Telegram Web
ዐረገ በእልልታ
@Mgetem

የተዋሐደውን ሥጋ ፤
የከፈለበትን ዋጋ ፤
አልተወውም በመቃብር ፤
ከፍ አደረገው በክብር ፤
የአዳምም ፀጋ ፤ ከቀድሞ በለጠ
በዘባነ ኪሩብ ፤ ሰው ልጅ ተቀመጠ ።
ዛሬ በደመና ፤ ሰማይ ተቀበለው
ትላንትና ዮሴፍ ፤ እንደ ጠቀለለው ።
ዛሬ በአባቱ ቀኝ ፤ ከበረ ክርስቶስ
ትላንት እንደ ቆመ ፤ በቅጥረ ጲላጦስ።
ዛሬ በመለከት ፤ ዐረገ በእልልታ
ትላንትና ህማም ፤ የዋለበት ጌታ።
ዛሬ ዘመሩለት ፤ መላእክት አጅበው
ትላንትና ጭፍሮች ፤ ያፌዙበት ከበው።
ዛሬም ቢሆን ፥ ወደ ሰማይ ፤ ነገም ቢሆን ትላንትና
እንደ ኢየሱስ ፥ ከፍ አይልም ፤ ዝቅ ያላለ በትህትና ።

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem

አቤል ታደለ

ለአስተያየት : @abeltadele
ዓርገ ሰማያተ በዓምደ ደመና፥
ለድንግል ተፈትሐ ማኅፀና፥
ለደቂቀ እስራኤል ዘአውረደ መና፥
ዓርገ ሰማያተ በአምደ ደመና።

ውርስ ትርጉም

በድንግል ማኅፀን፥
ያን ሥጋ አዳምን፥
ወደ አምላክነት ልዕልና ያሳረገ፥
በአምደ ደመና ወደ ሰማይ አረገ፥
ለእስራኤል ልጆች ያወረደ መና፥
ዐረገ በስብሐት በዐምደ ደመና።

ዚቅ

እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ በሰላም አደረሳችሁ!

____
www.tgoop.com/andkelem
www.tgoop.com/andkelem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ቅድስት_እናት
@Mgetem

ይቺ ቅድስት እናት _ ቃልን ወሰነችው
በከብቶቹ ግርግም_ ወልዳ ታቀፈችው
በመጠቅለያም_ጠቀለለችው።

ለደቱንም ዘር_ አልቀደመውም
የዳዊት ሥር ነው_መድኃኒአለም
በመወለዱም ድንግልናዋን_አልለወጠውም
የተዘጋች ደጃፍ_እናታችን ማርያም።

ቃል ከአብ _ ያለ ድካም ወጣ
የአዳም ልደቱ_ ደረሰለት ዕጣ
ከድንግልም ያለ _ሕማም ተወለደ
በእውነተኛው ብርሃን_ከሳሽ ተሰደደ።

ምጥ ሳያገኛት_ተሰማ እልልታ
ሰበአ ሰገል መጡ_ሊሰግዱ ለጌታ
እረኞች _ ዘመሩ ተሞልተው ደስታ።

ለአምላክነቱ አመጡለት _ዕጣን
ለንጉሥነቱ _ አቀረቡ ወርቁን
መድኃኒት ነውና _ ገለጡት ትንቢቱን
እነሆ አየነው_ ምስዋዕት ከርቤውን።

ግርማ ያለሽ_ድንግል የአሮን በትር
እናደንቅሻለን _ የሁላችን ክብር
ገናንነትሽን _ልንዘረዝር
በያሬድ ውብ ዜማ_ በዳዊት መዝሙር
ቆመናል ከደጅሽ_ ልንደረድር።

እንደ መልአኩ ገብርኤል_ ከላይ እንደመጣው
ልናመሰግንሽ _ ማርያም ግድ ነው
የባሕሪያችን መዳን_ካንቺ ተገኘልን
በማሕጸንሽ ፍሬ_ሞት ተቀበረልን።

እንደ ሠርግ _ቤት ጉድፍ የሌለብሽ
መንፈስ ቅዱስ _ ያደረብሽ
የልዑል ኃይልም ማርያም ጸለለበሽ ።

ዘለአለም ነዋሪ_የነገስታት ንጉስ
ከኃጢአት ያዳነን_ ይመስገን ኢየሱስ
የልባችን ሰላም_ፍቅርህ በኛ ይንገስ።

ከአብ የተወለደ _ከአለም በፊት የነበረ
አንዱ ቃል እራሱን ( ባሕሪዩን) ሰወረ
እንደምን ይረቃል_የሰማዩ ምስጢር
የሱ ያደረገን_ ይመስገን እግዚአብሔር።

