tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1521
Last Update:
በዲን ላይ መገለባበጥ እና በያዙት አቋም ላይ አለመፅናት የአሕሉል ቢደዕ አይነተኛ መገለጫ ነው።
ﻗﺎﻝ ﺍﺑﻦ ﺗﻴﻤﻴﺔ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ : “{ ﺇﻧﻚ ﺗﺠﺪ ﺃﻫﻞ ﺍﻟﻜﻼﻡ ﺃﻛﺜﺮ ﺍﻟﻨﺎﺱ ﺍﻧﺘﻘﺎﻻً ﻣﻦ ﻗﻮﻝ ﺇﻟﻰ ﻗﻮﻝ، ﻭﺟﺰﻣًﺎ ﺑﺎﻟﻘﻮﻝ ﻓﻲ ﻣﻮﺿﻊ، ﻭﺟﺰﻣًﺎ ﺑﻨﻘﻴﻀﻪ، ﻭﺗﻜﻔﻴﺮ ﻗﺎﺋﻠﻪ ﻓﻲ ﻣﻮﺿﻊ ﺁﺧﺮ، ﻭﻫﺬﺍ ﺩﻟﻴﻞ ﻋﺪﻡ ﺍﻟﻴﻘﻴﻦ، }
ለዚህም ሲባል ሸይኹል ኢስላም እንዲህ ይላሉ:- "አንተ የፍልስፍና ባልተቤቶችን ከአንድ ንግግር ወደ አንድ ንግግር በአንድ ቦታ በንግግር መቁረጥን በሌላቦታ ደግሞ ያን ንግግራቸውን በማፍረስ እንዲሁም (ይባስ ብለው) የዚያን የንግግር ባልተቤት በሌላ ቦታ በማክፈር ታገኛቸዋለህ ይህ ደግሞ (በያዙት አቋም ላይ) እርግጠኝነት እንደሌላቸው መረጃ ነው" [መጅሙኡል ፈታዋ (4/ 50)]
የቢድዓና የፊትና ሰው ወጥ አቋም የለውም ባለፈው አመት ሌላ አቋም ዛሬ ሌላ አቋም ወደፊት ሌላ በዲን ስም የተነሳ ፊትና ሁሉ የያዘውን አቋም ያስለቅቀዋል የሚረጋበት ነገር የለም ሁሌ አቋም እንደቀየረ ዛሬ ላይ ሆኖ የትላንቱን ማንነት ነገ ላይ ሲሆን የዛሬውን አቋም እንደተራገመ ይኖራል ምክኒያቱም በመረጃ የተደገፈ እሄነው የሚባል አቋም የለውም።
ሸይኽ ሙሀመድ ሰኢድ ረስላን እንዲህ ይላአሉ:- "ከቢዳዐ ሰዎች አንዱ በአንድ መንገድ ላይ ያነጋል በሌላ መንገድ ላይ ያመሻል ከልቦና እና ከአስተያየት ጋር ከመገለበበጥ አይወገድም በአንድ ነገር ላይ አይፀናም ምክኒያቱም እሱ ዘንድ (የሚፀናበት) እርግጠኛ የሆነ ነገር የለውም
አህሉሱናዎች ጋር (የሚፀኑበት) ቁራኣን እና ሐዲሥ አለ እነርሱም መልእክተኛው (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) የመጡባቸው እውነታዎች ናቸው" [ደዓኢሙ ሚንሀጅ ኑቡዋ (65)]
ሑዘይፋ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ይላል:-
"እውነተኛ ጥመት ብሎ ማለት መጥፎ የምትለውን ነገር ጥሩ አድርገህ ልትመለከት ነው ወይንም ጥሩ የምትለውን መጥፎ አድርገህ ልትመለከት ነው በዲን ላይ መገለባበጥን አደራህን የአላህ ዲን አንድ ነው" [አብረዛቅ ፊል ሙሰነፍ (11/249) አላልካዒይ (120)]
"(ሰለፎች) በዲን ላይ መገለባበጥን ይጠሉ ነበር" [አል-ኢባነቱል ኩብራ(574)]
ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላአሉ:-
"መድሀኒት የለለው በሽታ በዲን ላይ መከረባበት ነው" [አልኢባነቱል ኩብራ (576)]
አላህ በመንሀጀ ሰለፍ ላይ ፅናቱን ይወፍቀን መጨረሻቸው አምሮላቸው ከሚሞቱት ያድርገን
((ይህ ፅሑፍ ከዚህ በስተፊት (ሀምሌ 21/2008) «በመንሀጀ ሰለፍ ላይ መፅናት እና ለፅናት የሚያግዙን ወሳኝ ነጥቦች » በሚል ርእስ ከለቀቅኩት ፅሑፍ ላይ የተቆረጠ ፅሑፍ ነው።
ሙሉውን በዚህ ሊንክ ብገቡ ታገኙታላችሁ
[ www.tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1162 ]
✍ ወንድማችሁ/ ኢብኑ ሙሐመድዘይን
•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•
www.tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn
BY Ibnu Muhammedzeyn
Share with your friend now:
tgoop.com/IbnuMuhammedzeyn/1521