Telegram Web
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
- ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ
የሰሜን ጎጃምና የባሕር ዳር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
- ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
እግዚአብሔር አምላካችን በቤተ ክርስቲያን ላይ በየጊዜው የሚደርሰውን ፈተና በማስቻል ለዚህ ሲኖዶሳዊ ምልአተ ጉባኤ እንኳን በሰላም አደረሰን!

‹‹አስተብቊዓክሙ አኃዊነ በስሙ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትበሉ ኵልክሙ አሐደ ቃለ ወአሐደ ነገረ ወትኩኑ ፍጹማነ ወኢትትፋለጡ ወሀልዉ በአሐዱ ምክር ወበአሐዱ ልብ፤ ወንድሞች ሆይ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ፣ በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ›› (፩ቆሮ ፩፥፲)፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን መልእክት ለቆሮንቶስ ሰዎች ለመጻፍ ሲያስብ አንድ ዓቢይ ምክንያት እንዳለው ከመልእክቱ ይዘት መረዳት ይቻላል፤ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች አንድነትንና ሰላምን ፍቅርንና መተባበርን ከምትሰብከው ወንጌለ መንግሥተ እግዚአብሔር ወጥተው ብዙ ርቀት ሂደዋል፤ አንድነቱ፣ ኅብረቱ መረዳዳቱ መተጋገዙና መተባበሩ ከመካከላቸው ጠፍቶአል፤ ሌላው ቀርቶ ቅዱስ ቊርባንን ለመቀበል በሚሰበሰቡበት ጊዜ እንኳ የሀብታምና የድሀ የሚል ክፍፍል ተፈጥሮ ቤተ ክርስቲያኗን አደጋ ላይ ጥሎአል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን እና ይህንን የመሳሰለ ፈተና በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ሥር እየሰደደ መምጣቱን በእጅጉ አሳስቦታል፤ ይህ የሰላምና የአንድነት ጠንቅ የሆነው የመለያየት አዝማሚያ በጣም ሰፍቶ ቤተ ክርስቲያንን ከማፍረሱ በፊት በትምህርት በምክርና በተግሣጽ ማረም እንዳለበት ቅዱስ ጳውሎስ ተገንዝቦአል፤ እሱ ራሱም በአካል በመካከላቸው ተገኝቶ ሊያስተካክላቸው ፈቃደኛ ነበረ፤ ነገር ግን እሱ በዚህ ጊዜ በሮም ውስጥ እስር ቤት ላይ ስለነበረ አልቻለም፤ የነበረው አማራጭ በጽሑፍ ማስተማርና መምከር ነውና፤ ይህንን መልእክት ጽፎላቸዋል፡፡

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዘላቂው የቤተ ክርስቲያን ፈተና ሲነግረን ‹‹ወበዓለምሰ ሀለወክሙ ትርከቡ ሕማመ፤ በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ›› እንዳለው ቤተ ክርስቲያን ከፈተና ተለይታ አታውቅም፤ ፈተናውም ከተወሰነ አቅጣጫ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከብዙ አቅጣጫ ይከባታል፤ የቤተ ክርስቲያን መከራ ከውጭ ብቻም አይደለም ከውስጥም እንጂ፤ ከባዕድ ብቻም አይደለም ከወዳጅም እንጂ፣ የወዳጅ ፈታኝ እንደሚብስም ታውቆ ያደረ ነገር ነው፤ ባዕዳውያን አይሁድ ጌታን ይዘው የገደሉ የውስጥ ሰው የሆነው ይሁዳ በሰጣቸው ምልክት ነው፡፡
ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ በከባድ ፈተና ውስጥ እያለፈች ትገኛለች፤ እንደተነገረው የውጭው ፈተና ባይቀርላትም ከሱ በላይ ግን በውስጧ የሚነሡ ፈተናዎች ተልእኮዋን በአግባቡ እንዳትወጣ ዕንቅፋት ሆነውባታል፤ ከጥንት ጀምሮ የነበረ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ፣ የጸሊአ ሢመትና የጸሊአ ንዋይ መንፈሳዊ ባህሏ ተዘንግቶአል፤ በምትኩም ፍቅረ ሢመትና ፍቅረ ንዋይ ነግሦአል፤ መለያየትና መነቃቀፍ እየሰፉ መጥተዋል፣ ሃይማኖታችንንና ባህላችንን የማይወክሉ ኃይለ ቃላት፣ ኃላፊነት በጐደለው አገላለጽ እየተሰነዘሩ በጎቻችንን አስበርግገዋል፤ ድርጊቶቹ በበጎቻችን ዘንድ የነበረንን ተሰሚነትና ተደማጭነት ሊቀንሱብን እየተንደረደሩ ነው፡፡
እነዚህና እነዚህ የመሳሰሉ ክሥተቶች በውስጣችን ሥር በሰደዱ ቁጥር ጉዳትን እያስከተሉ ነው፤ ሰዎች ከኦርቶዶክሳዊ ቀኖና እና ሥርዓት ባፈነገጠ መልኩ ራስን በራስ የመሾም አባዜ እየተለማመዱ ነው፤ እሽቅድምድሙም በዚህ ዙሪያ አይሎአል፤ በአጠቃላይ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖችን የፈተነ መለያየት በቤተ ክርስቲያናችንም ብቅ ጥልቅ እያለ እየፈተነን ነው፤ የፈተናው መንሥኤ ውጫዊ ሳንካ ባይጠፋበትም የውስጣችን ሰዎች ለሱ ምቹ ሆነው መገኘታቸው አልቀረም፤ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ፈተና የማይናቅ ጉዳት እየደረሰባት ነው፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ ሰላምዋና አንድነቷ ጥያቄ ላይ ወድቆአል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በሀብተ መንፈስ ቅዱስ ወልደን፣ በሀብተ ክህነት ሹመን፣ በመዐርገ ምንኩስና አልቀን በቤተ ክርስቲያን ኃላፊነት ያስቀመጥናቸው ሰዎች በውኑ ‹‹እርስ በርስዋ የምትለያይ ቤት… የሚለውን አምላካዊ አስተምህሮ እንዴት ዘነጉት? ወይስ ድሮውንም ሳያውቁት ነው ኃላፊነቱ የተሰጣቸው? ወይስ ደግሞ ሆን ብለው ቃሉን ቸል ብለውታል? ሁሉም ውሉደ ክህነት ለዚህ መልስ መስጠት ይጠበቅበታል፤ በመልካም አስተዳደርና በቂም በቀል እያሳበቡ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ብሎም ለማፍረስ መሮጥ በማናቸውም መመዘኛ ሚዛን አይደፋም፤ ውሃም አያነሣም፡፡
ችግር ሲኖር በመወያየት በጥበብና በሕግ ማረም እንጂ የጋራ ችግርን ለተወሰነ አካል በመለጠፍና እሱን ብቻ ተጠያቂ በማድረግ ንጹህ መሆን አይቻልም፤ ሁሉም ጓዳው ቢፈተሽ ከዚህ የተለየ ነገር አይገኝም፤ አንድነትንና ሰላምን ግቡ ያደረገ ግምገማን መገምገም፣ መወያየትና መመካከር፣ ሕግንና ሥርዓትን ማእከል አድርጎ መሥራት ተመራጭ መፍትሔ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ባለፉት ዓመታት አስከፊ በደል ተፈጽሞአል አሁንም አልቆመም፤ ይሁን እንጂ በደል ዛሬ ብቻ የተጀመረ አድርገን አናስብ፤ ይብዛም ይነስ በደል ፊትም ነበረ፤ ዛሬም አለ፤ ነገም የተለየ ነገር ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፡፡
በደልን በካሣና በዕርቅ በይቅርታና በምሕረት መዝጋት፣ ተመሳሳይ በደል እንዳይፈጸም አስተማማኝ የሆነ ተቅዋማዊ ሥርዓትን ማበጀት መልካም ፈሊጥ ይሆናል፤ በደልንና ጥፋትን ምክንያት አድርገን እስከ ዘለቄታው መለያየትን መምረጥ ግን ራስን በራስ መጉዳት ይሆናል፤ ስለዚህ ይህ ቅዱስ ጉባኤ በዚህ ዙሪያ በስፋትና በጥልቀት በመወያየት ሁሉንም ሊያስማማ በሚችል መልኩ ወደ ሰላምና ዕርቅ ሊያደርስ የሚችል ስራ መስራት ይኖርበታል፡፡
ብፀዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖስ አባላት!
የማኅበረ ሰባችን ችግር በቤተ ክርስቲያን ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ በሀገር ደረጃ እየቀጠለ ያለው አለመግባባትም ለጠቅላላ ማኅበረ ሰባችን ፈተና ከሆነ ውሎ አድሮአል፤ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተና ምንጭ ከሆኑትም አንዱና ዕድል ሰጩ ይህ ሀገራዊ አለመግባባት ነው፤ በዚህ አለመግባባት ምክንያት ገዳማውያን መነኮሳት፤ መምህራን ካህናት ምእመናን አብያተ ክርስቲያናት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ በሰላም ወጥቶ መግባትም አጠራጣሪ ሆኖአል፤ ይህንን ችግር ለመፍታት የሚደረግ ጥረትም ጎልቶ አይታይም፡፡
በመሆኑም ይህ ክሥተት እውን ኢትዮጵያውያን የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት የማንችል ሰዎች ነን ወይ? ለኛስ ከኛ የበለጠ ማን ይመጣልናል? የሚለውን ጥያቄ ልናነሣ ግድ ነው፤ ስለዚህ ለሀገር ህልውናና ድኅነት የሚበጅ ነገር እንዲመጣ ቤተ ክርስቲያን ባላት ሃይማኖታዊና ሰብአዊ ኃላፊነት ጠንክራ መስራት ይጠበቅባታል፤ ከዚህ በተረፈ ይህ ዓቢይ ጉባኤ ወሳኝና ወቅታዊ እንዲሁም ሐዋርያዊና ቀኖናዊ በሆኑ የቤተ ክርስቲያናችን ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር የሚበጁ ነገሮችን በማየት ጠቃሚ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፍ በዚህ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡

በመጨረሻም
ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በእግዚአብሔር ፈቃድ የተጀመረ መሆኑን በመንፈስ ቅዱስ ስም እናበስራለን ፡፡

መልካም ጉባኤ ያደርግልን!
እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት ፳፩ ቀን !፻0፮ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

©️DEWOLደወል ሚዲያ

@Tinsae_ze_ethiopia
ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ
Photo
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፱፲ወ፮ ዓ/ም ባደረገው የጠዋቱ የግንቦት ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ሰባት አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በመወያያ አጀንዳ አርቃቂነት ሰየመ።
በዚሁም መሰረት በመወያያ አጀንዳ አርቃቂነት የተሰየሙት ሰባት አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሕገ ቤተ ክርስቲያን በሚያዘው መሰረት ከቋሚ ሲኖዶስ ለምልአተ ጉባኤ እንዲቀርቡ የተመሩ እና ተጨማሪ የሚባሉ አጀንዳዎችን በመቅረጽ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የማስጸደቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴነት የተመረጡት አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚከተሉት ናቸው።

1.ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
3.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ
4. ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ
5. ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል
6. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ
7. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል

ኢኦቴቤ ሕዝብ ግንኙነት

©️Dewol

@Tinsae_ze_ethiopia
👉በዚሁም መሰረት በመወያያ አጀንዳ አርቃቂነት በጉባኤው የተመረጡት ሰባት አበው ሊቃነ ጳጳሳት
ሲኖዶሱ እንዲወያይበት 21 አጀንዳዎችን የመረጡ ሲሆን ይህም ዝርዝሩ እንደሚከተለው ይቀርባል ፦

