MEBACHA Telegram 128
#ከጉድ_ዘመን_ወደ_እዬዬ_ዘመን ...
_________________________
( #ሚካኤል_እንዳለ )
.
ገና ከጅምሩ ከመስከረም መባቻ እንዲህ ያለ ነገር መስማት ገጠመኝ ነው ለማለት ይከብዳል ፡፡ መልካም አዲስ አመት ምኞት እንጂ እውን መሆኑን ዘንድሮም እንጃ  ፡፡ ከማስመሰል ይልቅ አዲስ ሰውነት ከመንግስት ባለስልጣናት ጀምሮ እስካልመጣ ድረስ አዲስ አመት የለም ፡፡ የሰኔ እና ሰኞ መግጠም ላይ ሲያሾፉ የነበሩ ሰዎች ፤ ሰኔና ሰኞ ሲገጥም ምን እንደሚያመጣ ከተረት በላይ በተግባር አይተውታል፡፡ ለወትሮውኑ ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ ይባል ነበር አሁን መስከረም ጠብቶም ጉድ እንደጉድ መደመጡን ቀጥሏል ፡፡
.
መስከረም ከመባቱ  በአንደኛው እለት ሚስቱን ጨምሮ አራት ሰዎችን የገደለው የፌደራል ፓሊስ አባል ዜና ሰምተን ሳንጨርስ ዛሬ ደሞ በቤንሻንጉል ጉምዝ የመተከል ዞን ጭፍጨፋን ሰማን ፡፡ ነገ ደግሞ ምን እንሰማ ይሆን ? ከነገ ወዲያ…? መንግስታችንም ችግኝ ስለሚተከል ሰው ቢነቀል ችግር የለውም ያለ ይመስላል፡፡ ሰው አቅፎ የማያውቅ ባለስልጣን ችግኝ አቅፎ ፎቶ ሲነሳ ይውላል፡፡ ባለስልጣን የተባለ ሁላ ቢሮውን ትቶ ፌስቡክ ላይ መዋል ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል ፡፡ እኛ ስራ የሌለን እንኳ የማንፓስተውን ያህል ፎቶ ባልስልጣናቱ ሲፓስቱት ይውላሉ፡፡ ስሰጥ እዩኝ ፤ ስረዳ እዩኝ ፤ ሳበላ እዩኝ ማለት እንደ ስራ ተቆጥሯል ፡፡ ትራምፕ ነው ወይስ ፑቲን ደሃ ሲረዳ የሚያሳይ ፎቶ ተነስቶ የሚፓስተው ፡፡ ህዝብን መርዳት እና ህዝብን የረዱ መምሰል ለየቅል ናቸው ፡፡ እየታዩ ከመስራት ሳይታዩ መስራት ፍሬ እንዳለው ተዘንግቷል፡፡ ሙያ በልብ ነው የሚለው የአባቶች ብሂል ለሰለጠነው ሐገር እንጂ ለእኛ ባዳ ሆኗል ፡፡ አንዳንድ ባለስልጣናትማ ፤ ይባስ ብለው የሚለብሱትን ልብስ ለማስተዋወቅ እስከሚመስል ድረስ በጥልፍ ባማረ ነጭ በነጭ ፏ ብለው መፓሰት ሁላ ጀምረዋል ፡፡ ሰው ሲያልቅ ህዝብ ሲጫረስ ግን ዝም ጭጭ ነው ፡፡ ለነሱ አመቱን ሙሉ አመት በዓል ነው፡፡ ለደሃው ህዝብ ግን አንድ ቀን ውሎ ማደር ጭንቅ ሆኗል፡፡ ህዝብ መውጫ መግቢያ ቸግሮት ሰው መሆኑን እስኪጠላ ድረስ መአት በሚሰማባት ሐገር ላይ የባለስልጣናቱ የፌስቡክ ላይ ውድድር እና ፋሽን ሾው ማብዛት ከግራም በላይ ሆኖብናል ፡፡ እኔን ማንም አይነካኝ በሚል እሳቤ የሚደረግ ጉዞ ''እውር እውርን እንደሚመራው '' መጨረሻው ገደል ነው፡፡ ምናገባኝ ማለት በኋላ የሚያመጣውን መዘዝ  አላስተዋሉት ይሆናል ፡፡ ትላንት ህዝብ ሲቸገር ምናገባኝ ያሉ ዛሬ የት እንዳሉ አይታችሁ ተማሩ፡፡ ፍርድ ከመለኮት እንጂ ከምድር ተገኝታ አታውቅም፡፡ የምታስቡት ስንት አመት መቀመጥ አለብኝ የምትለዋን ቀመር እንጂ የዜጎችን ስቃይ አይደለምና ፡፡ መንግስት ከመንግስት በደም የሚወርሰው በሽታ እስከሚመስል ድረስ ማስመሰል እና ሴራ ካንሰር ሆኖብናል፡፡
.
