tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1511
Create:
Last Update:
Last Update:
አሏህን በብችነት ማምልክ በርካቶች ዘንድ የማይታወቅ ፣ በእንግዳነት የሚፈረጅ መንገድ ሆኗል ። የመልእክተኛው ሱና እየተዘነጋ መጤና ለኢስላም ባእድ የሆነው ኮተት ሁሉ የጦዘበትና የተስፋፋበትን ሁኔታ እያየን ነው ። የብዙዎቻችን አመፅና ወንጀል ሞልቶ በመፍሰስ ላይ ነው ። አንዳንዶች ዘንድማ ወንጀል የቀለለ ከመሆን አልፎ የሚፎካከሩበት እሴት ከሆነ ከራርሟል።
ነገሮች በከባድ እና በፍጥነት እየተለዋወጡ እያየን ነው ። ሰላምና መረጋጋታችን አብዝቶ ደፍርሷል ። መሰረታዊ ነገሮችን ማሟላት ለብዙዎች የማይቻል ሸክም እየሆነ መምጣቱን እየተመለከትን ነው ።
ፈተናው አይነቱ በዝቷል ፣ ሸክሙ በርትቷል ነገሮች በወንጀላችን ምክንያት ብልሽትሽት እያሉ ነው ፣ አብዛኛው ደስታንና መረጋጋትን ተነፍጓል ….. ወንጀሉ አመፁ በዛዛዛ !!!!!!
ሞት ፣ ቀብር ፣ አሏህ ፊት መቆም ተዘነጋ !!!
ብርታት እጅጉን የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ። አሏህ ያበርታን ፣ ይመልሰን ፣ መጨረሻችንን ያሳምረው !!
https://www.tgoop.com/Muhammedsirage
BY Ibnu Muhammedzeyn
Share with your friend now:
tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1511