tgoop.com/Hulaadiss/38726
Create:
Last Update:
Last Update:
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሩስያ ሞስኮ ጉብኝት ስምምነት ሲደረስ ጉብኝት ሊያደርጉ እንደሚችሉ ገልጸዋል
ወደ ሞስኮ በትክክለኛው ሰዓት አቀናለሁ ያሉት ፕሬዝዳንቱ ትክክለኛ ጊዜ የሚሆነው የሩስያ እና ዩክሬን የሚጠናቀቅበት ወቅት እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱ በሳምንታት ውስጥ ሊቆም እንደሚችል ገልጸው በሞስኮ እና ኪየቭ መካከል የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ በሩስያ ጉብኝት ሊያደርጉ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
ከሰሞኑ በዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ላይ በሰነዘሩት ከፍተኛ ትችት ከአውሮፓ እና ከዩክሬን ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ፕሬዝዳንቱ ከፈረንዳዩ ፕሬዝዳንት ጋር በትላንትናው ዕለት በዋሽንግተን ተገናኝተዋል፡፡
በነጩ ቤተ መንግስት ከኢማኑኤል ማክሮን ጋር ባደረጉት ውይይት የአውሮፓ የሰላም አስከባሪ ጦር በዩክሬን መሰማራት የሚኖረውን ጠቀሜታ ከማክሮን ማብራርያ ተደርጎላቸዋል፡፡
የአውሮፓውያንን የዩክሬን የሰላም እቅድ ያቀረቡት ማክሮን የአውሮፓ ጦር መሰማራት የሰላም ስምምነቱን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ያለውን ወሳኝነት ገልጸዋል፡፡
BY Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

Share with your friend now:
tgoop.com/Hulaadiss/38726