ከለውጡ በላይ የናፈቀን ነገር ቢኖር ''ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዋች እና መንግስት መቼ እንደሚተዋወቁ '' ማወቅ ብቻ ነው፡፡ ሚዲያው ሁሉ ዜና ሲሰራ '' ማንነታቸው ባልታወቁ '' ካላለ ዜና የሰራ አይመስለውም ፡፡ ግልጽነት እና ተጠያቂነት በሌለበት በዚህ አካሄዳችን ከቀጠልን ''ከሰማይ የመጡ ዩፎዎች አደጋ አድርሰው ሄዱ'' የሚል ዜና በቅርቡ መስማታችን አይቀርም፡፡ ከእንጀራ ጥያቄ ተላቆ ለህሊናው የሚሰራ የመንግስት አካል እንደ ምንሊክ ድኩላ ተመናምኗል፡፡ ሁሉም ዛሬን ከኖረ ነገንም የሚኖር ይመስለዋል፡፡ እከርማለው ብለህ ስራ እሞታለው ብለህ ኑር የተባለውን እረስቷል ፡፡ እከርማለው ብሎ የሚሰራ መሞቱን ስለሚያውቅ ህዝብን ስለ እውነት ያገለግላል ፡፡ እኖራለው ብሎ የሚያምን ግን መሞቱን ስለሚረሳ በህዝብ ላይ መከራ ሲያወርድ ይኖራል፡፡ መከራ ሲደርስ ዝም ብሎ ማየት ተባባሪነትን ያመጣል፡፡
ይህ ደግሞ የኖርንበት ነውና አዲስ የተባለውን ለውጥ አዲስነት ያጠራጥረዋል፡፡ ለሰው የሚታይ ፊትን ብቻ እየታጠቡ ገላዬ ንፁህ ነው ማለት አይቻልም፡፡ መንግስት ከወረዳ ጀምሮ እስከ አናቱ እራሱን ካላፀዳ የዚህች ሐገር ብልፅግና አንድ ወደ ፊት ሁለት ወደኋላ ይሆናል፡፡ ይህን እያዩ እንዳልዩ ዝም ማለት ወንዝ ወዶ ውሃ ልቅዳ እንዳለው ጨው ተሸርሽሮ ማለቅን ያስረሳል፡፡ቆርጠው የሚለኩ ባለሙያዎችን ይዞ መጓዙ ትርፉ ቁርጥራጭን ማብዛት ነው፡፡ ለክተው የሚቆርጡትን ብልሆች በሞሉባት ሐገር  የቆርጦ ቀጥል መዋቅርን ማፍረስ ካልተቻለ ሰላም አይኖርም፡፡
.
ወደ ክበባችን እንመለስና ስለተነሳንበት እርዕስ እናውጋ ፤ ዘመነ ዩሐንስ ሰማይ የተደፋብን ያክል ከብዶን አለፈ፡፡ ለማቴዎስም አስረክቦናል፡፡ ማቴዎስም ከጅምሩ ጉድ እያሰማን ነው፡፡ የአቡሻህር ሆነ የመርሐ እውራን ወይም የባህረ ሐሳብ እና የፍካሬ ከዋክብት ቀመር ሊቃውንት  እንደሚናገሩት ከሆነ በዘመነ ማቴዎስ ከረሃብ ይልቅ ጦርነት እጅጉን ይበዛል ፡፡  ይህንም ለማረጋገጥ የታላቁን ሊቅ (የሐሽማል ደራሲ) የማእበል ፈጠነን ገጽ መበርበር ብቻ በቂ ነው፡፡ በትንሹም ቢሆን ጠቁሞናል፡፡
.
መቼም ዘንድሮ ጸሎታችን እራሱ ካልተቀየረ ዋጋ የሚያስገኝ አሎነም፡፡ ስለ ጻድቃን ብለህ ሳይሆን ስለ ድንቁርናችን ብለህ ማረን ማለቱ ሳያዋጣ እንደማይቀር ዲያቆን ብርሐኑ አድማስ ጠቁሞናል ፡፡ በቃ እንደ እንስሣት ቁጠረን ማለቱ ሳይቀለን አይቀረም፡፡ እሱንም ከእንስሳቱ ከተሻልን ነው፡፡ ምክኒያቱም በጻድቃ ጸሎት መአቱን እናልፈው ዘንድ ገና ብቃቱ እራሱ የለንም ፡፡ አንዳንዴ እንደ ሎጥ የሚለመንለት ሰው መሆን እስካልቻልን ድረስ የማንም ጸሎት አያተርፈንም ፡፡ ሰዶምን በሚያክል የሐጢያት ከተማ ውስጥ ይኖር የነበረው ሎጥ ፤ በሚሰማው እና በሚያየው ነገር እጅግ ነፍሱን ያስጨንቃት ነበር ፡፡ በዚህም ጭንቀቱ የተነሳ የአብርሃም ፀሎት አግዛው ከዞሐር ተራራ ተሸሽጎ ከሰዶም ጥፋት ዳነ፡፡ ዛሬስ ? ከሰዶም ዘመን ቢበልጥ እንጂ የማያንስ ስንት መአት እና ውርጅብኝ እያየን ነፍሳችንን እናስጨንቅ ይሆን ? የሞት ዜና በሰማን በደቂቃ ልዩነት ቻናል ቀይረን በዘፈን አልጨፈርንም ? እና ታዲያ ምናችንን አይቶ በፃድቃን ፀሎት ይማረን ? ፡፡ እንደ ሰራጵታዋ ታላቅ ሴት ሊበረከት የሚችል ትንሽ የእምነት ዘይት እስካልያዝን ድረስ የእነ ኤልሳ በረከት ወደ እኛ ሊመጣ አይችልም ፡፡
.
ብቻ የመቋጫው ዘመን ሲደርስ ''እባክህ አምላኬ አትመራመረኝ
እንደ በላሄ ሰብ በጥቂት ውሃ ማረኝ '' ለማለት እንችል ዘንድ ጥቂት ውሃ'ኳን ብትሆን ከኛ ይፈለጋል ፡፡ በዜሮ ምግባር በጻድቃን ጸሎት ብቻ ማረኝ ማለት በራሱ ፈጣሪን መፈታተን ነው ፡፡ ጥቂት ጠብታ ሲኖር ብቻ ነው የእመቤታችን ፀሎት ተጨምሮ እንደ በላሄ ሰብ በህይወታችን ስራ የሚሰራው፡፡ አንድዬ ይህን ዓመት'ኳ ከእንደዚ አይነት ወሬ እናርፍ ዘንድ የእርሱ ፍቃድ ይሁን ፡፡ መልካም አዲስ አመትን ሳይሆን መልካም አዲስ ሰውነትን ያምጣልን፡፡ መሪዋቻችንም ቢሆኑ ታክቲካቸውንና  ልብሳቸውን ሳይሆን ህሊናቸውን የሚቀይሩበት ዘመን ያድግልን፡፡ ሌላ ምን ይባላል እዬዬም ሲደላ ነውና ፡፡ ቢያንስ ተሳቀን ሳይሆን ደልቶን እዬዬ የምንልበትን ቀን ያምጣልን፡፡    



tgoop.com/Mebacha/128
Create:
Last Update:

#ከጉድ_ዘመን_ወደ_እዬዬ_ዘመን ...
_________________________
( #ሚካኤል_እንዳለ )
.
ገና ከጅምሩ ከመስከረም መባቻ እንዲህ ያለ ነገር መስማት ገጠመኝ ነው ለማለት ይከብዳል ፡፡ መልካም አዲስ አመት ምኞት እንጂ እውን መሆኑን ዘንድሮም እንጃ  ፡፡ ከማስመሰል ይልቅ አዲስ ሰውነት ከመንግስት ባለስልጣናት ጀምሮ እስካልመጣ ድረስ አዲስ አመት የለም ፡፡ የሰኔ እና ሰኞ መግጠም ላይ ሲያሾፉ የነበሩ ሰዎች ፤ ሰኔና ሰኞ ሲገጥም ምን እንደሚያመጣ ከተረት በላይ በተግባር አይተውታል፡፡ ለወትሮውኑ ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ ይባል ነበር አሁን መስከረም ጠብቶም ጉድ እንደጉድ መደመጡን ቀጥሏል ፡፡
.
መስከረም ከመባቱ  በአንደኛው እለት ሚስቱን ጨምሮ አራት ሰዎችን የገደለው የፌደራል ፓሊስ አባል ዜና ሰምተን ሳንጨርስ ዛሬ ደሞ በቤንሻንጉል ጉምዝ የመተከል ዞን ጭፍጨፋን ሰማን ፡፡ ነገ ደግሞ ምን እንሰማ ይሆን ? ከነገ ወዲያ…? መንግስታችንም ችግኝ ስለሚተከል ሰው ቢነቀል ችግር የለውም ያለ ይመስላል፡፡ ሰው አቅፎ የማያውቅ ባለስልጣን ችግኝ አቅፎ ፎቶ ሲነሳ ይውላል፡፡ ባለስልጣን የተባለ ሁላ ቢሮውን ትቶ ፌስቡክ ላይ መዋል ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል ፡፡ እኛ ስራ የሌለን እንኳ የማንፓስተውን ያህል ፎቶ ባልስልጣናቱ ሲፓስቱት ይውላሉ፡፡ ስሰጥ እዩኝ ፤ ስረዳ እዩኝ ፤ ሳበላ እዩኝ ማለት እንደ ስራ ተቆጥሯል ፡፡ ትራምፕ ነው ወይስ ፑቲን ደሃ ሲረዳ የሚያሳይ ፎቶ ተነስቶ የሚፓስተው ፡፡ ህዝብን መርዳት እና ህዝብን የረዱ መምሰል ለየቅል ናቸው ፡፡ እየታዩ ከመስራት ሳይታዩ መስራት ፍሬ እንዳለው ተዘንግቷል፡፡ ሙያ በልብ ነው የሚለው የአባቶች ብሂል ለሰለጠነው ሐገር እንጂ ለእኛ ባዳ ሆኗል ፡፡ አንዳንድ ባለስልጣናትማ ፤ ይባስ ብለው የሚለብሱትን ልብስ ለማስተዋወቅ እስከሚመስል ድረስ በጥልፍ ባማረ ነጭ በነጭ ፏ ብለው መፓሰት ሁላ ጀምረዋል ፡፡ ሰው ሲያልቅ ህዝብ ሲጫረስ ግን ዝም ጭጭ ነው ፡፡ ለነሱ አመቱን ሙሉ አመት በዓል ነው፡፡ ለደሃው ህዝብ ግን አንድ ቀን ውሎ ማደር ጭንቅ ሆኗል፡፡ ህዝብ መውጫ መግቢያ ቸግሮት ሰው መሆኑን እስኪጠላ ድረስ መአት በሚሰማባት ሐገር ላይ የባለስልጣናቱ የፌስቡክ ላይ ውድድር እና ፋሽን ሾው ማብዛት ከግራም በላይ ሆኖብናል ፡፡ እኔን ማንም አይነካኝ በሚል እሳቤ የሚደረግ ጉዞ ''እውር እውርን እንደሚመራው '' መጨረሻው ገደል ነው፡፡ ምናገባኝ ማለት በኋላ የሚያመጣውን መዘዝ  አላስተዋሉት ይሆናል ፡፡ ትላንት ህዝብ ሲቸገር ምናገባኝ ያሉ ዛሬ የት እንዳሉ አይታችሁ ተማሩ፡፡ ፍርድ ከመለኮት እንጂ ከምድር ተገኝታ አታውቅም፡፡ የምታስቡት ስንት አመት መቀመጥ አለብኝ የምትለዋን ቀመር እንጂ የዜጎችን ስቃይ አይደለምና ፡፡ መንግስት ከመንግስት በደም የሚወርሰው በሽታ እስከሚመስል ድረስ ማስመሰል እና ሴራ ካንሰር ሆኖብናል፡፡
.
ከለውጡ በላይ የናፈቀን ነገር ቢኖር ''ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዋች እና መንግስት መቼ እንደሚተዋወቁ '' ማወቅ ብቻ ነው፡፡ ሚዲያው ሁሉ ዜና ሲሰራ '' ማንነታቸው ባልታወቁ '' ካላለ ዜና የሰራ አይመስለውም ፡፡ ግልጽነት እና ተጠያቂነት በሌለበት በዚህ አካሄዳችን ከቀጠልን ''ከሰማይ የመጡ ዩፎዎች አደጋ አድርሰው ሄዱ'' የሚል ዜና በቅርቡ መስማታችን አይቀርም፡፡ ከእንጀራ ጥያቄ ተላቆ ለህሊናው የሚሰራ የመንግስት አካል እንደ ምንሊክ ድኩላ ተመናምኗል፡፡ ሁሉም ዛሬን ከኖረ ነገንም የሚኖር ይመስለዋል፡፡ እከርማለው ብለህ ስራ እሞታለው ብለህ ኑር የተባለውን እረስቷል ፡፡ እከርማለው ብሎ የሚሰራ መሞቱን ስለሚያውቅ ህዝብን ስለ እውነት ያገለግላል ፡፡ እኖራለው ብሎ የሚያምን ግን መሞቱን ስለሚረሳ በህዝብ ላይ መከራ ሲያወርድ ይኖራል፡፡ መከራ ሲደርስ ዝም ብሎ ማየት ተባባሪነትን ያመጣል፡፡
ይህ ደግሞ የኖርንበት ነውና አዲስ የተባለውን ለውጥ አዲስነት ያጠራጥረዋል፡፡ ለሰው የሚታይ ፊትን ብቻ እየታጠቡ ገላዬ ንፁህ ነው ማለት አይቻልም፡፡ መንግስት ከወረዳ ጀምሮ እስከ አናቱ እራሱን ካላፀዳ የዚህች ሐገር ብልፅግና አንድ ወደ ፊት ሁለት ወደኋላ ይሆናል፡፡ ይህን እያዩ እንዳልዩ ዝም ማለት ወንዝ ወዶ ውሃ ልቅዳ እንዳለው ጨው ተሸርሽሮ ማለቅን ያስረሳል፡፡ቆርጠው የሚለኩ ባለሙያዎችን ይዞ መጓዙ ትርፉ ቁርጥራጭን ማብዛት ነው፡፡ ለክተው የሚቆርጡትን ብልሆች በሞሉባት ሐገር  የቆርጦ ቀጥል መዋቅርን ማፍረስ ካልተቻለ ሰላም አይኖርም፡፡
.
ወደ ክበባችን እንመለስና ስለተነሳንበት እርዕስ እናውጋ ፤ ዘመነ ዩሐንስ ሰማይ የተደፋብን ያክል ከብዶን አለፈ፡፡ ለማቴዎስም አስረክቦናል፡፡ ማቴዎስም ከጅምሩ ጉድ እያሰማን ነው፡፡ የአቡሻህር ሆነ የመርሐ እውራን ወይም የባህረ ሐሳብ እና የፍካሬ ከዋክብት ቀመር ሊቃውንት  እንደሚናገሩት ከሆነ በዘመነ ማቴዎስ ከረሃብ ይልቅ ጦርነት እጅጉን ይበዛል ፡፡  ይህንም ለማረጋገጥ የታላቁን ሊቅ (የሐሽማል ደራሲ) የማእበል ፈጠነን ገጽ መበርበር ብቻ በቂ ነው፡፡ በትንሹም ቢሆን ጠቁሞናል፡፡
.
መቼም ዘንድሮ ጸሎታችን እራሱ ካልተቀየረ ዋጋ የሚያስገኝ አሎነም፡፡ ስለ ጻድቃን ብለህ ሳይሆን ስለ ድንቁርናችን ብለህ ማረን ማለቱ ሳያዋጣ እንደማይቀር ዲያቆን ብርሐኑ አድማስ ጠቁሞናል ፡፡ በቃ እንደ እንስሣት ቁጠረን ማለቱ ሳይቀለን አይቀረም፡፡ እሱንም ከእንስሳቱ ከተሻልን ነው፡፡ ምክኒያቱም በጻድቃ ጸሎት መአቱን እናልፈው ዘንድ ገና ብቃቱ እራሱ የለንም ፡፡ አንዳንዴ እንደ ሎጥ የሚለመንለት ሰው መሆን እስካልቻልን ድረስ የማንም ጸሎት አያተርፈንም ፡፡ ሰዶምን በሚያክል የሐጢያት ከተማ ውስጥ ይኖር የነበረው ሎጥ ፤ በሚሰማው እና በሚያየው ነገር እጅግ ነፍሱን ያስጨንቃት ነበር ፡፡ በዚህም ጭንቀቱ የተነሳ የአብርሃም ፀሎት አግዛው ከዞሐር ተራራ ተሸሽጎ ከሰዶም ጥፋት ዳነ፡፡ ዛሬስ ? ከሰዶም ዘመን ቢበልጥ እንጂ የማያንስ ስንት መአት እና ውርጅብኝ እያየን ነፍሳችንን እናስጨንቅ ይሆን ? የሞት ዜና በሰማን በደቂቃ ልዩነት ቻናል ቀይረን በዘፈን አልጨፈርንም ? እና ታዲያ ምናችንን አይቶ በፃድቃን ፀሎት ይማረን ? ፡፡ እንደ ሰራጵታዋ ታላቅ ሴት ሊበረከት የሚችል ትንሽ የእምነት ዘይት እስካልያዝን ድረስ የእነ ኤልሳ በረከት ወደ እኛ ሊመጣ አይችልም ፡፡
.
ብቻ የመቋጫው ዘመን ሲደርስ ''እባክህ አምላኬ አትመራመረኝ
እንደ በላሄ ሰብ በጥቂት ውሃ ማረኝ '' ለማለት እንችል ዘንድ ጥቂት ውሃ'ኳን ብትሆን ከኛ ይፈለጋል ፡፡ በዜሮ ምግባር በጻድቃን ጸሎት ብቻ ማረኝ ማለት በራሱ ፈጣሪን መፈታተን ነው ፡፡ ጥቂት ጠብታ ሲኖር ብቻ ነው የእመቤታችን ፀሎት ተጨምሮ እንደ በላሄ ሰብ በህይወታችን ስራ የሚሰራው፡፡ አንድዬ ይህን ዓመት'ኳ ከእንደዚ አይነት ወሬ እናርፍ ዘንድ የእርሱ ፍቃድ ይሁን ፡፡ መልካም አዲስ አመትን ሳይሆን መልካም አዲስ ሰውነትን ያምጣልን፡፡ መሪዋቻችንም ቢሆኑ ታክቲካቸውንና  ልብሳቸውን ሳይሆን ህሊናቸውን የሚቀይሩበት ዘመን ያድግልን፡፡ ሌላ ምን ይባላል እዬዬም ሲደላ ነውና ፡፡ ቢያንስ ተሳቀን ሳይሆን ደልቶን እዬዬ የምንልበትን ቀን ያምጣልን፡፡    

BY መባቻ ©


Share with your friend now:
tgoop.com/Mebacha/128

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial) Clear With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. ZDNET RECOMMENDS While the character limit is 255, try to fit into 200 characters. This way, users will be able to take in your text fast and efficiently. Reveal the essence of your channel and provide contact information. For example, you can add a bot name, link to your pricing plans, etc.
from us


Telegram መባቻ ©
FROM American