1.የቅዱስ ሲኖዶስ ዓመታዊ የሥራ ክንውንን በተመለከተ

2.የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማትን አስመልክቶ ከቤትና ሕንጻ አስተዳደርና ልማት ድርጅት የቀረበ ሪፖርት በተመለከተ

3.የሃይማኖት ረቂቅ አዋጅ በተመለከተ

4.የገቢዎች ባለሥልጣን የወሰነውን የግብር አከፋፈል ሁኔታ በተመለከተ

5.አገር አቀፍ የምክክር ኮሚሽንን በተመለከተ

6.ወደ ውጭ ሀገር ለአገልግሎት የሚላኩ አገልጋዮችን በተመለከተ

7.የ2017ዓ.ም በጀት ማጽደቅን በተመለከተ

8.የስዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅን በተመለከተ

9.የምግባረ ሠናይ ጠቅላላ ሆስፒታል ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ በተመለከተ

10.የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አንድነት ገዳም ኅብረት መተዳደሪያ ደንብ በተመለከተ

11. የጋሞጎፋ ሀገረ ስብከት ተብሎ የሚጠራበት ስም ቀርቶ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረስብከት አርባ ምንጭ ተብሎ ይጠራልኝ በማለት የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ

12.የጋምና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ስለ ዚጊቲ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ

13 ኦሲኤን ቴሌቭዥን አስመልክቶ የቀረበ ጥናት በተመለከተ

14.የብፁዓን አባቶች ዝውውር ጥያቄ በተመለከተ

15. የእነ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ማመልከቻን በተመለከት

16 ከመሪ እቅድ የሚቀርበውን ዝርዝር የመዋቅር ጥናትና ቻርት በተመለከተ

17.የመግለጫ አሰጣጥ እና የስብከት ዘዴ ትምህርት አቀራረብን በተመለከተ፣

18.አገራዊ ሰላምን በተመለከተ

19. የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ግበረ ሰዶማዊነትን በተመለከተ '

20 የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና የውስጥ አንድነትን ማጠናከር በተመለከተ

21.የቋሚ ሲኖዶስ አባላት ምርጫን በተመለከተ

©️ETHIO BETESEB MEDIA

@Tinsae_ze_ethiopia
ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ
Photo
በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን፣ የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት በሰጠው መግለጫ "የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ላይ ውግዘትም ሆነ በቦታቸው ሌላ አባት የመተካት ውሳኔ እንዳይተላለፍ አጥብቆ ጠየቀ። እንዲህ ያለ ውሳኔ ከተላለፈም እንደማይቀበለው አስታወቀ።
©️Adebabay media

@Tinsae_ze_ethiopia
መረጃ የአቡነ ጴጥሮስ ጉዳይ

(ግንቦት 26/ 2016 ዓ.ም ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ)

የአቡነ ጴጥሮስን ጉዳይ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶሱ ዛሬ ዉዉይት ያደረገ ሲሆን በዚህ መሠረት ፦ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣
አቡነ አብርሃም ፣ አቡነ ኤርምያስ ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ
፣ አቡነ ሳዊሮስ ፣ አቡነ ሄኖክ ፣ አቡነ ናትናኤል ዘሚኔንሶታ በመሆን መንግስትን እንዲያናግሩ፣ችግሩ እንዲፈታና ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ ዛሬ ወስኗል ፣ ይሳካ ይሆን እሱን የምናየው ነው ዝርዝር መረጃውን በመደበኛ ፕሮግራማችን ይጠብቁን

©️ETHIO BETESEB MEDIA
@tinsae_ze_ethiopia
ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ
Photo
የኦሮሞ ህዝብን በቋንቋው ያገልግሉ ተብለው የተሾሙ ጳጳሳት ለምን ከኦሮሚያ መውጣትን መረጡ?
...
ቤተክርስቲያንና ምዕመናኖቿ በሀዘን ጥቁር የለበስንበትን ጊዜ መቼም ከሰው ሁሉ ህሊና የማይዘነጋ ነው። ከሳሾች ቤተክርስቲያንን ለመክፈል እንደምክንያት የተጠቀሙበት ''በቂ የኦሮሞ ጳጳሳት የሉም'' የሚል አንዱ ነበር። ቤተክርስቲያን ምንም እንኳን ዘርና ነገድን መሰረት አድርጋ ባትሾምም ፤ ብትሾም እንኳን ፈቃደ እግዚአብሔር እንደማይኖርበትና ስራቸው ሁሉ እንደማይከናወንላቸው ብትረዳም ፥ የተጠየቀውን ጥያቄ ለመመለስ ቀድሞ ከነበሩት ጳጳሳት በተጨማሪ 7 Afaan Oromoo ተናጋሪ ጳጳሳትን ሾማ ኦሮሚያ ክልል ባሉ ሀገረ-ስብከቶች መደበች።
...
ባለፈውን አንድ ዓመት ብቻ 5 Afaan Oromoo ተናጋሪ ጳጳሳት ከተመደቡበት ኦሮሚያ ክልል እየለቀቁ ወጡ።

4ቱ ጳጳሳት ከተመደቡበት የወለጋ ዞኖች ነው ጥለው ወደ ሌላ ክልል መድቡን ብለው የለቀቁት ኦሮሚያ ክልልን። ልብ በሉ በብሄር ከኦሮሞ ማህበረሰብ የወጡ፣ በቋንቋ Afaan Oromoo ተናጋሪዎች፣ ምክንያተ ሹመታቸውም ቤተክርስቲያን ለኦሮሚያ ክልል በቂ ኦሮሞ ጳጳሳትን አልሾመችም የሚል ነበር።

በተሾሙ በዓመታቸው የተሾሙበት ሀገረ ስብከትና፣ የተሾሙበትን ምክንያት ሳይዘነጉ የኦሮሞን ህዝብ ጥለው ደቡብ፣ አፋርና አማራ ክልል መድቡን ብለው ለቀው ወጡ። 5ኛው አባት ከሀገር ጥለው ባህርማዶ ሄደዋል።
ይሄ ሁሉ ለምን?
1- ኦሮሚያ ክልል ባለው ኦርቶዶክሳዊያን ላይ ባነጣጠረው ተከታታይ ጥቃት ስጋት ምክንያት
2- ፖለቲካዊ ጫና ምክንያት
3- ለቀጣይ ዙር የቤተክርስቲያን ፈተና
4- ከዘርና ከብሄር ዝቅ ብሎ ያለው ጎጠኝነት?

ከላይ ከተዘረዘሩት ከ4ቱ ሶስቱን እርግጠኛ መሆን ይቻላል። አሁን በነዚህ ከኦሮሚያ ክልል እየጣሉ በወጡ የAfaan Oromoo ተናጋሪ ጳጳሳት ምክንያት 5 ሀገረ ስብከቶች በተደራቢነት ለሌላ ጳጳስ ተሰጥተዋል። ነገ በዚህ ደግሞ ቤተክርስቲያንን በሚጠሉና ሊያፈርሷት በሚሹ ዘረኞች ስትከሰስበት የምናየው ጉዳይ ነው። ለአንድ አባት ይሄ ሁሉ ሀገረ ስብከት ለምን ተደርቦ ተሰጠ የሚል ጥያቄ ይነሳል ምክንያቱ ሁለት ነው፤ አንደኛው በኦሮሚያ ክልል ኦሮሚኛ ቢናገሩ እንኳን ከኦሮሞ ብሄር ውጪ እንዳይሾሙ በሚለው ፖለቲካዊ ጫና ፣ ሁለተኛው ያሉት የኦሮሞ ጳጳሳትም ቢሆን ምዕራብ ኦሮሚያ በተለይም የወለጋና የሁሩ ጉዱሮ ሀገረስብከቶችን መምራት አንፈልግም ማለታቸው ነው።
©️Maramawit Henok

@tinsae_ze_ethiopia
2024/07/01 03:02:00
Back to Top
HTML Embed Code: