔሻሊቲ የትምህርት ዘርፎችን ሲከታተሉ የቆዩ መሆናቸው ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ ደረጄ ድጉማ (ዶ/ር ) ፣ የዩንቨርስቲው ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ፣ የጎንደር ከተማ ከንቲባና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን_ዶ/ር)፣ በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች፣ በኮሌጅ የትምህርት ጉባዔ ተመስክሮና በዩንቨርስቲው ሴኔት ጸድቆ ለምርቃት ቀን በቅተዋል ብለዋል፡፡
"ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያ እናንተን በጥብቅ ትፈልጋችኋለችና ይህ ደስታ የእናት አገራችሁ ጭምር ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የሰለጠኑበት ሙያ ፈታኝና የተከበረ ቢሆንም ውጤቱ ግን ፈዋሽ መሆኑን እንደሚገነዘቡ ጠቅሰዋል፡፡
በርካታ "እንቅልፍ አልባ ለሊቶች፣ ስንፍናና ድካም የሻረ ትጋት በብዙ ተግዳሮቶች የተፈተነ ግን ያልተሸነፈ ጥንካሬያችሁ ለዛሬው ቀን አብቅቷችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ለተመራቂ ተማሪዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዴዔታው ዶ/ር ደረጄ ድጉማ በበኩላቸው፤ "ተመራቂዎች አድካሚውን የትምህርት ጉዞ በስኬት አጠናቃችሁ በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው የምርቃት ቀናችሁ እንኳን አደረሳችሁ" ያሉ ሲሆን፤ "ቀጣይ የአገራችን ጉዞ ዛሬ የምትመረቁት ተማሪዎች እጅ ላይ የሚወድቅ ነው" ብለዋል፡፡
ተመራቂ ተማሪዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ያሳሰቡት ዶ/ር ደረጄ፣ በቀጣይ ወደ ሥራ ሲገቡ በሙያቸው አገራቸውንና ወገኖቻቸውን ያለ ስስት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመረቁበት ሙያ ማህበረሰቡን ያለ ምንም አድሎ ሙያው የሚጠይቀውን ስነ ምግባር አክብረው ሀላፊነታቸውን እንሚወጡ ቃል ገብተዋል።
ከ2010 ዓ/ም ጀምረው ሌሊትና ቀን ክረምትና በጋ ሳይሉ ላለፉት 7 ዓመታት በአስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታ ማለፋቸውን ተመራቂ ተማሪዎች በተለይ ለሪፖርተር ተናግረዋል።
በኮሮና ቫይረስ ወቅት ለአንድ ዓመት አቋርጠው እንደነበር ያስታወሱት ተማሪዎቹ፣ በዚያም አንድ ዓመትን ጨምረው 7 ዓመት ቆይታ ማድረጋቸውን ተናግረዋል
በመርሃ ግብሩ ላይም በቅርቡ ሕይወቱ ያለፈውና በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊስት ሃኪም የነበረውን ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜን በማሰብ የህሊና ጸሎት ተደርጓል፡፡
ጎንደር ዩኒቨርስቲ 70ኛ ዓመትና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በማክበር ላይ ሲሆን በስፖርታዊ ውድድር፣ አዳዲስ መሠረተ ልማቶችን በማስጀመር በነፃ ለማኅበረሰቡ አገልግሎት በመስጠት በዓሉን እንደሚያከብር መናገሩ ይታወሳ።
ዩኒቨርሲቲው በ11 ኮሌጆች በ87 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ዛሬ የተመረቁትን ጨምሮ ከ300 በላይ በሁለተኛ ሦስተኛ ዲግሪና ስፔሻላይዜሽን ፕሮግራሞች ከ40 ሺሕ በላይ ያስተናግዳል። ።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲው ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 254 ወንድ እና 112 ሴት የሕክምና ተማሪዎቹን ያስመረቀው ለ40ኛ ጊዜ መሆኑንና ይኸም ዩኒቨርስቲው የተመሠረተበትን ምዕተዓመት እያከበረ ባለበት ጊዜ በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
ተቋሙ ህክምና ተማሪዎች 40ኛ ዙርና 21ኛ ዙር የፋርማሲ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲና ሰብ ስፔሻሊቲ የትምህርት ዘርፎችን ሲከታተሉ የቆዩ መሆናቸው ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ ደረጄ ድጉማ (ዶ/ር ) ፣ የዩንቨርስቲው ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ፣ የጎንደር ከተማ ከንቲባና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን_ዶ/ር)፣ በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች፣ በኮሌጅ የትምህርት ጉባዔ ተመስክሮና በዩንቨርስቲው ሴኔት ጸድቆ ለምርቃት ቀን በቅተዋል ብለዋል፡፡
"ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያ እናንተን በጥብቅ ትፈልጋችኋለችና ይህ ደስታ የእናት አገራችሁ ጭምር ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የሰለጠኑበት ሙያ ፈታኝና የተከበረ ቢሆንም ውጤቱ ግን ፈዋሽ መሆኑን እንደሚገነዘቡ ጠቅሰዋል፡፡
በርካታ "እንቅልፍ አልባ ለሊቶች፣ ስንፍናና ድካም የሻረ ትጋት በብዙ ተግዳሮቶች የተፈተነ ግን ያልተሸነፈ ጥንካሬያችሁ ለዛሬው ቀን አብቅቷችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ለተመራቂ ተማሪዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዴዔታው ዶ/ር ደረጄ ድጉማ በበኩላቸው፤ "ተመራቂዎች አድካሚውን የትምህርት ጉዞ በስኬት አጠናቃችሁ በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው የምርቃት ቀናችሁ እንኳን አደረሳችሁ" ያሉ ሲሆን፤ "ቀጣይ የአገራችን ጉዞ ዛሬ የምትመረቁት ተማሪዎች እጅ ላይ የሚወድቅ ነው" ብለዋል፡፡
ተመራቂ ተማሪዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ያሳሰቡት ዶ/ር ደረጄ፣ በቀጣይ ወደ ሥራ ሲገቡ በሙያቸው አገራቸውንና ወገኖቻቸውን ያለ ስስት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመረቁበት ሙያ ማህበረሰቡን ያለ ምንም አድሎ ሙያው የሚጠይቀውን ስነ ምግባር አክብረው ሀላፊነታቸውን እንሚወጡ ቃል ገብተዋል።
ከ2010 ዓ/ም ጀምረው ሌሊትና ቀን ክረምትና በጋ ሳይሉ ላለፉት 7 ዓመታት በአስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታ ማለፋቸውን ተመራቂ ተማሪዎች በተለይ ለሪፖርተር ተናግረዋል።
በኮሮና ቫይረስ ወቅት ለአንድ ዓመት አቋርጠው እንደነበር ያስታወሱት ተማሪዎቹ፣ በዚያም አንድ ዓመትን ጨምረው 7 ዓመት ቆይታ ማድረጋቸውን ተናግረዋል
በመርሃ ግብሩ ላይም በቅርቡ ሕይወቱ ያለፈውና በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊስት ሃኪም የነበረውን ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜን በማሰብ የህሊና ጸሎት ተደርጓል፡፡
ጎንደር ዩኒቨርስቲ 70ኛ ዓመትና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በማክበር ላይ ሲሆን በስፖርታዊ ውድድር፣ አዳዲስ መሠረተ ልማቶችን በማስጀመር በነፃ ለማኅበረሰቡ አገልግሎት በመስጠት በዓሉን እንደሚያከብር መናገሩ ይታወሳ።
ዩኒቨርሲቲው በ11 ኮሌጆች በ87 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ዛሬ የተመረቁትን ጨምሮ ከ300 በላይ በሁለተኛ ሦስተኛ ዲግሪና ስፔሻላይዜሽን ፕሮግራሞች ከ40 ሺሕ በላይ ያስተናግዳል። ።
የጅቡቲ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ
የ59 ዓመቱ ዲፕሎማትና የጂቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚስተር ማህሙድ ዓሊ ይሱፍ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽንን ሊቀመንበር ሆነው እንዲመሩ ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ ም በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ ተመረጡ።
አሊ ሞሐመድ ይሱፍ ላለፉት ሥምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋኪ ማኅማትን ይተካሉ።
ይሱፍ የተመረጡት የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋንና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚና የፋይናንስ ሚኒስትር የነበሩትን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው።
የአፍሪካ ኅብረት 38ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲጀመር፣ የአንጎላው ፕሬዝደንት ዮዋዎ ሎሬንሶ የዓመቱን የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ሞሐመድ ዑልድ ተረክበዋል።
የ59 ዓመቱ ዲፕሎማትና የጂቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚስተር ማህሙድ ዓሊ ይሱፍ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽንን ሊቀመንበር ሆነው እንዲመሩ ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ ም በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ ተመረጡ።
አሊ ሞሐመድ ይሱፍ ላለፉት ሥምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋኪ ማኅማትን ይተካሉ።
ይሱፍ የተመረጡት የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋንና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚና የፋይናንስ ሚኒስትር የነበሩትን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው።
የአፍሪካ ኅብረት 38ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲጀመር፣ የአንጎላው ፕሬዝደንት ዮዋዎ ሎሬንሶ የዓመቱን የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ሞሐመድ ዑልድ ተረክበዋል።
ፖርላማው አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ
በአራተኛ ዓመት የፓርላማ ዘመን የግማሽ ዓመት እረፍት ላይ የሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት፣ ከተቋቋመ ሶስት አመታትን ያስቆጠረውን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ሪፓርት ለማዳመጥና በፓርላማ የፀደቀለትን የሶስት ዓመት የሥራ ጊዜ እንደገና ለማራዘም፣ በመጭው ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።
ኮሚሽኑ ያላጠናቀቃቸውን ስራዎች ለመጨረስ ተጫመሪ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ከዚህ ቀደም ሲገልፅ ነበር። የኮሚሽኑ የሶስት አመት የስራ ዘመን በያዝነው የካቲት 2017 ዓም ይጠናቀቃል ።
በአራተኛ ዓመት የፓርላማ ዘመን የግማሽ ዓመት እረፍት ላይ የሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት፣ ከተቋቋመ ሶስት አመታትን ያስቆጠረውን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ሪፓርት ለማዳመጥና በፓርላማ የፀደቀለትን የሶስት ዓመት የሥራ ጊዜ እንደገና ለማራዘም፣ በመጭው ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።
ኮሚሽኑ ያላጠናቀቃቸውን ስራዎች ለመጨረስ ተጫመሪ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ከዚህ ቀደም ሲገልፅ ነበር። የኮሚሽኑ የሶስት አመት የስራ ዘመን በያዝነው የካቲት 2017 ዓም ይጠናቀቃል ።
ዘወትር እሁድ የሚጠብቁት የሪፖርተር ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎችን ይዞ በገበያ ላይ ይገኛል
በድረገጻችን https://www.ethiopianreporter.com/ ላይም ያገኙታል።
----------||----------
የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር↠ https://bit.ly/35qeNwV
ቴሌግራም↠ http://bit.ly/37OFEnC
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3p0jUQY
የ ስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com
በድረገጻችን https://www.ethiopianreporter.com/ ላይም ያገኙታል።
----------||----------
የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር↠ https://bit.ly/35qeNwV
ቴሌግራም↠ http://bit.ly/37OFEnC
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3p0jUQY
የ ስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com
የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ
በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።
ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት <<የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው" ብለዋል። አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።
ፎቶ: መስፍን ሰለሞን
በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።
ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት <<የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው" ብለዋል። አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።
ፎቶ: መስፍን ሰለሞን
#ማስታወቂያ
ከተለያየ የዓለም ክፍሎች የሚላክልዎትን ገንዘብ ከሕብረት ባንክ ይቀበሉ፡፡
ከባንካችን ጋር ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች ማለትም ዌስተርን ዪኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስፋስት፣ ሪያ ፣ዳሃብሺል እና ዩፔሲ እንዲሁም በባንኩ ስዊፍት ኮድ - UNTDETAA አማካኝነት ይቀበሉ፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://www.tgoop.com/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#FastRemittances #MoneyTrasnfer #HibretBank #Swift
ከተለያየ የዓለም ክፍሎች የሚላክልዎትን ገንዘብ ከሕብረት ባንክ ይቀበሉ፡፡
ከባንካችን ጋር ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች ማለትም ዌስተርን ዪኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስፋስት፣ ሪያ ፣ዳሃብሺል እና ዩፔሲ እንዲሁም በባንኩ ስዊፍት ኮድ - UNTDETAA አማካኝነት ይቀበሉ፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://www.tgoop.com/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#FastRemittances #MoneyTrasnfer #HibretBank #Swift
#ማስታወቂያ
የካቲት 16 እየደረሰ ነው!
*
ግብይትዎን በፖስ ፈፅመው 10 ሺ ብር የሚሸለሙበት መርሀ ግብር የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡
ከ1,000 ብር ጀምሮ በፖስ ሲከፍሉ
እድል ከቀናዎ የ10 ሺ ብር ተሸላሚ ይሆናሉ፡፡
መልካም ዕድል!
***
የባንካችንን ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃ ያግኙ!
Facebook https://www.facebook.com/combanketh
Telegram https://www.tgoop.com/combankethofficial
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #digitalbanking #pos #banking
የካቲት 16 እየደረሰ ነው!
*
ግብይትዎን በፖስ ፈፅመው 10 ሺ ብር የሚሸለሙበት መርሀ ግብር የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡
ከ1,000 ብር ጀምሮ በፖስ ሲከፍሉ
እድል ከቀናዎ የ10 ሺ ብር ተሸላሚ ይሆናሉ፡፡
መልካም ዕድል!
***
የባንካችንን ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃ ያግኙ!
Facebook https://www.facebook.com/combanketh
Telegram https://www.tgoop.com/combankethofficial
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #digitalbanking #pos #banking
ኢትዩጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 600 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ፕሮጀክት ውል ተፈራረመ
የኢትዩጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚተዳደረው የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን፤ አሴት ግሪን ከተባለ የዩናይትድ ኪንግደም ሃ/የተ/ማህበር ጋር ወደ 600 ሚሊዩን ዶላር የሚጠጋ፣ የተቀናጀ የሰብል ልማት፣ የወተት ተዋጽኦ ምርትና ንግድ ለማከናወን የሚያስችል ፕሮጀክት የአክሲዩን ድርሻ ውል ተፈራረሙ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህና የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በተገኙበት የተፈረመው የአክሲዮን ባለድርሻ ስምምነት፣ የወተት፣ የወተት ተዋፅኦ ምርቶችና የተቀናጀ የሰብል ልማት ስራዎች በ15,000 ሄክታር መሬት ላይ፣ በሁለት ምዕራፍ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ የተቀናጀ የሰብል ልማት፣ የወተት ተዋጽኦ ምርትና ንግድ ላይ እንደሚያተኩር ሲነገር፤ በሁለተኛው የፕሮጀክቱ ክፍል የጥጥ፣ የቅባት እህሎችና የሩዝ ምርቶችም እንደሚካተቱ ተጠቅሷል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ፣ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽንና የዩናይትድ ኪንግደሙ አሴት ግሪን ኃ/የተ/የግ/ ኩባንያ ኃላፊዎች ተፈራርመዋል።
የኢትዩጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚተዳደረው የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን፤ አሴት ግሪን ከተባለ የዩናይትድ ኪንግደም ሃ/የተ/ማህበር ጋር ወደ 600 ሚሊዩን ዶላር የሚጠጋ፣ የተቀናጀ የሰብል ልማት፣ የወተት ተዋጽኦ ምርትና ንግድ ለማከናወን የሚያስችል ፕሮጀክት የአክሲዩን ድርሻ ውል ተፈራረሙ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህና የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በተገኙበት የተፈረመው የአክሲዮን ባለድርሻ ስምምነት፣ የወተት፣ የወተት ተዋፅኦ ምርቶችና የተቀናጀ የሰብል ልማት ስራዎች በ15,000 ሄክታር መሬት ላይ፣ በሁለት ምዕራፍ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ የተቀናጀ የሰብል ልማት፣ የወተት ተዋጽኦ ምርትና ንግድ ላይ እንደሚያተኩር ሲነገር፤ በሁለተኛው የፕሮጀክቱ ክፍል የጥጥ፣ የቅባት እህሎችና የሩዝ ምርቶችም እንደሚካተቱ ተጠቅሷል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ፣ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽንና የዩናይትድ ኪንግደሙ አሴት ግሪን ኃ/የተ/የግ/ ኩባንያ ኃላፊዎች ተፈራርመዋል።