Telegram Web
Channel created
አቶ አብይ አህመድ ፣ በእርግጥ ጤነኛ ነውን?
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኦቦ ኤርሚያስ የቀደመ እናት ድርጅታቸው ኦህዴድ (በአዲስ ስሙ ኦሮሞ ብልፅግና) ጋር ግንኙነት አለኝ ይሉናል
እኛም ድሮም ስልጣን እና ገንዘብ ፍለጋ እንጂ የህዝብ ጥያቄን ወይም ችግር ለመፍታት እንዳልሆነ እናውቅ ነበር
" ለረጅም ግዜ ታግሰናል። ከዚህ በኋላ ግን ሁሉም ነገር በህግና ስርዓት መልክ እንዲይዝ እናደርጋለን " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰላምና የፀጥታ ቢሮ   

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰላምና የፀጥታ ቢሮ ፤ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

" በአሁኑ ሰዓት የክልሉ የፀጥታ ሃይል በተናበበና በተቀናጀ  አኳሃን በመስራት በቅርቡ ከሌላው ጊዜ የተሻለ የፀጥታ ሁኔታ እንዲኖር በመስራት ላይ እንገኛለን " ብሏል።

የህግ ልዕልና ማረጋገጥ እንዳለ ሆኖ በተለይ  ከብረታ ብረት ስርቆት ጋር ተያይዞ የተጀመረው ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደ መነሻ በመውሰድ በወርቅ ፣ ማዕድንና መሬት ዘረፋና እገታ እንዲሁም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ስርዓት የማስያዝ ስራዎችና እርምጃዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብሏል።

" የተጀመረው ህግ የማስከበር እንቅስቃሴ ያስደነገጣቸው ህገ-ወጥ  አካላት ጉዳዩ ፓለቲካዊ መልክ ሊያስይዙት እየሞከሩ ነው " ያለው ቢሮው " በማህበራዊ የትስስር ገፆች በሚነዛው በሬ ወለደ ውዥንብር ሳንደናገጥ ስራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን " ሲል አሳውቋል።

" ለረጅም ግዜ ታግሰናል ፤ ከዚህ በኋላ ግን ሁሉም ነገር በህግና ስርዓት መልክ እንዲይዝ እናደርጋለን " ሲል አረጋግጧል።

እስካሁን በተለያዩ ህገ-ወጥ ተግባሮች ተሳተፉ  ናቸው የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል።

እነማን እንደሆኑ በስም የተጠቀሰ ነገር የለም።

ሳምንቱን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ከትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን 3 ከፍተኛ አመራሮች ከሃላፊነት ተነስተው በሌሎች መተካታቸው ሲዘዋወር ነበር።

ከብረታ ብረት ስርቆትና ሌሎች ህገ-ወጥ ተግባራት ጋር በተያያዘም በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ቢነገርም መረጃውን የጊዚያዊ አስተዳደሩና የፀጥታና ሰላም ቢሮ ማረጋገጫ ሊሰጥበት አልቻለም።
በአዲስ አበባ ከተማ የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንደሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በከተማዋ በሚገኙ የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው፥ በ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,046 ተማሪዎች መካከል 80,198 ተማሪዎች ወይም 94.3 በመቶዎቹ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡

የተማሪ ወላጆች ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን የመለያ ቁጥር እና ስም በማስገባት ውጤት መመልከት ይችላሉ። ወይም ከስር የተቀመጠውን የቴሌግራም ቦት ይጠቀሙ፡፡

ውጤት ለማየት፦ https://aa6.ministry.et/#/result

በቴሌግራም ቦት፦ @emacs_ministry_result_qmt_bot
" ችግሩ ከአቅማችን በላይ ነው " - መሰቦ ሲሚንቶ

የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ፤ ለጊዜው ስሚንቶ ማምረት ማቆሙን አሳውቋል።

ፋብሪካው የሲሚንቶ ማምረት ስራ ያቆመው አጋጠመኝ ባለው " የጥሬ እቃ አቅርቦት እጥረት " ነው።

መሰቦ ፥ " ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሲሚንቶ ለማምረት የምንጠቀምባቸው ጥሬ እቃዎች በተለያዩ ጊዚያት በአግባቡና በወቅቱ ለማግኘት አልቻልንም " ብሏል።

" የተለያዩ ጥሬ እቃዎች ሚገኙባቸው ቦታዎች ከሚኖር ማህበረሰብ ጋር የተፈጠረው ችግር በጊዚያዊነት እና በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላትና የአከባቢው ነዋሪዎች በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም እስከ አሁን መፍታት አልተቻለም " ብሏል ፋብሪካው፡፡ 

እነዚህ ችግሮች ምን ምን እንደሆኑ በይፋ ከመናገር ተቆጥቧል።

" የተፈጠረው ችግር ከእኔ አቅም በላይ ነው " ያለው መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ችግሩን የሚመለከተው አካል ትኩረት ሰጥቶ መፍትሄ እስኪሰጠው ድረስ ለጊዜው ሙሉ በሙሉ ሲሚንቶ ማምረት አቁሞ በጥገና ስራ እንደሚገኝ አሳውቋል።
" በአሜሪካ ሁሉንም ጨዋታዎች ማሸነፍ እንፈልጋለን " ሌኒ ዮሮ

የማንችስተር ዩናይትድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ሌኒ ዮሮ በዛሬው የወዳጅነት ጨዋታ ባሳየው እንቅስቃሴ ደስተኛ መሆኑን ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" ዛሬ ባደረግኩት እንቅስቃሴ ደስተኛ ነኝ በዚህ እንደምቀጥል ተስፋ አደርጋለሁ " ያለው ሌኒ ዮሮ " የቡድኑ ስሜት ደስ ይላል እሮብ አሜሪካ ሄደን ሶስት ጨዋታዎች እናደርጋለን ፣ ሁሉንም ለማሸነፍ የቻልነውን እናደርጋለን " ብሏል።

ማንችስተር ዩናይትድ በአሜሪካ ቆይታው ከአርሰናል፣ ሪያል ቤቲስ እና ሊቨርፑል ጋር በተከታታይ የወዳጅነት ጨዋታዎች ያደርጋል።
2025/02/19 00:27:36
Back to Top
HTML Embed Code: