Forwarded from ቸርነት
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 22 ፥ 1 - 23
መልካም ዕለተ ሰንበት
ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 22 ፥ 1 - 23
መልካም ዕለተ ሰንበት
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 12 ፥ 20 - 26
መልካም ዕለተ ሠሉስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #tuesday
ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 12 ፥ 20 - 26
መልካም ዕለተ ሠሉስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #tuesday
❤5
††† ✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!✝ †††
††† ✝እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ✝ †††
††† ✝ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ✝ †††
=>ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
+የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::
+ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::
+የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
=>መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
+የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
+በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
+በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
+እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
+የጌታችንን መንገድ የጠረገ
+ጌታውን ያጠመቀና
+ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
††† ✝እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ✝ †††
††† ✝ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ✝ †††
=>ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
+የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::
+ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::
+የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
=>መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
+የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
+በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
+በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
+እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
+የጌታችንን መንገድ የጠረገ
+ጌታውን ያጠመቀና
+ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
+ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች::
❤1
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ ።
+++
ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።
ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።
የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እነሆ ብሎ ኢሳይያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለሱ እንዲህ አለ። በፊትህ ጐዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልእክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ።
ራሱ መድኃኒታችንም ስለርሱ ሲናገር ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም ብሏል። ይህ የእግዚአብሔርን ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።
ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት ጸሎት መንፈሳውያን በሆኑ በቅዱሳን መላእክትም አማላጅነት ይልቁንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷና በአማላጅነቷ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን።
+++
ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።
ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።
የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እነሆ ብሎ ኢሳይያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለሱ እንዲህ አለ። በፊትህ ጐዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልእክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ።
ራሱ መድኃኒታችንም ስለርሱ ሲናገር ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም ብሏል። ይህ የእግዚአብሔርን ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።
ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት ጸሎት መንፈሳውያን በሆኑ በቅዱሳን መላእክትም አማላጅነት ይልቁንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷና በአማላጅነቷ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን።
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 19 - ፍጻሜ
መልካም ዕለተ ሠሉስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #tuesday
ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 19 - ፍጻሜ
መልካም ዕለተ ሠሉስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #tuesday
❤1
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 18 ፥ 15 - 21
መልካም ዕለተ ሐሙስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #thursday
ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 18 ፥ 15 - 21
መልካም ዕለተ ሐሙስ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #thursday
የሐምሌ ወር ሐመር #መጽሔት #በውስጧ ምን ይዛለች ?
የሐምሌ ወር ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን "#የተሰጠህን አደራ #ጠብቅ ›› በሚል ግቢ ጉባኤያትን በተመለከተ አደራን ስለመወጣት በመልእክቱ ዐምዱ ይዛለች።
.#ዐውደ ስብከት ሥር #ክርስቶስን ደቀመዛሙርት እከተላቸው ዘንድ ፍቅረ እግዚአብሔር ያስገድደኛል"
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር "ሐዋርያው #ቅዱስ ጴጥሮስ "በሚል ርእስ ትውልዱእና እድገቱ ፣የቅዱስ ጴጥሮስ መጠራት ሰፊ ትምህርት ያስጨብጣል። #በመልአከ ሰላም ቀሲስ #ደጀኔ ሺፈራው የተዘጋጀ ግሩም ጹሑፍ ትምህርተ ሃይማኖት ይዛለች።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# ዛሬ ሳንሠራ ቀርተን ነገን እንዳንቸገር ልዩ ትኩረት ለግቢ ጉባኤያት " በሚል ርእስ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ፣የመምህራን ችግር፣የቋንቋ ጉዳይ ፣የየዮኒቨርቲዎች የትምህርት የጊዜ ሠሌዳ፣ሀገሪቱ ያለችበት የጸጥታ ችግር ፣እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ፣መፍትሔ ከማን ምን ይጠበቃል ? የሚሉትን መሠረታዊ ጉዳዩች ይዟል።
"#ክርስትና በማኀበራዊ ኑሮ፦ #ኦርቶዶክሳውያን በማኅበረሰብ ውስጥ ቦታችን የት ነው _ክፍል _፫" በሚል ርእሰ #በጎ አድራጎት እና ኦርቶዶክሳውያን ምንና ምን ናቸው ? በማለት በጎ ማድረግ ዘርፈ ብዙ መሆኑን ያሳያል ።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ "በሚል ርእስ የስሙ ትርጓሜ፣ልደቱና እድገቱ፣የትምህርት ሕይወቱ የሹመት ዘመኑ፣ማስተማር ሕይወቱን በተመለከተ ፣የቅዱስ ቄርሎስ ሥራዎች፣መዓርገ ቅድስና በማንሳት ስለ ቅዱሱ ሰፊ ትምህርት ይሰጣል ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ክርስቲያናዊ ሕይወትን በዕቅድ መምራት "በሚል ጥሩ ነገር ታስነብባለች።
የሐምሌ ወር ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን "#የተሰጠህን አደራ #ጠብቅ ›› በሚል ግቢ ጉባኤያትን በተመለከተ አደራን ስለመወጣት በመልእክቱ ዐምዱ ይዛለች።
.#ዐውደ ስብከት ሥር #ክርስቶስን ደቀመዛሙርት እከተላቸው ዘንድ ፍቅረ እግዚአብሔር ያስገድደኛል"
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር "ሐዋርያው #ቅዱስ ጴጥሮስ "በሚል ርእስ ትውልዱእና እድገቱ ፣የቅዱስ ጴጥሮስ መጠራት ሰፊ ትምህርት ያስጨብጣል። #በመልአከ ሰላም ቀሲስ #ደጀኔ ሺፈራው የተዘጋጀ ግሩም ጹሑፍ ትምህርተ ሃይማኖት ይዛለች።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# ዛሬ ሳንሠራ ቀርተን ነገን እንዳንቸገር ልዩ ትኩረት ለግቢ ጉባኤያት " በሚል ርእስ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ፣የመምህራን ችግር፣የቋንቋ ጉዳይ ፣የየዮኒቨርቲዎች የትምህርት የጊዜ ሠሌዳ፣ሀገሪቱ ያለችበት የጸጥታ ችግር ፣እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ፣መፍትሔ ከማን ምን ይጠበቃል ? የሚሉትን መሠረታዊ ጉዳዩች ይዟል።
"#ክርስትና በማኀበራዊ ኑሮ፦ #ኦርቶዶክሳውያን በማኅበረሰብ ውስጥ ቦታችን የት ነው _ክፍል _፫" በሚል ርእሰ #በጎ አድራጎት እና ኦርቶዶክሳውያን ምንና ምን ናቸው ? በማለት በጎ ማድረግ ዘርፈ ብዙ መሆኑን ያሳያል ።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ "በሚል ርእስ የስሙ ትርጓሜ፣ልደቱና እድገቱ፣የትምህርት ሕይወቱ የሹመት ዘመኑ፣ማስተማር ሕይወቱን በተመለከተ ፣የቅዱስ ቄርሎስ ሥራዎች፣መዓርገ ቅድስና በማንሳት ስለ ቅዱሱ ሰፊ ትምህርት ይሰጣል ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ክርስቲያናዊ ሕይወትን በዕቅድ መምራት "በሚል ጥሩ ነገር ታስነብባለች።
❤2
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 21 ፥ 33 - ፍጻሜ
መልካም ዕለተ አርብ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #friday
ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 21 ፥ 33 - ፍጻሜ
መልካም ዕለተ አርብ !
#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter #friday
🥰1