የኪዳን ጽላት_ያለብሽ
የተሰወረ መና_የተሸከምሽ
የወርቅ መሶብ_ የምንልሽ
ደብተራ ድንኳን _አንቺ ነሽ
የጥበብን ወንጌል_ በክንድሽ የታቀፍሽ
አሳስቢ ድንግል ሆይ_ ለመሃሪው ልጅሽ
እናምናለንና _ ሁሉ እንደሚቻልሽ

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
# መስክር
https://www.tgoop.com/Mgetem

ልጨክን እልና....
ላልጨክን  ተዋለው :
የእውነት ለመኖር....
የውሸት ኖራለው:

ክርስቲያን ነኝ  ብልም 
ግብሬ ግን ሌላ ነው :
ላልጨክን መጨከን
ለኔ  አይነት አዳ ነው ::
  
       ወይ እውነት ወይ ሐሰት :
       ወይ ድፍረት ወይ ሃፍረት :
       መመስከር ግድ ነው
        አኔ በማምንበት::

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
ማርያም እስካለ
@Mgetem

የበግ ለምድ ለበሶ ፤ አስመሳዩ ተኩላ
ከእናታችን ነጥቆ ፤ እኛንም ሊበላ
መስሎ ተቆርቋሪ ፤ የእውነት ጠበቃ
ፀሀይን ጋረደች ፤ ይለናል ጨረቃ ።
ደካማ ነው ብሎ ፤ ሺ ጊዜ ቢወድቅም
ማርያም እስካለ ፤ ሰይጣን ሰው አይንቅም።
የጥላቻ መርዙን ፤ በወንጌል አስታኮ
የኛንም ምስጋና ፤ ይለዋል አምልኮ ።
ደግነቷ እንጂ ፤ የጌታዬ እናቱ
ከክፉ ጠማማ ፤ ከእንደኛ አይነቱ
አለም ካሰመጠን ፤ በኃጢያት ማእበል
ባልተገባት ነበር ፤ ምስጋና መቀበል።

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
✍️ አቤል ታደለ

ለአስተያየት : @abeltadele
እንደምን አይገርም
@Mgetem

አምላክን መጽነሷን ፤ እመብርሃን አውቃ
ዘመዷን ኤልሳቤጥ ፤ ሄዳ መጠየቋ
እንደምን አይገርም ።
ከሴቶች መካከል ፤ ከፃድቃኑም ጎራ
አንቺ ብርክት ነሽ ፤ ተብላ ሳትኮራ
ወደ ተራራማው ፤ የይሁዳ ከተማ
ፈጥና መነሳቷ ፤ ጥቂት ሳታቅማማ
እንደምን አይገርም ።
ታላቅ የምስራች ፤ ሆኖ የእሷ ጉዳይ
ከታናሹ ደስታ ፤ ልትሆን ተካፋይ
አማናዊ ፀሀይ ፤ በማህፀኗ ይዛ
የኮከቡን እናት ፤ ልትጎበኝ መጓዟ
እንደምን አይገርም ።
የንጉሦች ንጉስ ፤ ፈጣሪን ጸንሳ
ትእቢት ሳይኖርባት ፤ ዘመድ ማስታወሷ
ክብሯን ሳትነፃፅር ፤ ከኤልሳቤጥ ጋራ
አጃቢ ሳትሻ ፤ መንገድ መጀመሯ
እንደምን አይገርም።

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
አቤል ታደለ
ለአስተያየት :
@abeltadele
ንሸጣ፦የብርሃን እናት (ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ)
እርሱ ሚካኤል ነው
@Mgetem

ወደ ፅድቅ መንገድ ፤ እኛን እየመራ
እግዜር እንዳይቆርጠን ፤ ፍሬ ሳናፈራ
እርሱ ሚካኤል ነው ፤ የመላእክት አለቃ
ባማላጅነቱ ፤ የሆነን ጠበቃ።
ለባሕራን የሞቱን ፤ ደብዳቤ የቀየረ
ሰይጣን ዳቢሎስን ፤ በሲኦል ያሰረ
እስራኤልን ከግብፅ ፤ መርቶ ያሻገረ
እርሱ ሚካኤል ነው ፤ ሀያል የከበረ ።
የሰናክሬም ጦሮች ፤ ቢሆኑ ብዙሃን
ሳይዋጋ የፈጃቸው ፤ በሰይፉ ብርሃን
አዛኝና የውሃ ፤ ከጥፋት ታዳጊ
እርሱ ሚካኤል ነው ፤ የእኛ አሳዳጊ ።

አቤል ታደለ

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem

ለአስተያየት : @abeltadele
#አሻግረን_ባህሩን
@Mgetem

ለነፃነት ያልነዉ፣ የግብፅ ህልም እንጀራ ፣ ባርነት ሆኖብን፤
የሸጥነዉም ዮሴፍ፣ በሕሊና ወንበር ፣ እየፈረደብን፤
በባዕድ ሀገር በዝተን ፣ የበረከት ፈንታዉ ፣ ጥሎን ከሥጋቱ፥
የወለድነዉን ልጅ ፣ መልሰን ከጭቃዉ ፣ ረግጦ መጫወቱ፥
ያኘክነዉም ጮማ ፣ ከጥርሳችን ሳይወርድ ፣ የመርገም ሞት ጠርቶ፥
የመኖር ህግ ሲጎድል፣ በሞት ተጠግቶ…ሞትን ተመክቶ፤
ከአስሩ መቅሰፍት፣ ቸነፈር ረሃቡ ፣ ተዓምር ድንቃ ድንቁ፤
አንድ አማኝን አጥተዉ ፣ በኩረ ሞት እስኪደርስ፣ ድንጋን ላይ ሲወድቁ፤
የምፅዓት ምልክት፣ በበሮቹ መቃን፣ ቢቀባ በበግ ደም፤
የግብፃዉያን ዓይን- የጡቡን ግንብ እንጂ ፣ ይህን ማየት አይወድም።
የተፈራዉ ደርሷል፣ ሞት ገብቷል በየቤት ፣ ሀገር ተሸብራል፤
የመቅሰፍት ወላፈን ፣ መጥቶ ሲጥል እንጂ፣ ሲሄድ ተሰዉሯል፤
ለእምነት የሚሆን ፣ የበግ ደም ያለበት ፣ የእምነት ፍሪዳ፥
አንሶ ዋይታ ሆኗል፣ በፈረኦን ቤትም ፣ በእስራኤልም ጓዳ፤
ለነፃነት ብለን ፣ ሌሊት የተጓዝነዉ፣ ሌሊቱ ረዝሞብን፥
ከቀመስነዉ መና ፣ የለመድነዉ ሽንኩርት ፣ ያምናዉ አይሎብን፥
የጨረቃዉ ድምቀት፣ የኮከቡ ምሪት ፣ የሌሊቱ መንገድ፥
አንተ ካላበራህ ፣ ለመቆም አይሆንም፣ እንኳንስ ለመሄድ፤
የጪንጫ ላይ ወሃ፣ አይፈልቅም ያለ አንተ ፣ ለጥማችን አይሆን፤
የበረሃ ልብሳችን ፣ ለቀን አይበረክት፣ አያረካ ለዓይን፤
የገመጥነዉ ሥጋ ፣ ከጉሮሮ ሳይወርድ ፣ ሆኖብን ሞት ጠሪ፤
በሄድንበት ጉዞ፣ ያለ ሩኅሩኅ መልአክ ፣ ያለ መንገድ መሪ።
ከፊታችን ቆሟል ፣ የኤርትራ ባህር ፣ ግንብ ሆኖ በመፍሰስ፤
ከኋላችን መጥቷል ፣ የፈረኦን ሠራዊት ፣ ጦር ሰብቆ በፈረስ፤
ከሁለቱም በፊት ፣ ከሙሴ በትር ጋር ፣ ሚካኤል ሆይ ድረስ።
በጦርም በባህርም ፣ የኢትዮጵያ ድንኳን፣ አይተህ መሸበሩን፤
ልንሰጥም ነዉና፣ መልአከ ምህረት ሆይ ፣ አሻግረን ባህሩን።

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
አሸን መሰናክል በጫንቃዬ አዝዬ
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት

በጸሎቴ መሀል የሀሰትን መና
ሽቅብ አንጠልጥሎ ሰቅሎ ከደመና
"ይብቃህ ዳዊት መድገም - ተው ውዳሴ ማርያም
ምስጋና፣ መሻትህ - ደርሷል ከአርያም
ተመልከት ወደ ላይ - አንጋጥጥ በጥብቅ
አየህ በረከትክን አንተን ሲጠብቅ"
እያለ ይጮኻል - ከንቱ ወናፍ ላንቃ
ከመች ጀምሮ ነው
ጸሎት የሚቋረጥ ምስጋናስ ሚበቃ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል ረዳቴ - ዞርኩኝ ወደ ምስልህ
አሳቼን አየኹት ሲንፈራገጥ ከእግርህ

በስምህ ልዘክር - ካለኝ ላይ ቀንሼ
በደስታ እያበራኹ ከደጅህ ደርሼ
ስከፍት ሞሰቤን እጄን እያነቀ
በአዛኝ ከንፈሩ የፌዝ እየሳቀ
የኑሮን ውድነት እየዘረዘረ
"ገነት ለገባ ነፍስ - ጸድቆ ለበረረ
ገንዘብ የሚያባክን ምጽዋት ምን ሊበጅ?
ከሞት አያነቃ ህይወት አያደረጅ"
ይለኛል አስሬ እየዘጋ መንገድ
ከመቼ ወዲህ ነው
ምጽዋት ተለግሶ ውድቀት የሚታጨድ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል አጋዤ ምስልህን ስታቀፍ
ጠላቴን አየሁት ከመኖር ሲቀረፍ

ክብርህ ያልገባቸው ምልጃህን ሊያጎድፉ
ጥቅስ እያጣቀሱ ቃል ሲለፈልፉ
ላስረዳቸው ስጥር ገድልህን አንብቤ
እንድትገልጥላቸው ስጽልይ በልቤ
የኔን እየተው ሊጫኑኝ በጩኸት
አፋቸው ደጋግሞ በውድቀት ሲከፈት
መዳረቅን ሽሽት ስሄድ ጥያቼው
እየተዘባበቱ በጉድፍ ቃላቸው
መክሰሬን ሲገልጹ አንተን በማክበሬ
የፌዝ ሳቅ አንግቤ - ሳያቸው ዞሬ
"ሂድና በላቸው ጥርሳቸውን አርግፍ
እንዴት ዝም ትላለህ - ክብሬ ሲጎድፍ"
የሚል ቁጣ ትዕዛዝ - ገባ ወደ ዕዝኔ
መቼ ይሆን ደግሞ
ስላንተ መምታትን የተማርኩት እኔ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
አልመስልህ አለኝ እውን ያንተ ቃል
ለስምህ መሞት እንጂ - መግደል ያጸድቃል?
ሚካኤል አዳኜ
አወጣኹ ምስልህን - ኪሴ ውስጥ መዝዤ
አነቀኝ አንዳች ኃይል - ቀረኹኝ ፈዝዤ
ባጣ መታገያ አቅም - ወረደ እንባዬ
ብቻ ግን ደስ አለኝ - አልሳትኩም ተታልዬ

ልጅህን የማትተው በፈተና ቃርሚያ
አዳንከኝ ሚካኤል ልክ እንደ አፎሚያ

አሸን መሰናክል በጫንቃዬ አዝዬ
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት

#ኤልዳን

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
✴️ ✴️60 ሺ subscribers ያለው የቴሌግራም ቻናል መግዛት የሚፈልግ በ @buchula36 ላይ ያነጋግሩኝ ።📳📳
የፀጋው ግምጃ ቤት
@mgetem

ከፀጋ ቀንሶ ፤ ልጇ መድሀኒአለም
ከድንግል ማርያም ፤ ያስቀረባት የለም።
ለሚካኤል ምህረት ፤ ለገብርኤል ብሥራት
ሰፍሮ እንደሰጣቸው ፤ አላጎደለባት
የሰማይ ሀብት ሁሉ ፤ ለማርያም ተሰጣት።
አላት ልዩ ግርማ ፤ የሚወደድ ጠባይ
ከኪሩቤል እና ፤ ከሱራፌል በላይ።
የቅዱሳን ሁሉ ፤ የሐዋርያትም
ፀጋ ቢሰበሰብ ፤ ከማርያም አይበልጥም ።
ክብር የምታሰጥ ፤ የፀጋው ግምጃ ቤት
ለሰው ልጆች ሁሉ ፤ አርጓታል ተምሳሌት።
ለደናግል ቢሉ ፤ በአላማ ፅኑነት
ከእርሷ የተሻለ ፤ ማን አለ አብነት ።
ለወላጅም ቢሉ ፤ ከእርሷ ማነው በልጦስ
እናት ቢሉ እናት ፤ ያውም የክርስቶስ ።
ለጠቢባን ቢሉ ፤ እንደ እርሷ አዋቂ
ማን አለ መላእክን ፤ መርማሪ ጠያቂ።
እንደ አባ ጊዮርጊስ ፤ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም
የለመናት ዛሬም ፤
ከእርሷ የተጠጋ ፤
ፈልጎ አያጣም ፤ የእግዚአብሔርን ጸጋ።

አቤል ታደለ

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
ለአስተያየት : @abeltadele
አይደለም ገብታን
@Mgetem

ከእውቀት ባሻገር ፤ ከቃል ማብራሪያም
ዕፁብ ድንቅ ነው ፤ ነገረ ማርያም።
ቀለም ቢቀዳ ፤ ተጨልፎ ባህር
በየብስ ወረቀት ፤ በውሃ ብእር
አይበቃም ሥፍራ ፤ እስካለም አጽናፍ
ድንግልናዋ ብቻውን ቢፃፍ ።
የእርሷን ከፍታ ፤ የእርሷን ልዕልና
ቃል ሊሸከመው ፤ አይችልምና
ብንናገርም ፤ ገናንነቷን
ከፍቅር እንጂ ፤ አይደለም ገብታን።

✍️ አቤል ታደለ

https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
https://www.tgoop.com/Mgetem
ለአስተያየት : @abeltadele
2025/06/26 14:38:45
Back to Top
HTML Embed Code: