Telegram Web
ትምራን 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን አከበረች
ሴቶች ወደ ፖለቲካ ተሳትፎ እና አመራርነት እንዲመጡ የማስቻል ራእይ ሰንቃ በመጋቢት 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የምዝገባ ምስክር ወረቀት ያገኘችው ትምራን 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን በሳፋየር አዲስ ሆቴል ነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም አከበረች።
በክብረ በዓሉ ላይ የትምራን መሥራቾች፣ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት፣ ለጋሾች፣ ባለድርሻ አካላት፣ ጥሪ የደረገላቸው እንግዶች እና ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
በበዓሉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የትምራን ቦርድ ሰብሳቢ መስከረም ገስጥ፣ እንኳን አደረሳችኹ ያሉ ሲኾን ትምራን ቁጭት እና ቁርጠኝነት የወለዳት ድርጅት ነች ብለዋል። ይኽም ሴቶች የሚገባቸውን የፖለቲካ መድረክ እና ሕዝባዊ ተሳትፎ አለማግኘታቸው እና ወጥነት ባለው እና በተቀናጀ መልኩ ዕለት ከዕለት የሚሠራ አካል ባለመኖሩ መኾኑን ጠቅሰዋል።
የትምራን ምሥረታ ሐሳብን በማመንጨት ረገድ በዋናነት በሴቶች መብቶች ላይ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ የሚሠሩ በርካታ ተዋናዮች መኖራቸውንም አመልክተዋል። ቁርጠኝነቱ ይኽንን ትግል ሀገራዊ አድርጎ ለመንቀሳቀስ መደራጀት አስፈላጊ መኾኑ ነው ብለዋል። ትምራን ዕድሜዋ ትንሽ ቢኾንም ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጀምሮ እስከ ሀገራዊ ምክክር ድረስ ሴቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና መጫወቷን ገልጸዋል። በበዓሉ ላይ ኬር ከተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ትምራን በአምስት ዓመታት ውስጥ ባከናወነቻቸው ተግባራት ያሳደረችው በጎ ተፅዕኖ ጥናት ቀርቧል። የዚኽ ጥናት ውጤት በቀጣይ ስልታዊ እቅዷን ለመከለስ እገዛ ማድረጉ ተገልጿል።
ትምራን አቅም ግንባታ እና ቅስቀሳ፣ ጥናት፣ ምርምር እና ኅትመት፣ ውትወታ፣ ትስስር እና አጋርነት እንዲሁም ድጋፍ እና ከለላ የሚሉ አምስት ምሰሶዎችን ይዛ ትንቀሳቀሳለች። #TIMRAN@5
4
TIMRAN celebrated her 5th Year Anniversary
TIMRAN, marked her 5th year anniversary on September 03, 2025, at the Sapphire Addis Hotel.
The event was attended by TIMRAN's founders, General Assembly members, donors, stakeholders, invited guests, and her staff.
On her opening remark, the Chairwoman of TIMRAN Board, Meskerem Geset, welcomed the event attendees and said TIMRAN is the result of aspiration and commitment. She emphasized that women do not have the political platform and public participation they rightfully deserve, and that there was a lack of organization for long-term, that coordinate such efforts on a daily basis.
She also highlighted there are many CSOs working on women's rights in generating the idea of establishing a specific organization. The commitment was bringing this struggle in organized way. Despite her young age, TIMRAN significantly contributed to ensuring women's active participation from the 6th general election to the Ethiopian national dialogue cause.
TIMRAN operates based on five key pillars: capacity building and public education, research and publication, advocacy, networking and partnerships, and support and protection.
On the event, with the financial support of CARE, TIMRAN’s five years impact assessment result presented and the findings of this research have contributed to updating her current strategic plan.
TIMRAN received a certificate of registration from Authority of Civil Society Organizations (ACSO) in March 2020 with the aim of empowering women to engage in politics and leadership.
#TIMRAN@5
5
መልካም 1500ኛ ዓመት የመውሊድ በዓል!
Joyful 1500th Year Mawlid Celebration!
#TIMRAN@5
2
Forwarded from ELiDA Ethiopia (Amen 🦋)
Call for Membership Women Peacebuilders and Rights Defenders (Tigray)

ELiDA is establishing a Regional Network of Women Peacebuilders and Rights Defenders in Tigray to promote women’s leadership and participation in peacebuilding and conflict resolution processes.

We invite women interested in joining the network to apply through this link-

https://bit.ly/RNWPBT

Deadline: September 9, 2025
ትምራን ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችኹ እያለች አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት እንደ መሆኑ መጠን ኢትዮጵያውያን ሴቶች እኩል የፖለቲካ እና የውሳኔ ሰጭነት እድል የሚያገኙበት እንዲሆን ትመኛለች።

TIMRAN wishes to all Ethiopians a HAPPY NEW YEAR.
As the New Year symbolizes fresh hope, she aspires for Ethiopian women to have equal opportunities in political and decision-making roles.
#TIMRAN@5
2
2025/09/16 04:15:57
Back to Top
HTML Embed Code: