ሰላም የቻናላችን ተከታታዮች። እናንተን ላለመሰልቸት ፕሮሞሽን ብዙም አንሠራም ። ለእናንተ ደግሞ አንድ ኃላፊነት ልስጣችሁ ቢያንስ ለአንድ ሰው ሊንካችንን ላኩ ሰው ገብቶ እንዲማር ኃላፊነትን ይወጡ
Https://www.tgoop.com/venisiya21
Https://www.tgoop.com/venisiya21
Telegram
ቬኒሲያ
ተወዳጇ ቬኒሲያ በአዲስ መልክ ጀምራለች። ይህ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖታችንን አስተምህሮ በጣፋጭ ታሪኮች እያዋዛ የሚያቀርብ መንፈሳዊ ቻናል ነው
ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ
https://www.tgoop.com/Get_loza ያድርሱን።
ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ
https://www.tgoop.com/Get_loza ያድርሱን።
"የተሰረቀ ሞት"
🍇🍇🍇🍇🍇🍇
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አባ መርትያኖስ የተባለ በምግባር በሃይማኖቱ፣ በትሩፋት በተጋድሎው የተመሰገነ ታላቅ ጻድቅ በመንገድ ሲሔድ አንድ ሰው ሞቶ ሊቀብሩት
ሲወስዱት አየ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐመፀኛ ሰው በዚያ በሞተው ሰው ላይ ሐሰት በመናገር ‹‹ከዚህ ሰው ጋር አራት መቶ የወርቅ ዲናር አለኝ›› በማለት አላስቀብርም ብሎ
አወከ፡፡
አባ መርትያኖስም የሞተውን በሰላም ይቀብሩት ዘንድ ያን ዐመፀኛ ቢለምኑት ዳግመኛ አላስቀብርም ብሎ እምቢ አላቸው፡፡ ከዚኽም በኋላ አባ መርትያኖስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩ በማለዱ ጊዜ ያ የሞተው ሰው ተነሥቶ የማንም ሰው ምንም ዓይነት ዕዳ እንደሌለበት ተናገረ፡፡
ከዚኽም በኋላ አባ መርትያኖስ ያንን ዐመፀኛ በሰው ሁሉ ፊት ‹‹ለምን በሐሰት ተናገርክ? የተሰወረውን የሚያውቅ እግዚአብሔርን አትፈራምን?›› አሉት፡፡ በዚያም ጊዜ ያ ዐመፀኛ ፈጥኖ ሞተ፣ ከሞት የተነሣው ሰው ግን በሰላም ወደቤቱ ተመልሶ ሔደ፡፡
ይህንንም ያዩ ሁሉ በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ድንቅ ድንቅ ነገርን የሚያደርግ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ አባ መርትያኖስም መላ ዘመኑን በታላቅ ተጋድሎ እግዚአብሔርን ሲያገለግል ኖሮ በሰላም ዐረፈ፡፡
ክፉዎችና በደለኞች የሌላውንም ሰው ሞት የሚሰርቁበት አጋጣሚ ብዙ ነው!!!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
🍇🍇🍇🍇🍇🍇
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አባ መርትያኖስ የተባለ በምግባር በሃይማኖቱ፣ በትሩፋት በተጋድሎው የተመሰገነ ታላቅ ጻድቅ በመንገድ ሲሔድ አንድ ሰው ሞቶ ሊቀብሩት
ሲወስዱት አየ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐመፀኛ ሰው በዚያ በሞተው ሰው ላይ ሐሰት በመናገር ‹‹ከዚህ ሰው ጋር አራት መቶ የወርቅ ዲናር አለኝ›› በማለት አላስቀብርም ብሎ
አወከ፡፡
አባ መርትያኖስም የሞተውን በሰላም ይቀብሩት ዘንድ ያን ዐመፀኛ ቢለምኑት ዳግመኛ አላስቀብርም ብሎ እምቢ አላቸው፡፡ ከዚኽም በኋላ አባ መርትያኖስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩ በማለዱ ጊዜ ያ የሞተው ሰው ተነሥቶ የማንም ሰው ምንም ዓይነት ዕዳ እንደሌለበት ተናገረ፡፡
ከዚኽም በኋላ አባ መርትያኖስ ያንን ዐመፀኛ በሰው ሁሉ ፊት ‹‹ለምን በሐሰት ተናገርክ? የተሰወረውን የሚያውቅ እግዚአብሔርን አትፈራምን?›› አሉት፡፡ በዚያም ጊዜ ያ ዐመፀኛ ፈጥኖ ሞተ፣ ከሞት የተነሣው ሰው ግን በሰላም ወደቤቱ ተመልሶ ሔደ፡፡
ይህንንም ያዩ ሁሉ በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ድንቅ ድንቅ ነገርን የሚያደርግ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ አባ መርትያኖስም መላ ዘመኑን በታላቅ ተጋድሎ እግዚአብሔርን ሲያገለግል ኖሮ በሰላም ዐረፈ፡፡
ክፉዎችና በደለኞች የሌላውንም ሰው ሞት የሚሰርቁበት አጋጣሚ ብዙ ነው!!!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
☦☦☦☦☦☦☦☦☦
አንድ ጎልማሳ ሰው እለት እለት ወደ ቤተክርስቲያን እየሄደ እግዚአብሔርን ወርቅ ስጠኝ እያለ ይለምነዋል በዚህ ተግባሩም ሰነበተ.........
:: እግዚአብሔርም ተገልጾ ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ ይለዋል
:ሰውየውም የምነካው ሁሉ ወርቅ ይሁንልኝ ይለዋል.....
:እግዚአብሔርም እንዳልክ ይሁንልህ ብሎ ይሰወራል
:በዚህ የተደሰተው ሰውዬ መንገድ ላይ ያገኘውን ነገር ሁሉ ወርቅ እያደረገ ለባለቤቱ እስኪነግራት እየተቻኮለ በፍጥነት ወደ ቤቱ ገሰገሰ።
: እቤቱም እንደደረሰ ባለቤቱን ጠርቶ "የእኔ ውድ እያለ የቤቱን እቃ በሙሉ እየነካ ወርቅ አደረገው። ባለቤቱም በመደሰት ምግብ ታቀርባለች እሱ ግን ገና ምግቡን ሲነካው ወርቅ በመሆኑ እሷ እያጎረሰችው መመገብ ጀመሩ
: እሱም ወደ መጥገቡ ሲደርስ በቃኝ የእኔ ውድ ይላታል እሷም እንዴ በዛሬ ቀን ያልተበላ መች ሊበላ ነው እያለች በላይ በላይ ስታጎርሰው "ውይ በቃኝ" ብሎ እጇን ሲይዛት ወርቅ ሆነች.......
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.ወይኔ ብሎ ራሱን ሲይዝ ......😊😊 ወርቅ ሆኖ አረፈው
💮💮💮💮💮💮💮💮💮💮
ጌታችን "የምትለምኑትን አታውቁምን?" ያለው ይህን ነው እኛም ክርስቲያኖች አስቀድመን ጽድቁን እና መንግስቱን ነው ልንሻ ሚያስፈልገን ሌላው ትርፍ ነው .....
🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐
@venisiya21 @venisiya21
✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝
አንድ ጎልማሳ ሰው እለት እለት ወደ ቤተክርስቲያን እየሄደ እግዚአብሔርን ወርቅ ስጠኝ እያለ ይለምነዋል በዚህ ተግባሩም ሰነበተ.........
:: እግዚአብሔርም ተገልጾ ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ ይለዋል
:ሰውየውም የምነካው ሁሉ ወርቅ ይሁንልኝ ይለዋል.....
:እግዚአብሔርም እንዳልክ ይሁንልህ ብሎ ይሰወራል
:በዚህ የተደሰተው ሰውዬ መንገድ ላይ ያገኘውን ነገር ሁሉ ወርቅ እያደረገ ለባለቤቱ እስኪነግራት እየተቻኮለ በፍጥነት ወደ ቤቱ ገሰገሰ።
: እቤቱም እንደደረሰ ባለቤቱን ጠርቶ "የእኔ ውድ እያለ የቤቱን እቃ በሙሉ እየነካ ወርቅ አደረገው። ባለቤቱም በመደሰት ምግብ ታቀርባለች እሱ ግን ገና ምግቡን ሲነካው ወርቅ በመሆኑ እሷ እያጎረሰችው መመገብ ጀመሩ
: እሱም ወደ መጥገቡ ሲደርስ በቃኝ የእኔ ውድ ይላታል እሷም እንዴ በዛሬ ቀን ያልተበላ መች ሊበላ ነው እያለች በላይ በላይ ስታጎርሰው "ውይ በቃኝ" ብሎ እጇን ሲይዛት ወርቅ ሆነች.......
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.ወይኔ ብሎ ራሱን ሲይዝ ......😊😊 ወርቅ ሆኖ አረፈው
💮💮💮💮💮💮💮💮💮💮
ጌታችን "የምትለምኑትን አታውቁምን?" ያለው ይህን ነው እኛም ክርስቲያኖች አስቀድመን ጽድቁን እና መንግስቱን ነው ልንሻ ሚያስፈልገን ሌላው ትርፍ ነው .....
🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐🛐
@venisiya21 @venisiya21
✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝
ሴትየዋ እንጀራ ለመጋገር ዝግጅቱን ሁሉ አጠናቃለች ሊጡ ቀጥኖ ቀራርቧል ማገዶው ተነስንሶ ምጣዱም ተጥዷል ድንገት እንግዳ የሆነ ነገር ተከሰተ።
አንድ ወደል አይጥ ከየት መጣ ሳይባል እምጣዱ ላይ ጉብ ይላል።
በንዴት የበገነችው ሴትዮዋ ወፍራም ዱላ ታነሳና ወደ አይጡ ትጠጋለች ድርጊቱን ስትከታታል የነበረችውና ፍጻሜው ያላማራት ጎረቤቷ የሴትዮዋን ስም ጠርታ "እገሊት ዱላውን ተይው እሳቱን ቆስቁሽው/አያይዥው/ አለቻት።
⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛
ለአይጧ ዱላ ከማንሳት በፊት አይጧ የተቀመጠችበትን ንብረት ማየት ያስፈልጋል። የስሙኒ ዶሮ የብር ገመድ ይዛ መጥፋት የለባትም ።
ምእመናን እምነታቸውን ዐውቀው እንዲጸኑ ብቻ ከደከምን በአይጥ የተመሰሉ አፅራረ ቤተክርስቲያንን ማስወገድ እንችላለን።
ሃይማኖት አለን ይህን ሃይማኖት በሥራ እንግለጠው
☦☦☦☦☦☦☦☦☦
@Venisiya21 @Venisiya21
🔅🔆🔅🔆🔅🔆🔅🔆🔅
አንድ ወደል አይጥ ከየት መጣ ሳይባል እምጣዱ ላይ ጉብ ይላል።
በንዴት የበገነችው ሴትዮዋ ወፍራም ዱላ ታነሳና ወደ አይጡ ትጠጋለች ድርጊቱን ስትከታታል የነበረችውና ፍጻሜው ያላማራት ጎረቤቷ የሴትዮዋን ስም ጠርታ "እገሊት ዱላውን ተይው እሳቱን ቆስቁሽው/አያይዥው/ አለቻት።
⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛⚛
ለአይጧ ዱላ ከማንሳት በፊት አይጧ የተቀመጠችበትን ንብረት ማየት ያስፈልጋል። የስሙኒ ዶሮ የብር ገመድ ይዛ መጥፋት የለባትም ።
ምእመናን እምነታቸውን ዐውቀው እንዲጸኑ ብቻ ከደከምን በአይጥ የተመሰሉ አፅራረ ቤተክርስቲያንን ማስወገድ እንችላለን።
ሃይማኖት አለን ይህን ሃይማኖት በሥራ እንግለጠው
☦☦☦☦☦☦☦☦☦
@Venisiya21 @Venisiya21
🔅🔆🔅🔆🔅🔆🔅🔆🔅
እንዲህ አይነት ምርቃት አለ
ሁለት ካህናት ከአንድ ምእመን ጋር ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ በእግራቸው ሲሄዱ ይመሽባቸውና ከሰው ቤት ለምነው ይገባሉ። ባለቤትየውም መንገደኞቹ ከጠበቁት በላይ ተንከባክቦ ያሳድራቸዋል። ጠዋት መንገዳቸውን ሊቀጥሉ ሲሉም ለቁርስ የሚሆን ቁራሽ ይቋጠርላቸዋል በዚህ ሁሉ የተደነቁት አረጋዊ ካህን:-
በሰማይ ቤት ሰይጣንን ከሳሽ
እርስዎን ተከሳሽ
እኛን ምስክር አድርጎ ያቁመን
ብለው ያሳደሯቸውን ሰው መረቁት
@Venisiya21 @Venisiya21
ሁለት ካህናት ከአንድ ምእመን ጋር ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ በእግራቸው ሲሄዱ ይመሽባቸውና ከሰው ቤት ለምነው ይገባሉ። ባለቤትየውም መንገደኞቹ ከጠበቁት በላይ ተንከባክቦ ያሳድራቸዋል። ጠዋት መንገዳቸውን ሊቀጥሉ ሲሉም ለቁርስ የሚሆን ቁራሽ ይቋጠርላቸዋል በዚህ ሁሉ የተደነቁት አረጋዊ ካህን:-
በሰማይ ቤት ሰይጣንን ከሳሽ
እርስዎን ተከሳሽ
እኛን ምስክር አድርጎ ያቁመን
ብለው ያሳደሯቸውን ሰው መረቁት
@Venisiya21 @Venisiya21
+++ ምን ብዬ ልጸልይ? +++
በግሪክ ሀገር ሁለት ሴት ልጆቹን ያሉት አንድ አባት ነበር። በአንድ ዓመት ብቻ የሚበላለጡትን እነዚህን ሕጻናት እንደ አባትም እንደ እናትም ሆኖ ተንከባክቦ ማሳደግ የዚህ ሰው ዋነኛ ሥራው ነበር።
ስለዚህ ወጥቶ በገባ ቁጥር ልጆቹን የሚያስደስት ነገር እየገዛ ፣ የሚጠይቁትን እያሟላ በድሎት ያኖራቸው ነበር። የራሱን ሕይወት ወደ ጎን ትቶ ለልጆቹ መኖሩ ያለ ዋጋ አልቀረም። ሁለቱም ልጆቹ በጤንነት አድገው ዕድሜያቸው ለጋብቻ ደረሰ።
አባት የለፋባቸው ልጆቹን ከመዳሩ በፊት ብዙ መሰብ ነበረበት። አስተዋይ ነበርና ብዙ ሽማግሌ ቢላክበትም ልጆቹን ለመሥጠት የወሰነው ግን በጥንቃቄ ነበር። ስለዚህ ልጆቹ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እንዳይቸገሩ በማሰብ የተለያየና የማይነጥፍ መተዳደሪያ ላላቸው ወንዶች ባል እንዲሆኑ ለማድረግ ወሰነ።
እንዲህ ሲልም ያወጣና ያወርድ ጀመር :
"ሰዎች ሁልጊዜም ምግብ ያስፈልጋቸዋል ስለዚህ ገበሬ መቼም ቢሆን እህል ገዢ አያጣም። እንዲሁም ሰዎች ውኃ ለመቅዳት ምግብ ለመሥራት ሸክላ ስለሚፈልጉ ሸክላ ሠሪም ገበያ አያጣም።
ስለዚህ ልጆቼን የምሠጠው ለሸክላ ሠሪና ለገበሬ ነው" አለ። እንዳለውም አንዲቷ ልጁ የገበሬ ሚስት ሌላኛዋ ደግሞ የሸክላ ሠሪ ሚስት እንዲሆኑ ሠጣቸው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በአንድ ሰንበት ይህ ሽማግሌ ዛሬስ ልጆቼን ልጠይቅ ብሎ ተነሣ። በመጀመሪያ ወደ ገበሬው ሚስት ሔዶ ሲጫወት አረፈደ።
ተሰናብቶ ሊወጣ ሲል ልጁ እንዲህ አለችው :
"አባዬ እስካሁን ኑሮአችን ሰላም ነበር። አሁን ግን ችግር ላይ ነን። ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም ጨርሶ አልዘነበም። በዚሁ ከቀጠለ የዘራነው አይበቅልም ፣ ተክሎቻችንም ይደርቃሉ።
አባዬ አደራ! በሚመጣው ወር ከባድ ዝናም እንዲጥል ወደ ፈጣሪ ጸልይልን!"
አባት አደራውን ተቀብሎ ተሰናብቶ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ለመሔድ ጉዞውን ጀመረ።
ከሰዓት በኋላ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ሲደርስ ከሸክላ ሠሪው ባሏ ጋር በአክብሮት ተቀብለው አስተናገዱት። ከጠዋቱ የበለጠ ደስተኛ ሆኖም አሳለፈ። መሰናበቻው ላይ ግን ልጁ ተነሥታ እንዲህ አለችው:
"አባዬ ለአንተ ለጸሎተኛው አባቴና ለጠንካራው ባለቤቴ ምስጋና ይሁንና ኑሮአችን እስካሁን ጥሩ ነው። እንደምታውቀው ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም አልዘነመም። በዚህም ደስተኞች ነን። አሁን የምለምንህ አንድ ነገር ብቻ ነው።
በሜዳ ላይ ተደርድሮ እንደምታየው እጅግ ብዙ ሸክላዎች እየሠራን ነው። በሚመጣው ወር ዝናም ካልዘነመና ደረቅ ከሆነ የሠራናቸው ዕቃዎች ሁሉ ደርቀው ለገበያ ይደርሱልናል። ስለዚህ በሚመጣው ወር ዝናም እንዳይጥል ወደ ፈጣሪህ ጸልይልን"
አባት ተሰናብቶ ሲወጣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ
"ፈጣሪዬ ሆይ አንዲቱ እንዳይዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ሌላዋ እንዲዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ምን ብዬ ልጸልይ?" አለ።
ይህ አረጋዊ የእኛን ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቢያስቀድስ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም ነበር። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ የሚያነበው ምእመናን በግንባራቸው ተደፍተው የሚሰሙት "በእንተ ቅድሳት" የሚባል ጸሎት ላይ የዚህን ሽማግሌ ልብ የሚያረጋጋ ስለ ዝናም የሚጸለይ አንቀጽ አለ። እንዲህ ይላል:
"በሚሻበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ ስለ ዝናም እንማልዳለን"
"በሚሻበት" የሚለው ቃል ላይ "ሻ" ጠብቃ ትነበባለች። "በሚፈለግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ" (ኀበ ዘይትፈቀድ መካን) ማለት ነው። ቀሳውስቱም ስለ ዝናማት በሚጸልዩት መስተብቁዕ ላይ "ወደ ሚሻበት ቦታ ዝናሙን ይልክ ዘንድ" (ከመ ዝናሞ ይፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) "ወደሚሻበት ቦታ ዝናሞችህን ላክ"(ዝናማቲከ ፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) ይላሉ።
ዝናም እንደ ገበሬው ቤት የሚፈለግበት ቦታ እንዳለ ሁሉ እንደ ሸክላ ሠሪው ቤት ደግሞ የማይፈለግበት ቦታ አለና ቤተ ክርስቲያን ከፈጣሪዋ ዝናም ከመለመን አልፋ የሚያዘንምበትን ቦታም እየጠቆመች ትጸልያለች። ⊰
ቬ⊱⊰ኒ⊱⊰ሲ⊱⊰ያ⊱:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
በግሪክ ሀገር ሁለት ሴት ልጆቹን ያሉት አንድ አባት ነበር። በአንድ ዓመት ብቻ የሚበላለጡትን እነዚህን ሕጻናት እንደ አባትም እንደ እናትም ሆኖ ተንከባክቦ ማሳደግ የዚህ ሰው ዋነኛ ሥራው ነበር።
ስለዚህ ወጥቶ በገባ ቁጥር ልጆቹን የሚያስደስት ነገር እየገዛ ፣ የሚጠይቁትን እያሟላ በድሎት ያኖራቸው ነበር። የራሱን ሕይወት ወደ ጎን ትቶ ለልጆቹ መኖሩ ያለ ዋጋ አልቀረም። ሁለቱም ልጆቹ በጤንነት አድገው ዕድሜያቸው ለጋብቻ ደረሰ።
አባት የለፋባቸው ልጆቹን ከመዳሩ በፊት ብዙ መሰብ ነበረበት። አስተዋይ ነበርና ብዙ ሽማግሌ ቢላክበትም ልጆቹን ለመሥጠት የወሰነው ግን በጥንቃቄ ነበር። ስለዚህ ልጆቹ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እንዳይቸገሩ በማሰብ የተለያየና የማይነጥፍ መተዳደሪያ ላላቸው ወንዶች ባል እንዲሆኑ ለማድረግ ወሰነ።
እንዲህ ሲልም ያወጣና ያወርድ ጀመር :
"ሰዎች ሁልጊዜም ምግብ ያስፈልጋቸዋል ስለዚህ ገበሬ መቼም ቢሆን እህል ገዢ አያጣም። እንዲሁም ሰዎች ውኃ ለመቅዳት ምግብ ለመሥራት ሸክላ ስለሚፈልጉ ሸክላ ሠሪም ገበያ አያጣም።
ስለዚህ ልጆቼን የምሠጠው ለሸክላ ሠሪና ለገበሬ ነው" አለ። እንዳለውም አንዲቷ ልጁ የገበሬ ሚስት ሌላኛዋ ደግሞ የሸክላ ሠሪ ሚስት እንዲሆኑ ሠጣቸው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በአንድ ሰንበት ይህ ሽማግሌ ዛሬስ ልጆቼን ልጠይቅ ብሎ ተነሣ። በመጀመሪያ ወደ ገበሬው ሚስት ሔዶ ሲጫወት አረፈደ።
ተሰናብቶ ሊወጣ ሲል ልጁ እንዲህ አለችው :
"አባዬ እስካሁን ኑሮአችን ሰላም ነበር። አሁን ግን ችግር ላይ ነን። ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም ጨርሶ አልዘነበም። በዚሁ ከቀጠለ የዘራነው አይበቅልም ፣ ተክሎቻችንም ይደርቃሉ።
አባዬ አደራ! በሚመጣው ወር ከባድ ዝናም እንዲጥል ወደ ፈጣሪ ጸልይልን!"
አባት አደራውን ተቀብሎ ተሰናብቶ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ለመሔድ ጉዞውን ጀመረ።
ከሰዓት በኋላ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ሲደርስ ከሸክላ ሠሪው ባሏ ጋር በአክብሮት ተቀብለው አስተናገዱት። ከጠዋቱ የበለጠ ደስተኛ ሆኖም አሳለፈ። መሰናበቻው ላይ ግን ልጁ ተነሥታ እንዲህ አለችው:
"አባዬ ለአንተ ለጸሎተኛው አባቴና ለጠንካራው ባለቤቴ ምስጋና ይሁንና ኑሮአችን እስካሁን ጥሩ ነው። እንደምታውቀው ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም አልዘነመም። በዚህም ደስተኞች ነን። አሁን የምለምንህ አንድ ነገር ብቻ ነው።
በሜዳ ላይ ተደርድሮ እንደምታየው እጅግ ብዙ ሸክላዎች እየሠራን ነው። በሚመጣው ወር ዝናም ካልዘነመና ደረቅ ከሆነ የሠራናቸው ዕቃዎች ሁሉ ደርቀው ለገበያ ይደርሱልናል። ስለዚህ በሚመጣው ወር ዝናም እንዳይጥል ወደ ፈጣሪህ ጸልይልን"
አባት ተሰናብቶ ሲወጣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ
"ፈጣሪዬ ሆይ አንዲቱ እንዳይዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ሌላዋ እንዲዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ምን ብዬ ልጸልይ?" አለ።
ይህ አረጋዊ የእኛን ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቢያስቀድስ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም ነበር። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ የሚያነበው ምእመናን በግንባራቸው ተደፍተው የሚሰሙት "በእንተ ቅድሳት" የሚባል ጸሎት ላይ የዚህን ሽማግሌ ልብ የሚያረጋጋ ስለ ዝናም የሚጸለይ አንቀጽ አለ። እንዲህ ይላል:
"በሚሻበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ ስለ ዝናም እንማልዳለን"
"በሚሻበት" የሚለው ቃል ላይ "ሻ" ጠብቃ ትነበባለች። "በሚፈለግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ" (ኀበ ዘይትፈቀድ መካን) ማለት ነው። ቀሳውስቱም ስለ ዝናማት በሚጸልዩት መስተብቁዕ ላይ "ወደ ሚሻበት ቦታ ዝናሙን ይልክ ዘንድ" (ከመ ዝናሞ ይፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) "ወደሚሻበት ቦታ ዝናሞችህን ላክ"(ዝናማቲከ ፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) ይላሉ።
ዝናም እንደ ገበሬው ቤት የሚፈለግበት ቦታ እንዳለ ሁሉ እንደ ሸክላ ሠሪው ቤት ደግሞ የማይፈለግበት ቦታ አለና ቤተ ክርስቲያን ከፈጣሪዋ ዝናም ከመለመን አልፋ የሚያዘንምበትን ቦታም እየጠቆመች ትጸልያለች። ⊰
ቬ⊱⊰ኒ⊱⊰ሲ⊱⊰ያ⊱:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
በአንድ ብርጭቆ ወተት ተከፍሏል
አንድ እጅግ በድህነት ያለ ወጣት በየቤቱ እየዞረ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ለትምህርት ቤት በመክፈልና የእለት ቀለብ በማግኘት ይኖር ነበር፡፡ አንድ ቀን እጅግ በጣም ተራበ፡፡ በእጁ ያለው አስር ሳንቲም ብቻ ስለነበረ ምንም ነገር ማድረግ አልቻም፡፡ ረሃቡ ሲጠናበት አንድ ቤት አንኳኩቶ ምግብ ለመጠየቅ ፈለገና የአንድን ቤት በር ሲያንኳኳ አንዲት ቆንጆ ወጣት በሩን ስትከፍት ምግብ መጠየቅን አፈረና ውኃ አጠጭኝ ብሎ ጠየቃት፡፡
ልጅቷ ወጣቱን ስታየው እንደራበው ስለገመተች በትልቅ ብርጭቆ ወተት ይዛ መጣችና ሰጠችው፡፡ በቀስታ እያጣጣመ ከጠጣ በኋላ፣ የወተቱን ሂሳብ ለመክፈል ያለበትን እዳ ጠየቃት፡፡ “ምንም እዳ የለብህም” ነበር የልጅቷ መልስ፡፡ በመቀጠልም፣ “እናታችን ለሰው ለምታደርጉት መልካምነት በፍጹም ክፍያን አትቀበሉ ብላ አስተምራ ነው ያሳደገችን” አለችው፡፡ “ከልብ አመሰግንሻለሁ” ብሏት ተስፋ ቆርጦ የነበረው ይህ ወጣት በብርታት ተሞልቶ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ይህ ሁኔታ ከተከናወነ ከብዙ አመታት በኋላ ያቺ ወተት ያጠጣችው ወጣት በእድሜ ገፋ ብላ ባለችበት ወቅት አደገኛ ህመም ላይ ወደቀች፡፡ የአካቢቢው ሃኪሞች ሁሉ በሽታዋን ሊያውቁት ስላልቻሉ ግር ተሰኙ፡፡ ምርጫቸው ትልቅ ከተማ ውስጥ ወደሚገኝ ከፍተኛ ሆስፒታል ማስተላለፍ ነበር፡፡ በዚያ ትልቅ ሆስፒታል የታወቀ የሕክምና ባለሞያ መጠራት ነበረበት፡፡ ይህ የተገኘው ዶክተር ማለት ከብዙ አመታት በፊት በረሃብ ሳለ በትልቅ ብርጭቆ ወተትን ከዚህች ሴት እጅ ተቀብሎ ጠጥቶ ረሃቡን ያስታገሰ ሰው ነው፡፡
ይህ ዶክተር በሽተኛዋ የመጣችበትን ትንሽ ከተማ ስም ሲሰማ ጆሮውን ጣል አደረገ፤ እርሱም ያደገው እዚያች ከተማ ውስጥ በመሆኑ፡፡ የህክምና ነጭ ልብሱን ለብሶ በፍጥነት ወደ ክፍሏ ሲገባ በአንድ ጊዜ ትዝ አለችው፤ እሷ ግን አላወቀችውም፡፡ ሃኪሞች ወደሚማከሩበት ክፍል በመግባት ይህችን የረሃብ ዘመን ባለውለታው የሆነችውን ሴት ለማዳን የተቻለውን ጥረት ማድረግ ጀመረ፡፡ ከብዙ ትግል በኋላ በሽታው ተገኘና ሴቲቱ ዳነች፡፡
ይህች ሴት በአንድ ጎኑ ሕመሟ በመዳኑ ደስ ሲላት በሌላው ጎኑ ግን አንድ ነገር አሳስቧት ነበር፡፡ ለህክምና የወጣውን የገንዘብ መጠን እንኳን ይህች ሴት ልትከፍለው ቀርቶ ማሰብ እንኳ እስከማትችል እጅግ ብዙና ለመክፈል እድሜ ልኳን ሊፈጅባት የሚችል ነበር፡፡ ዶክተር ሃዋርደ የህክምና ሂሳብ ወደ ቢሮው እንዲልኩለት መልእክትን ካስተላለፈ በኋላ ቢሮ ገባ፡፡ ለህክምና የወጣውን የወጪ ደረሰኝ በእጁ ካስገባ በኋላ አንድ ነገር ጻፈበትና በኤንቨሎፕ አሽጎ ወደ ህመምተኛዋ እንዲሰጥ ላከው፡፡
ሴትዬዋ ሊመጣባት የሚችለውን የወጪ መዘዝ ስላሰበች የክፍያ ማዘዣ የያዘውን ኤንቨሎፕ ለመክፈት እጅግ ፈራች፤ እድሜ ልኳን ብትሰራ እንኳ ከፍላ የማትጨርሰው ወጪ እንደሚሆን ግልጽ ስለነበር፡፡ ሆኖም ማድረግ የነበረባት ነገር ስነበር በቀስታና በፍርሃ ከፈተችው፡፡ የገንዘቡን መጠን ካነበበች በኋላ ልቧ እየመታ ወረቀቱ ጫፍ ላይ የዶክተር ሃዋርድ ፊርማ ያለበትን አጭር ማስታወሻ ተመለከተች፡፡ እንዲህ ይላል፣ “የሕክምናው እዳ በአንድ ብርጭቆ ወተት ተከፍሏል”፡፡ ታሪኩ በአንድ ጊዜ ትዝ አላትና ሳታስበው አይኖቿ እንባን ማፍሰስ ጀመሩ
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
ከዚህ ታሪክ እንደምንማረው መልካም ማድረግ መልሶ እኛኑ እንደሚጠቅም ነውና ያለንን ስንሰጥ እግዚአብሔር በችግራችን ሰዓት ይደርስልናል።
ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
አንድ እጅግ በድህነት ያለ ወጣት በየቤቱ እየዞረ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ለትምህርት ቤት በመክፈልና የእለት ቀለብ በማግኘት ይኖር ነበር፡፡ አንድ ቀን እጅግ በጣም ተራበ፡፡ በእጁ ያለው አስር ሳንቲም ብቻ ስለነበረ ምንም ነገር ማድረግ አልቻም፡፡ ረሃቡ ሲጠናበት አንድ ቤት አንኳኩቶ ምግብ ለመጠየቅ ፈለገና የአንድን ቤት በር ሲያንኳኳ አንዲት ቆንጆ ወጣት በሩን ስትከፍት ምግብ መጠየቅን አፈረና ውኃ አጠጭኝ ብሎ ጠየቃት፡፡
ልጅቷ ወጣቱን ስታየው እንደራበው ስለገመተች በትልቅ ብርጭቆ ወተት ይዛ መጣችና ሰጠችው፡፡ በቀስታ እያጣጣመ ከጠጣ በኋላ፣ የወተቱን ሂሳብ ለመክፈል ያለበትን እዳ ጠየቃት፡፡ “ምንም እዳ የለብህም” ነበር የልጅቷ መልስ፡፡ በመቀጠልም፣ “እናታችን ለሰው ለምታደርጉት መልካምነት በፍጹም ክፍያን አትቀበሉ ብላ አስተምራ ነው ያሳደገችን” አለችው፡፡ “ከልብ አመሰግንሻለሁ” ብሏት ተስፋ ቆርጦ የነበረው ይህ ወጣት በብርታት ተሞልቶ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ይህ ሁኔታ ከተከናወነ ከብዙ አመታት በኋላ ያቺ ወተት ያጠጣችው ወጣት በእድሜ ገፋ ብላ ባለችበት ወቅት አደገኛ ህመም ላይ ወደቀች፡፡ የአካቢቢው ሃኪሞች ሁሉ በሽታዋን ሊያውቁት ስላልቻሉ ግር ተሰኙ፡፡ ምርጫቸው ትልቅ ከተማ ውስጥ ወደሚገኝ ከፍተኛ ሆስፒታል ማስተላለፍ ነበር፡፡ በዚያ ትልቅ ሆስፒታል የታወቀ የሕክምና ባለሞያ መጠራት ነበረበት፡፡ ይህ የተገኘው ዶክተር ማለት ከብዙ አመታት በፊት በረሃብ ሳለ በትልቅ ብርጭቆ ወተትን ከዚህች ሴት እጅ ተቀብሎ ጠጥቶ ረሃቡን ያስታገሰ ሰው ነው፡፡
ይህ ዶክተር በሽተኛዋ የመጣችበትን ትንሽ ከተማ ስም ሲሰማ ጆሮውን ጣል አደረገ፤ እርሱም ያደገው እዚያች ከተማ ውስጥ በመሆኑ፡፡ የህክምና ነጭ ልብሱን ለብሶ በፍጥነት ወደ ክፍሏ ሲገባ በአንድ ጊዜ ትዝ አለችው፤ እሷ ግን አላወቀችውም፡፡ ሃኪሞች ወደሚማከሩበት ክፍል በመግባት ይህችን የረሃብ ዘመን ባለውለታው የሆነችውን ሴት ለማዳን የተቻለውን ጥረት ማድረግ ጀመረ፡፡ ከብዙ ትግል በኋላ በሽታው ተገኘና ሴቲቱ ዳነች፡፡
ይህች ሴት በአንድ ጎኑ ሕመሟ በመዳኑ ደስ ሲላት በሌላው ጎኑ ግን አንድ ነገር አሳስቧት ነበር፡፡ ለህክምና የወጣውን የገንዘብ መጠን እንኳን ይህች ሴት ልትከፍለው ቀርቶ ማሰብ እንኳ እስከማትችል እጅግ ብዙና ለመክፈል እድሜ ልኳን ሊፈጅባት የሚችል ነበር፡፡ ዶክተር ሃዋርደ የህክምና ሂሳብ ወደ ቢሮው እንዲልኩለት መልእክትን ካስተላለፈ በኋላ ቢሮ ገባ፡፡ ለህክምና የወጣውን የወጪ ደረሰኝ በእጁ ካስገባ በኋላ አንድ ነገር ጻፈበትና በኤንቨሎፕ አሽጎ ወደ ህመምተኛዋ እንዲሰጥ ላከው፡፡
ሴትዬዋ ሊመጣባት የሚችለውን የወጪ መዘዝ ስላሰበች የክፍያ ማዘዣ የያዘውን ኤንቨሎፕ ለመክፈት እጅግ ፈራች፤ እድሜ ልኳን ብትሰራ እንኳ ከፍላ የማትጨርሰው ወጪ እንደሚሆን ግልጽ ስለነበር፡፡ ሆኖም ማድረግ የነበረባት ነገር ስነበር በቀስታና በፍርሃ ከፈተችው፡፡ የገንዘቡን መጠን ካነበበች በኋላ ልቧ እየመታ ወረቀቱ ጫፍ ላይ የዶክተር ሃዋርድ ፊርማ ያለበትን አጭር ማስታወሻ ተመለከተች፡፡ እንዲህ ይላል፣ “የሕክምናው እዳ በአንድ ብርጭቆ ወተት ተከፍሏል”፡፡ ታሪኩ በአንድ ጊዜ ትዝ አላትና ሳታስበው አይኖቿ እንባን ማፍሰስ ጀመሩ
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
ከዚህ ታሪክ እንደምንማረው መልካም ማድረግ መልሶ እኛኑ እንደሚጠቅም ነውና ያለንን ስንሰጥ እግዚአብሔር በችግራችን ሰዓት ይደርስልናል።
ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
በተሣፋሪወች የተሞላዉ አዉቶብስ ጉዞ ላይ ነዉ...ወዲያዉ የአካባቢዉ የአየር ሁኔታ ተቀያየረና አስፈሪ የነጎድጓድ ድምፅ፡በረዶ..የመብረቅ ብልጭታ መታየት ጀመረ፡፡
ተሣፋሪዎቹ አዉቶብሱ ከአሁን አሁን በመብረቅ ተመታ እያሉ መጨነቅ ጀመሩ...መብረቁ ግን መኪናዉን እያለፈ ይወድቅ ነበር፡፡
እንዲህ አይነቱ አጋጣሚ ሁለት ሶስቴ እንደቀጠለ....ሾፌሩ አዉቶብሱን ከአንድ ዛፍ ሃምሳ ጫማ ርቀት ሲቀረዉ አቆመና
ተሣፋሪወቹን
"ከእናንተ መሃል ዛሬ መሞቱ ግዴታ የሆነ ሰዉ አለ...ከአሁን በኋላ አብሮን ከተጓዘ በእሱ ምክንያት ሌሎቻችንም አብረን ልንጠፋ እንችላለን ስለዚህ...ሁላችሁም በየተራ እየወጣችሁ ያንን ዛፍ እየነካችሁ እንድትመለሱ እፈልጋለሁ...መሞት ያለበት ሰዉ ካለም ዛፉን የነካ ጊዜ በመብረቅ ይመታል..ሌሎቻችን ግን እንተርፍለን ማለት ነዉ!!" አለ
.ሁሉም የመጀመሪያዉን ተሳፋሪ ሄዶ ዛፍን እንዲነካ መጎትጎት ጀመሩ...እሱም እየጨነቀዉና በፍርሃት ተዉጦ ሄዶ ዛፍን ነክቶ በሰላም ተመለሰ...ምንም ሳይሆን በመመለሱም ልቡ በደስታ ጮቤ ረገጠች፡፡
.መጨረሻ ላይ የነበረዉ ተሣፋሪ ተራ እንደደረሰ..ሁሉም በበደለኛ(ሟቹ እሱ እንደሆነ በማሠብ) አይን እያዩት እንዲሄድ ገፋፉት..እሱም በመሞት ፍራቻ ተዉጦ ከአዉቶብሱ ወረደ::
....ከዛፉ ደርሶ እንደነካዉም ሃይለኛ ድምፅ ተሠማ ፡ አስፈሪ የመብረቅ ብልጭታም ታየ....መብረቁ
.
.
.
.
.
.ግን የመታዉ አዉቶብሱን ነዉ...አዎ አዉቶብሱን መታዉ..ዉስጡ የነበሩት ተሳፋሪዎችም ሞቱ፡፡
...እነዚያ ቀደም ብሎ አዉቶብሱን ያለፉት አደጋወች ሁሉ ያለፉትም በመጨረሻዉ ተሣፋሪ ምክንያት ነበር፡፡
አንዳንዴ የስኬቶቻችን ሁሉ አድራጊ ፈጣሪዎች ራሳችን ብቻ እንደሆንን እናስብና..ሽልማቱን ለራሣችን ብቻ እንሰጣለን...ለዚያ ያበቁን ብዙ ባለዉለታወቻችንን ፈጣሪን ዘንግተን እኮ ነዉ፡፡
“እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።”
— ማቴዎስ 7፥1-2
ተሣፋሪዎቹ አዉቶብሱ ከአሁን አሁን በመብረቅ ተመታ እያሉ መጨነቅ ጀመሩ...መብረቁ ግን መኪናዉን እያለፈ ይወድቅ ነበር፡፡
እንዲህ አይነቱ አጋጣሚ ሁለት ሶስቴ እንደቀጠለ....ሾፌሩ አዉቶብሱን ከአንድ ዛፍ ሃምሳ ጫማ ርቀት ሲቀረዉ አቆመና
ተሣፋሪወቹን
"ከእናንተ መሃል ዛሬ መሞቱ ግዴታ የሆነ ሰዉ አለ...ከአሁን በኋላ አብሮን ከተጓዘ በእሱ ምክንያት ሌሎቻችንም አብረን ልንጠፋ እንችላለን ስለዚህ...ሁላችሁም በየተራ እየወጣችሁ ያንን ዛፍ እየነካችሁ እንድትመለሱ እፈልጋለሁ...መሞት ያለበት ሰዉ ካለም ዛፉን የነካ ጊዜ በመብረቅ ይመታል..ሌሎቻችን ግን እንተርፍለን ማለት ነዉ!!" አለ
.ሁሉም የመጀመሪያዉን ተሳፋሪ ሄዶ ዛፍን እንዲነካ መጎትጎት ጀመሩ...እሱም እየጨነቀዉና በፍርሃት ተዉጦ ሄዶ ዛፍን ነክቶ በሰላም ተመለሰ...ምንም ሳይሆን በመመለሱም ልቡ በደስታ ጮቤ ረገጠች፡፡
.መጨረሻ ላይ የነበረዉ ተሣፋሪ ተራ እንደደረሰ..ሁሉም በበደለኛ(ሟቹ እሱ እንደሆነ በማሠብ) አይን እያዩት እንዲሄድ ገፋፉት..እሱም በመሞት ፍራቻ ተዉጦ ከአዉቶብሱ ወረደ::
....ከዛፉ ደርሶ እንደነካዉም ሃይለኛ ድምፅ ተሠማ ፡ አስፈሪ የመብረቅ ብልጭታም ታየ....መብረቁ
.
.
.
.
.
.ግን የመታዉ አዉቶብሱን ነዉ...አዎ አዉቶብሱን መታዉ..ዉስጡ የነበሩት ተሳፋሪዎችም ሞቱ፡፡
...እነዚያ ቀደም ብሎ አዉቶብሱን ያለፉት አደጋወች ሁሉ ያለፉትም በመጨረሻዉ ተሣፋሪ ምክንያት ነበር፡፡
አንዳንዴ የስኬቶቻችን ሁሉ አድራጊ ፈጣሪዎች ራሳችን ብቻ እንደሆንን እናስብና..ሽልማቱን ለራሣችን ብቻ እንሰጣለን...ለዚያ ያበቁን ብዙ ባለዉለታወቻችንን ፈጣሪን ዘንግተን እኮ ነዉ፡፡
“እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።”
— ማቴዎስ 7፥1-2
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
🌱🌱🌱 ችግኟ 🌱🌱🌱🌱
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ችግኝ ተተክሎ ዛፍ እንደሚሆን እንጂ ችግኝን እንዴት እንደሚንከባከቡት በውል የማያውቀው ሕጻን የተከላትን የዛፍ ችግኝ ለማየት ጠዋት ይወጣና ውኃ ካጠጣት በኋላ አጠገቡ ቁጭ ብሎ ሲያያት ውሎ ሲያያት ያመሻል።
እንዲህ የመጨነቁና የመጠበቡ ምስጢር ደግሞ አባቱ ይኽቺን ችግኝ ተክለህና አጽድቀህ ጠብቀኝ ብሎት ለሥራ ወደ ክፍለ ሃገር ስለሄደ ነበር። እናት የልጇን እንግዳ ነገር ስለለመደችው የት ዋልክ እያለች አታስጨንቀውም። ብቻ ጀምበሯ ማዘቅዘቅ ስትጀምር ልጇን ለእራትና ለመኝታ ትጠራዋለች ።
ይኸ እየሆነ ሳለ በእግዚአብሔር ቸርነት ችግኟ ጸደቀች፣ አባትም ከሄደበት አገር በሰላም ተመለሰና ለልጁ አደራ ሰጥቶት የሄደው የችግኟ ነገር ከምን እንደደረሰ ለማወቅ ሽቶ "ችግኝህ እንዴት ሆነች? የእኔ ጎበዝ? ሲል ጥያቄ አቀረበ።
ገና ከጅማሬው የችግኝን ጠባይ ያልተረዳው የዋሑ ሕጻን ፊቱ በደስታ እየፈካ አባቱ የሰጠውን ኃላፊነት በሚገባ እንደተወጣ ለማሳየት " ቆይ ላሳይህ" አለና ወደ ውጪ በረረ።
አባት ለነገሩ ትኩረት ሳይሰጠው ከባለቤቱ ጋር ወግ ይዞ እያለ ሕጻኑ በፍጥነት ተመልሶ " ይኸው አባዬ ችግኟ ጸድቃለች" አለ ችግኟን ነቅሎ አምጥቶ ለአባቱ እያሳየ። ያልታደለች ችግኝ።
☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘
ሁሌም ቢሆን አንድን ሥራ ለምን እንደምንሠራው ምክንያቱን፣ ለማን እንደምንሰራው ባለቤቱን ማወቅ ይኖርብናል። ይህ ደግሞ ስራችን በገዛ ራሳችን እንዳይበላሽና በሥራችን ተስፋ እንዳንቆርጥ ይረዳናል። በተጨማሪም ሥራችንን እናከብረውና እንጠብቀው ዘንድ ያግዘናል።
ይኽ አጭር ታሪክን የሚጠቁመን ይህንኑ ነው በተለይም ችግኟን እንደነቀለው እንደዚህ አላዋቂ ህጻን ማተባችንን የቆረጥን (የበጠስን) ነጠላችንን የጣልን በአጠቃላይ የምንሠራው የጠፋብን ካለን ልብ በሉ ይለናል።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
🌱🌱🌱 ችግኟ 🌱🌱🌱🌱
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ችግኝ ተተክሎ ዛፍ እንደሚሆን እንጂ ችግኝን እንዴት እንደሚንከባከቡት በውል የማያውቀው ሕጻን የተከላትን የዛፍ ችግኝ ለማየት ጠዋት ይወጣና ውኃ ካጠጣት በኋላ አጠገቡ ቁጭ ብሎ ሲያያት ውሎ ሲያያት ያመሻል።
እንዲህ የመጨነቁና የመጠበቡ ምስጢር ደግሞ አባቱ ይኽቺን ችግኝ ተክለህና አጽድቀህ ጠብቀኝ ብሎት ለሥራ ወደ ክፍለ ሃገር ስለሄደ ነበር። እናት የልጇን እንግዳ ነገር ስለለመደችው የት ዋልክ እያለች አታስጨንቀውም። ብቻ ጀምበሯ ማዘቅዘቅ ስትጀምር ልጇን ለእራትና ለመኝታ ትጠራዋለች ።
ይኸ እየሆነ ሳለ በእግዚአብሔር ቸርነት ችግኟ ጸደቀች፣ አባትም ከሄደበት አገር በሰላም ተመለሰና ለልጁ አደራ ሰጥቶት የሄደው የችግኟ ነገር ከምን እንደደረሰ ለማወቅ ሽቶ "ችግኝህ እንዴት ሆነች? የእኔ ጎበዝ? ሲል ጥያቄ አቀረበ።
ገና ከጅማሬው የችግኝን ጠባይ ያልተረዳው የዋሑ ሕጻን ፊቱ በደስታ እየፈካ አባቱ የሰጠውን ኃላፊነት በሚገባ እንደተወጣ ለማሳየት " ቆይ ላሳይህ" አለና ወደ ውጪ በረረ።
አባት ለነገሩ ትኩረት ሳይሰጠው ከባለቤቱ ጋር ወግ ይዞ እያለ ሕጻኑ በፍጥነት ተመልሶ " ይኸው አባዬ ችግኟ ጸድቃለች" አለ ችግኟን ነቅሎ አምጥቶ ለአባቱ እያሳየ። ያልታደለች ችግኝ።
☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘
ሁሌም ቢሆን አንድን ሥራ ለምን እንደምንሠራው ምክንያቱን፣ ለማን እንደምንሰራው ባለቤቱን ማወቅ ይኖርብናል። ይህ ደግሞ ስራችን በገዛ ራሳችን እንዳይበላሽና በሥራችን ተስፋ እንዳንቆርጥ ይረዳናል። በተጨማሪም ሥራችንን እናከብረውና እንጠብቀው ዘንድ ያግዘናል።
ይኽ አጭር ታሪክን የሚጠቁመን ይህንኑ ነው በተለይም ችግኟን እንደነቀለው እንደዚህ አላዋቂ ህጻን ማተባችንን የቆረጥን (የበጠስን) ነጠላችንን የጣልን በአጠቃላይ የምንሠራው የጠፋብን ካለን ልብ በሉ ይለናል።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
አንድ የኮንስትራክሽን ተቆጣጣሪ ከ6ኛ ፎቅ ላይ ሆኖ መሬት ላይ የሚስራውን ሰራተኛ ይጠራዋል፣ ስራተኛው ሊስማው አልቻለም፡፡ ስራተኛው የአሰሪውን ጥሪ ሊስማው ስላልቻለ ተቆጣጣሪው መላ ዘየደ፡፡
እናም የሰራትኛውን ሃሳብ ልማግገኘት ሲል ተቆጣጣሪው ከላይ ብር ጣለለት ብሩም ከሰራተኛው እግር ስር አረፈ፣ ሰራተኛው ብሩን አንስቶ ወደ ኪሱ አሰገብቶ ስራውን ቀጠለ…… በድጋሜ የሰራተኛውን ሃሳብ ለማግኘት ተቆጣጣሪው መጀመሪያ ከጣለው ብር በላይ ሌላ ብር ጨምሮ ጣለለት፣ የቀን ሰራተኛውም ልከ እንደ መጀመሪያው ብሩን አንስቶ ወደ ኪሱ አስገብቶ ስራውን ቀጠለ፡፡
በመጨረሻ ሌላ መላ ዘየደ ብር በመጣል የሰራተኛውን ሀሳብ ማግኘት ስላልቻለ የሰራተኛውን ሃሳብ ለማግኘት አነስ ያለ ድንጋይ አነሳና ወደ ሰራተኛው ወረወረው፣ ድንጋዩም የሰራተኛውን ጭንቅላት አገኝው በዚህ ሰዓት ነበር ሰራተኛው ወደ ላይ የተመለከተው እና ከተቆጣጣሪው ጋር መነጋግር የጀመረው፡፡
ይሄ ታሪክ ከእኛ ህይወት ጋር ይመሳሰላል ፈጣሪ ከኛ ጋር መገናኘት ይፈልጋል ነገር ግን እኛ በጣም በ አለማዊ ስራ ራሳችንን ጠምደናል ከዛ ፈጣሪ ትንሽ ስጦታ ይሰጠናል እኛም ስራችንን እንቀጥላለን ከየት እንዳገኘነው ቀጥ ብለን ለማየት ጊዜ የለንም፡፡
በድጋሜ ፈጣሪ ከመጀመሪያው የተሸለ ስጦታን ይሰጠናል አሁንም ልክ እንደ መጀመሪያው ስጦታውን ወስደን ምስጋናም ለፈጣሪ ሳናቀርብ እድልኞች ነን ብቻ ብለን ስራችንን እንቀጥላልን ከየት እና ከማን እንዳገኘነው ቀና ብለን ለማየት አንሞክርም፡፡
እናም በትንሽ ድንጋይ ስንመታ፣ ማለት ትንሽ ችግር ቢጤ ስታገኘን ወደ ላይ ማየት እና መጮህ ከዚያም ከፈጣሪ ጋር መነጋገር እንጀምራለን፡፡
ስለዚህ ምንግዜም በህይወታችን ስጦታን ስናገኝ በፍጥነት ፈጣሪን ማመስገን አለብን በጭራሽ በትንሽ ድንጋይ እስክንመታ መጠበቅ የለብንም ሁሌም ቢሆን ከፈጣሪ ጋር እንገናኝ፡፡
“ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር።”
— ያዕቆብ 5፥13
እናም የሰራትኛውን ሃሳብ ልማግገኘት ሲል ተቆጣጣሪው ከላይ ብር ጣለለት ብሩም ከሰራተኛው እግር ስር አረፈ፣ ሰራተኛው ብሩን አንስቶ ወደ ኪሱ አሰገብቶ ስራውን ቀጠለ…… በድጋሜ የሰራተኛውን ሃሳብ ለማግኘት ተቆጣጣሪው መጀመሪያ ከጣለው ብር በላይ ሌላ ብር ጨምሮ ጣለለት፣ የቀን ሰራተኛውም ልከ እንደ መጀመሪያው ብሩን አንስቶ ወደ ኪሱ አስገብቶ ስራውን ቀጠለ፡፡
በመጨረሻ ሌላ መላ ዘየደ ብር በመጣል የሰራተኛውን ሀሳብ ማግኘት ስላልቻለ የሰራተኛውን ሃሳብ ለማግኘት አነስ ያለ ድንጋይ አነሳና ወደ ሰራተኛው ወረወረው፣ ድንጋዩም የሰራተኛውን ጭንቅላት አገኝው በዚህ ሰዓት ነበር ሰራተኛው ወደ ላይ የተመለከተው እና ከተቆጣጣሪው ጋር መነጋግር የጀመረው፡፡
ይሄ ታሪክ ከእኛ ህይወት ጋር ይመሳሰላል ፈጣሪ ከኛ ጋር መገናኘት ይፈልጋል ነገር ግን እኛ በጣም በ አለማዊ ስራ ራሳችንን ጠምደናል ከዛ ፈጣሪ ትንሽ ስጦታ ይሰጠናል እኛም ስራችንን እንቀጥላለን ከየት እንዳገኘነው ቀጥ ብለን ለማየት ጊዜ የለንም፡፡
በድጋሜ ፈጣሪ ከመጀመሪያው የተሸለ ስጦታን ይሰጠናል አሁንም ልክ እንደ መጀመሪያው ስጦታውን ወስደን ምስጋናም ለፈጣሪ ሳናቀርብ እድልኞች ነን ብቻ ብለን ስራችንን እንቀጥላልን ከየት እና ከማን እንዳገኘነው ቀና ብለን ለማየት አንሞክርም፡፡
እናም በትንሽ ድንጋይ ስንመታ፣ ማለት ትንሽ ችግር ቢጤ ስታገኘን ወደ ላይ ማየት እና መጮህ ከዚያም ከፈጣሪ ጋር መነጋገር እንጀምራለን፡፡
ስለዚህ ምንግዜም በህይወታችን ስጦታን ስናገኝ በፍጥነት ፈጣሪን ማመስገን አለብን በጭራሽ በትንሽ ድንጋይ እስክንመታ መጠበቅ የለብንም ሁሌም ቢሆን ከፈጣሪ ጋር እንገናኝ፡፡
“ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር።”
— ያዕቆብ 5፥13
ተጠንቀቁ እንጂ አትፍሩ!
አንድ ጊዜ አንድ ንጉስ ከጦር አጃቢዎቹ ጋር ሆኖ ወደ ሌላ ሃገር ጉዞ ሲደርግ አንድ እጅግ አጥፊ የሆነ አውሎ ነፋስ ወደ እሱ አገር አቅጣጫ በመገስገስ ላይ እንዳለ ተመለከተና ባለው የጦር ኃይል አውሎ ነፋሱን አስቁሞ፣ “ወደ እኔ ሃገር አቅጣጫ በመሄድ ላይ ነህ፡፡ ከእኔ ሃገር ሰው ማንንም እንዳማታጠፋ ቃል ካልገባህ አታልፍም አለው” አውሎ ነፋሱም፣ “በእርግጥ ነው ወደዚያ አቅጠጫ ነው የምሄደው፤ ነገር ግን የአንተን ሃገር ሕዝብ በፍጹም እንደማልነካ ቃል እገባልሃለሁ” አለው፡፡
ንጉሱ ከጉዞው ሲመለስ ከሃገሩ ሰዎች በርካታዎቹ እንደሞቱ ሰማ፡፡ በጣም በመቆጣት አውሎ ነፋሱን ተከታትሎ ደረሰበትና፣ “ማንንም እንደማትነካ ቃል ገብተህልኝ ለምንድን ነው ብዙ ሰው የገደልከው?” አለው፡፡ አውሎ ነፋሱም እዲህ ሲል መለሰ፣ “እኔ በሃገርህ አጠገብ አለፍኩኝ እንጂ የሃገርህን ህዝብ አንዱንም አልነካሁም፡፡ እንደሰማሁት ከሆነ ግን ከባድ አውሎ ነፋስ መጣ የሚል ወሬ ተወርቶ በፍርሃትና በድንጋጤ አንዳንዱ በልብ ድካም፣ አንዳንዱ ሲሯሯጥ እርስ በርሱ ተረጋግጦ ነው የሞተው”፡፡
አንዳንዴ በሃገራችን ከሚከሰተው ችግር ይልቅ በችግሩ ላይ ያለን አመለካከት፣ የሚወርሰን ፍርሃት፣ የምንሰጠው ተገቢ ያልሆነ ምላሽና የፍርሃትና የድንጋጤ ስሜታችን ከማየሉ የተነሳ አዋቂዎቹ የሚነግሩንን መመሪያ በአአምሯችን አስበን አለመከተላችን ነው የሚያጠፋን፡፡
አንባቢዎቼ በወቅቱ በደረሰብን አስጊ ሁኔታ ስለራሳችንና ስለቤተሰቦቻችን የማሰባችን ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በምክንያት የለሽ ፍርሃት ከመተራመስና ራስን ለከፋ ነገር ከማጋለጥ እንጠበቅ፡፡
በዚሁ አጋጣሚ ንስሐ ገብተን ፣ ቅዱስ ቁርባንን ተቀብለን እንዘጋጅ
ፈጣሪ እናንተንና የእናንተ የሆኑትን ሁሉ ይጠብቅላችሁ፡፡
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
አንድ ጊዜ አንድ ንጉስ ከጦር አጃቢዎቹ ጋር ሆኖ ወደ ሌላ ሃገር ጉዞ ሲደርግ አንድ እጅግ አጥፊ የሆነ አውሎ ነፋስ ወደ እሱ አገር አቅጣጫ በመገስገስ ላይ እንዳለ ተመለከተና ባለው የጦር ኃይል አውሎ ነፋሱን አስቁሞ፣ “ወደ እኔ ሃገር አቅጣጫ በመሄድ ላይ ነህ፡፡ ከእኔ ሃገር ሰው ማንንም እንዳማታጠፋ ቃል ካልገባህ አታልፍም አለው” አውሎ ነፋሱም፣ “በእርግጥ ነው ወደዚያ አቅጠጫ ነው የምሄደው፤ ነገር ግን የአንተን ሃገር ሕዝብ በፍጹም እንደማልነካ ቃል እገባልሃለሁ” አለው፡፡
ንጉሱ ከጉዞው ሲመለስ ከሃገሩ ሰዎች በርካታዎቹ እንደሞቱ ሰማ፡፡ በጣም በመቆጣት አውሎ ነፋሱን ተከታትሎ ደረሰበትና፣ “ማንንም እንደማትነካ ቃል ገብተህልኝ ለምንድን ነው ብዙ ሰው የገደልከው?” አለው፡፡ አውሎ ነፋሱም እዲህ ሲል መለሰ፣ “እኔ በሃገርህ አጠገብ አለፍኩኝ እንጂ የሃገርህን ህዝብ አንዱንም አልነካሁም፡፡ እንደሰማሁት ከሆነ ግን ከባድ አውሎ ነፋስ መጣ የሚል ወሬ ተወርቶ በፍርሃትና በድንጋጤ አንዳንዱ በልብ ድካም፣ አንዳንዱ ሲሯሯጥ እርስ በርሱ ተረጋግጦ ነው የሞተው”፡፡
አንዳንዴ በሃገራችን ከሚከሰተው ችግር ይልቅ በችግሩ ላይ ያለን አመለካከት፣ የሚወርሰን ፍርሃት፣ የምንሰጠው ተገቢ ያልሆነ ምላሽና የፍርሃትና የድንጋጤ ስሜታችን ከማየሉ የተነሳ አዋቂዎቹ የሚነግሩንን መመሪያ በአአምሯችን አስበን አለመከተላችን ነው የሚያጠፋን፡፡
አንባቢዎቼ በወቅቱ በደረሰብን አስጊ ሁኔታ ስለራሳችንና ስለቤተሰቦቻችን የማሰባችን ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በምክንያት የለሽ ፍርሃት ከመተራመስና ራስን ለከፋ ነገር ከማጋለጥ እንጠበቅ፡፡
በዚሁ አጋጣሚ ንስሐ ገብተን ፣ ቅዱስ ቁርባንን ተቀብለን እንዘጋጅ
ፈጣሪ እናንተንና የእናንተ የሆኑትን ሁሉ ይጠብቅላችሁ፡፡
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
አንድ ተማሪ በፈተና አዳራሽ ገብቶ ሁለት ጥያቄዎችን እንዲሠራ ተሰጠው። ጥያቄዎቹ እነዚህ ናቸው።
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ።
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
ወንድሜ ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑርህ።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ።
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
ወንድሜ ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑርህ።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
ከእለታት አንድ ቀን አንዲት ደቃቃ ጥንቸል እህል ውሃ ፍለጋ በጫካ ውስጥ ስትዘዋወር አንድ ዝንጀሮ ታገኛታለች። ጥንቸሏ ግዙፍ ስላልሆነች በየቅጠላ ቅጠሉ ውስጥ እየተሽሉከለከች መሄድ እንደምትችል ዝንጀሮው ያውቃል ሆኖም አንድ ምክር ሊመክራት ፈልጓል።
እመት ጥንቸል የረዥም ጊዜ ወዳጅነታችንን መሠረት በማድረግ ምክር ልለግስሽ እፈልጋለሁ አላት
ጥንቸልም ምን ዓይነት ምክር? ስትል ጠየቀችው ዝንጀሮውም ይህን ጫካ አትመኝው ሰሞኑን አዳኞች መጥተው ለአውሬ ማጥመጃ የሚሆን ትላልቅ ጉድጓድ ሲቆፍሩ እኔ ዛፍ ላይ ሆኜ አይቻለሁ ስለዚህ ጫካው እንደድሮው ሰላም መስሎሽ ወዲያ ወዲህ አትበይ።
ጥንቸልም "አመሰግናለሁ ወጥመዱን የሠሩት ለእኔ አይመስለኝም። እንደ አንበሳና እንደ ነብር ላሉት እንጂ እንደኔ ቀጫጫ ለሆኑ ፍጡር አይደለም። ባጋጣሚ ጉድጓድ ውስጥ ብወድቅም መውጫ ብልሃት አላጣም! ትለዋለች።
ዝንጀሮም "እንግዲህ የወንድምነቴን መክሬሻለሁ፤ ብታውቂ እወቂበት" አላትና ሄደ። ጥንቸልም እየተዘዋወረች ቅጠል መበጠሷን ትቀጥላለች። ጥቂት እንደሄደች ዝንጀሮ እንደፈራው አንድ በቅጠል የተሸፈነ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ሳታስበው ትወድቃለች። ጉድጓዱ በጣም ጥልቀት ያለው በመሆኑ ልትወጣበት የምትችልበት አይደለም። ስለዚህ አላፊ አግዳሚውን እንዲያወጣት ለመለመን ተገደደች።
እባካችሁ አውጡኝ፣ እርዱኝ እያለች ስትጮህ ተኩላ ድምጿን ይሰማና ወደ ጉድጓዱ አፍ ይሄዳል። አጎንብሷም ወደ ጥንቸሏ ያይ ጀመር ።
ጥንቸልም " አያ ተኩላ እባክህ ዘወር በል ይሄ ጉድጓድ ለሁለታችንም አይበቃንም አንተ ያለህበት ቦታ እንደበረሃ የሚያቃጥል አየር ነው ያለው እዚህ ግን በጣም ነፋሻና ቀዝቀዝ ያለ አየር ነው ያለው ለእኔ በጣም ተስማምቶኛል ሆኖም ወደዚህ መውረድ ብትችል እንኳን ለ2 አይበቃንም" አለችው።
ተኩላው የጥንቸሏ ንግግር በጣም አጓጓውና "ልውረድስ ብል በምን እወርዳለሁ" ሲል ጠየቃት።
ጥንቸልም "እዚያጉድጓድ አፍ አጠገብ አንድ በገመድ የታሰረ ባሊ አለልህ ባሊ ውስጥ ገብተህ በገመዱ ተንሸራተህ መውረድ ትችላለህ" አለችው
እውነትም አንድ ባሊ አጠገቡ እንዳለ አየ ባሊው ወደታች ሲወርድ ጉድጓድ ውስጥ ያለው ገመድ ጫፍ ወደ ላይ የሚወጣ ነው(እንደ ፑሊ የሚሠራ ገመድ ነው) ጉድጓዱ ውስጥ ያለውን ጫፍ ጥንቸሏ ይዛለች።
አያ ተኩላ ባሊ ውስጥ ገብቶ ቁልቁል ተምዘግዝጎ ሲወርድ ጥንቸል የገመዱን ጫፍ ይዛ ወደ ላይ ወጣች። እሱ እየወረደ እሷ እየወጣች መንገድ ሲተላለፉ ከት ብላ እየሳቀች "አየህ አያ ተኩላ፣ ህይወት ማለት እንደዚህ ናት አንዱ ሲወርድ አንዱ ይወጣል" አለችው። ተኩላው መሬት ሲደርስ ጥንቸሏ ጉድጓዱ አፋፍ ላይ ወጣች።
😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊
አንዳንድ ሰዎች ችግር ውስጥ ሲገቡ ሌላውን እዛ ውስጥ ከትተው እራሳቸውን ለማዳን ይሞክራሉ።
እዛው ጉድጓድ ውስጥ የሚገቡት ሞኞች ደግሞ በአልጠግብ ባይነታቸው ነው
አደጋን ከሩቅ አይተው የሚያስጠነቅቁ እንደ ዝንጀሮ ያሉ አስተዋዮች ሊኖሩ ያስፈልጋል
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
@Venisiya21 @Venisiya21
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
እመት ጥንቸል የረዥም ጊዜ ወዳጅነታችንን መሠረት በማድረግ ምክር ልለግስሽ እፈልጋለሁ አላት
ጥንቸልም ምን ዓይነት ምክር? ስትል ጠየቀችው ዝንጀሮውም ይህን ጫካ አትመኝው ሰሞኑን አዳኞች መጥተው ለአውሬ ማጥመጃ የሚሆን ትላልቅ ጉድጓድ ሲቆፍሩ እኔ ዛፍ ላይ ሆኜ አይቻለሁ ስለዚህ ጫካው እንደድሮው ሰላም መስሎሽ ወዲያ ወዲህ አትበይ።
ጥንቸልም "አመሰግናለሁ ወጥመዱን የሠሩት ለእኔ አይመስለኝም። እንደ አንበሳና እንደ ነብር ላሉት እንጂ እንደኔ ቀጫጫ ለሆኑ ፍጡር አይደለም። ባጋጣሚ ጉድጓድ ውስጥ ብወድቅም መውጫ ብልሃት አላጣም! ትለዋለች።
ዝንጀሮም "እንግዲህ የወንድምነቴን መክሬሻለሁ፤ ብታውቂ እወቂበት" አላትና ሄደ። ጥንቸልም እየተዘዋወረች ቅጠል መበጠሷን ትቀጥላለች። ጥቂት እንደሄደች ዝንጀሮ እንደፈራው አንድ በቅጠል የተሸፈነ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ሳታስበው ትወድቃለች። ጉድጓዱ በጣም ጥልቀት ያለው በመሆኑ ልትወጣበት የምትችልበት አይደለም። ስለዚህ አላፊ አግዳሚውን እንዲያወጣት ለመለመን ተገደደች።
እባካችሁ አውጡኝ፣ እርዱኝ እያለች ስትጮህ ተኩላ ድምጿን ይሰማና ወደ ጉድጓዱ አፍ ይሄዳል። አጎንብሷም ወደ ጥንቸሏ ያይ ጀመር ።
ጥንቸልም " አያ ተኩላ እባክህ ዘወር በል ይሄ ጉድጓድ ለሁለታችንም አይበቃንም አንተ ያለህበት ቦታ እንደበረሃ የሚያቃጥል አየር ነው ያለው እዚህ ግን በጣም ነፋሻና ቀዝቀዝ ያለ አየር ነው ያለው ለእኔ በጣም ተስማምቶኛል ሆኖም ወደዚህ መውረድ ብትችል እንኳን ለ2 አይበቃንም" አለችው።
ተኩላው የጥንቸሏ ንግግር በጣም አጓጓውና "ልውረድስ ብል በምን እወርዳለሁ" ሲል ጠየቃት።
ጥንቸልም "እዚያጉድጓድ አፍ አጠገብ አንድ በገመድ የታሰረ ባሊ አለልህ ባሊ ውስጥ ገብተህ በገመዱ ተንሸራተህ መውረድ ትችላለህ" አለችው
እውነትም አንድ ባሊ አጠገቡ እንዳለ አየ ባሊው ወደታች ሲወርድ ጉድጓድ ውስጥ ያለው ገመድ ጫፍ ወደ ላይ የሚወጣ ነው(እንደ ፑሊ የሚሠራ ገመድ ነው) ጉድጓዱ ውስጥ ያለውን ጫፍ ጥንቸሏ ይዛለች።
አያ ተኩላ ባሊ ውስጥ ገብቶ ቁልቁል ተምዘግዝጎ ሲወርድ ጥንቸል የገመዱን ጫፍ ይዛ ወደ ላይ ወጣች። እሱ እየወረደ እሷ እየወጣች መንገድ ሲተላለፉ ከት ብላ እየሳቀች "አየህ አያ ተኩላ፣ ህይወት ማለት እንደዚህ ናት አንዱ ሲወርድ አንዱ ይወጣል" አለችው። ተኩላው መሬት ሲደርስ ጥንቸሏ ጉድጓዱ አፋፍ ላይ ወጣች።
😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊
አንዳንድ ሰዎች ችግር ውስጥ ሲገቡ ሌላውን እዛ ውስጥ ከትተው እራሳቸውን ለማዳን ይሞክራሉ።
እዛው ጉድጓድ ውስጥ የሚገቡት ሞኞች ደግሞ በአልጠግብ ባይነታቸው ነው
አደጋን ከሩቅ አይተው የሚያስጠነቅቁ እንደ ዝንጀሮ ያሉ አስተዋዮች ሊኖሩ ያስፈልጋል
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
@Venisiya21 @Venisiya21
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
+ በእግዚአብሔር መንግሥት አንድ ቀን +
ጸአተ ነፍስ (The departure of Soul) ከተሰኘው የኦርቶዶክስ ቴዎሎጂ ምሁራን የጋራ
ሥራ የሆነ ዳጎስ ያለ ድንቅ መጽሐፍ መግቢያ ላይ አንድ አባት ስለ አንድ ሰው ታሪክ የጻፉት
ነገር በጣም አስገራሚ ሆነብኝ:: እጅግ መጥፎ የነበረ አንድ ሰው ድንገት በጠና ይታመምና
በአልጋ ላይ ይውላል:: ሕመሙ እጅግ የጠና ቢሆንም የማይገድለው ሆነና ለሠላሳ ዓመታት
ተሠቃየ:: በክፉ አመል ላይ ክፉ ሕመም ተጨምሮ ለሌሎችም ችግር ሆነ:: በአልጋው ላይ
ሆኖም ደጋግሞ ሰውንም ፈጣሪውንም ይሳደብ ነበር::
ከሠላሳ ዓመታት ሥቃይ በኁዋላ ግን ይህ ሰው ነፍሱ ከሥጋው ተለየች:: የመንደሩ ሰው
ተሰበሰበና ማልቀስ ጀመረ:: "ውይ ተገላገለ" "ይኼ ክፉ አረፈ? ያረፍነውስ እኛም ነን!"
እያለ በልቡ እያሸሞረ ቁጭ አለ:: አጅሬው ግን ሞተ ከተባለ ሦስት ሰዓታት ቆይታ በኁዋላ
ድንገት እንደ እንቅልፍ ነቃ:: ሰዉ ድንጋጤም ደስታም ተቀላቅሎበት ተቀበለው::
ከዚያች ዕለት ጀምሮ ሞገደኛው ሰው እንደቀደመው መናከሱን ትቶ ትሑት ለሰው አዛኝ ሆኖ
አረፈው:: የጠሉት ሁሉ ይቅርታ እስኪያደርጉለት ድረስ እጅግ መልካም ሰው ሆነ:: አንድ
አባት በሰውዬው መለወጥ ተደንቆ ሞቶ በነበረበት ጊዜ ምን እንደገጠመው ጠየቀው::
እርሱም
እንዲህ አለ :-
"ከሞትሁ በኁዋላ ለሦስት ሰዓታት ያህል በሲኦል ሥቃይ ውስጥ ቆይቼ ነበር:: በሲኦል
ካሳለፍሁት የሦስት ሰዓታት ሥቃይ የምድር ላይ የሠላሳ ዓመት ሥቃይ እጅግ ይሻለኛል::
በሲኦል ሦስት ሰዓት ከመቆየት በምድር ላይ የዕድሜ ልክ ሥቃይ ይሻላል"
በእርግጥ የሲኦል የአንድ ሰዓት ሥቃይ ከዚህ ዓለም የዐሥር ዓመት ሥቃይ ከበለጠ ከዚህ
ዓለም የዕድሜ ልክ ደስታም የመንግሥተ ሰማያት የአንዲት ቀን ደስታ ይበልጣል::
ንጉሥ ዳዊት "ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች" እንዳለ በመንግሥተ
ሰማያት አንዲት ቀን መቆየት ደግሞ በዚህ ምድር ላይ ሺህ ዓመት ከመደሰት ይበልጣል::
“በዚህ ዓለም ብዙ ዘመን ከመኖር በገነት አንዲት ቀን ደስ መሰኘት ይሻላል:: ከብዙ
ዘመኖችም አቤቱ ይቅርታህን ማግኘት ይሻላል" 2 መቃ. 13:4
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
@Venisiya21 @Venisiya21
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
ጸአተ ነፍስ (The departure of Soul) ከተሰኘው የኦርቶዶክስ ቴዎሎጂ ምሁራን የጋራ
ሥራ የሆነ ዳጎስ ያለ ድንቅ መጽሐፍ መግቢያ ላይ አንድ አባት ስለ አንድ ሰው ታሪክ የጻፉት
ነገር በጣም አስገራሚ ሆነብኝ:: እጅግ መጥፎ የነበረ አንድ ሰው ድንገት በጠና ይታመምና
በአልጋ ላይ ይውላል:: ሕመሙ እጅግ የጠና ቢሆንም የማይገድለው ሆነና ለሠላሳ ዓመታት
ተሠቃየ:: በክፉ አመል ላይ ክፉ ሕመም ተጨምሮ ለሌሎችም ችግር ሆነ:: በአልጋው ላይ
ሆኖም ደጋግሞ ሰውንም ፈጣሪውንም ይሳደብ ነበር::
ከሠላሳ ዓመታት ሥቃይ በኁዋላ ግን ይህ ሰው ነፍሱ ከሥጋው ተለየች:: የመንደሩ ሰው
ተሰበሰበና ማልቀስ ጀመረ:: "ውይ ተገላገለ" "ይኼ ክፉ አረፈ? ያረፍነውስ እኛም ነን!"
እያለ በልቡ እያሸሞረ ቁጭ አለ:: አጅሬው ግን ሞተ ከተባለ ሦስት ሰዓታት ቆይታ በኁዋላ
ድንገት እንደ እንቅልፍ ነቃ:: ሰዉ ድንጋጤም ደስታም ተቀላቅሎበት ተቀበለው::
ከዚያች ዕለት ጀምሮ ሞገደኛው ሰው እንደቀደመው መናከሱን ትቶ ትሑት ለሰው አዛኝ ሆኖ
አረፈው:: የጠሉት ሁሉ ይቅርታ እስኪያደርጉለት ድረስ እጅግ መልካም ሰው ሆነ:: አንድ
አባት በሰውዬው መለወጥ ተደንቆ ሞቶ በነበረበት ጊዜ ምን እንደገጠመው ጠየቀው::
እርሱም
እንዲህ አለ :-
"ከሞትሁ በኁዋላ ለሦስት ሰዓታት ያህል በሲኦል ሥቃይ ውስጥ ቆይቼ ነበር:: በሲኦል
ካሳለፍሁት የሦስት ሰዓታት ሥቃይ የምድር ላይ የሠላሳ ዓመት ሥቃይ እጅግ ይሻለኛል::
በሲኦል ሦስት ሰዓት ከመቆየት በምድር ላይ የዕድሜ ልክ ሥቃይ ይሻላል"
በእርግጥ የሲኦል የአንድ ሰዓት ሥቃይ ከዚህ ዓለም የዐሥር ዓመት ሥቃይ ከበለጠ ከዚህ
ዓለም የዕድሜ ልክ ደስታም የመንግሥተ ሰማያት የአንዲት ቀን ደስታ ይበልጣል::
ንጉሥ ዳዊት "ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች" እንዳለ በመንግሥተ
ሰማያት አንዲት ቀን መቆየት ደግሞ በዚህ ምድር ላይ ሺህ ዓመት ከመደሰት ይበልጣል::
“በዚህ ዓለም ብዙ ዘመን ከመኖር በገነት አንዲት ቀን ደስ መሰኘት ይሻላል:: ከብዙ
ዘመኖችም አቤቱ ይቅርታህን ማግኘት ይሻላል" 2 መቃ. 13:4
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
@Venisiya21 @Venisiya21
•••••••••••••፨፨♥፨፨•••••••••••••••
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
#ጾመ_ዮዲት
በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡
የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በዓዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡
በዚያም ነዋሪዎችን በማስፈራራት የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበሉትን ሁሉ እያሳደደ ስላስጨነቃቸው ማቅ ለብሰው፣ አመድ ነስንሰውና ድንጋይ ተንተርሰው ወደ ፈጣሪያቸው በመጮህ መለመን ጀመሩ። በጭካኔ የተሞላው የጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስም ይበልጥ እጅግ እንዲሰቃዩ ውኃ የሚቀዱበትን ስፍራ ተቆጣጠረው፤ በግዴታ ማርኮም እጅ እንዲሰጡ እንዳደረጋቸው በመጽሐፈ ዮዲት ፪፥፪ ላይ ተጽፏል፡፡
በአካባቢው ይኖር የነበረ ዖዝያን የተባለ አንድ ሰው የአባቶቻቸው አምላክ ጸሎታቸውን እንዲሰማቸው ለአምስት ቀናት በትዕግሥት ይጾሙና ይጸልዩ ዘንድ ሕዝቡን መከራቸው፤ እነርሱም በትዕግሥት ሊጠብቁ ተስማሙ፡፡
የእስራኤል ልጆች የናቡከደነጾርን ጦር ብንችል ተዋግተን እንረታለን፤ ካልሆነም እጅ እንሰጣለን በማለት ይመካከሩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ባሏ የሞተባትና በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ዮዲት የተባለች ሴት ነበረች። (ዮዲት ፯፥፲)
እግዚአብሔርን የምትፈራ ብቸኛዋ ሴት እርሷ ነበረችና ምክክራቸውን ስትሰማ ለምን «እግዚአብሔር ያድነናል አትሉም» ብላ ገሠጸቻቸው፡፡
ማቅ በመልበስ፣ አመድ በመነስነስና ድንጋይ በመንተራስም ሱባኤ ገባች። በሦስተኛው ቀንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቧን የምታድንበትን ጥበብ ገለጸላት፤ ዮዲትም እግዚአብሔር የሰጣትን ውበት ተጠቅማ ሕዝቧን ከጥፋት የምትታደግበትን ጥበብ ተረዳች።
የክት ልብሷን ለብሳ፣ ሽቱ ተቀብታና ተውባ የጠላት ሠራዊት ወዳሉበት የጦር ሰፈር በድፍረት አመራች፡፡ ሠራዊቱም ውበቷን አይተው እጅግ በመደነቅ «ይህችስ ለአለቃችን ትገባለች» ተባብለው ከጦር መሪያቸው ዘንድ ወሰዷት።
እርሷም ቀድማ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅታ ነበርና ወደ አዛዡ ከገባች በኋላ «ክቡር ጌታዬ ሆይ ርስት ተወስዶብኛል፤ እንድትመልስልኝ አስቀድሜ ደጅ ልጠና መጥቻለውና ርዳኝ፤ ትብብርህ አይለየኝ» አለችው፡፡ በስሜት ፈረስ ታውሮ የነበረው የሠራዊቶቹ አዛዥም የጠየቀችውን እንደሚፈጽምላት ቃል ገባላት።
ባማረ ድንካን እንዲያስቀምጧት ሎሌዎቹን አዘዘ። ዮዲትም የተሰጣትን ጥበብ ተጠቅማ፣ መውጣት ስትፈልግ የምትወጣበትን እና የምትገባበትን ዕድል በእግዚአብሔር አጋዥነት ዐወቀች፡፡ ከቀናት በኃላ የጦር አበጋዙ ለሠራዊቱ የምሳ ግብዣ አዘጋጅቶ ዮዲትን ከጎኑ አስቀመጣት፤ ከበሉና ከጠጡ በኋላም ሁሉን ሰው አስወጣ፤ እልፍኙን በመዝጋት ከእርሷ ጋር ብቻውን ሆነ፤ ነገር ግን እንቅልፍ ጣለው፡፡ (ዮዲት ፰፥፪)
እርሷም ወደ አምላኳ ጸለየች፤ ፈጣሪዋ እንዲረዳትም አጥብቃ ለመነች። በኋላም ከራስጌው ሰይፍ አንስታ አንገቱን ቀላችው፤ በድኑንም ከመሬት ጣለችው። የሆሎፎርኒስን ሞት ሠራዊቱ ሲሰሙ አውራ እንደሌለው ንብ ተበተኑ፤ ከፊሎቹ ሞቱ።
እስራኤላውያንም ከሞት ተርፈው በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረጉ፤ በደስታም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ።
ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ የሚያስረዳን ዮዲት ጠላቶቿን ድል ያደረገችው በጾምና በጸሎት እንደሆነ ነው፡፡
ለእኛም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ምንም እንኳ ወርኃ ጳጉሜን የፈቃድ ጾም ቢሆንም በሀገራችን የተጋረጠውን ችግር እናልፍ ዘንድ በፈቃደኝነት እንጾማለን። እግዚአብሔር አምላካችን ለሁላችንም ጥበብ ሰጥቶናል።
ይህም ችግሮችን ሁሉ የምንፈታበት መንገድ ነው። በዚህም የዓመተ መሸጋገሪያና የክረምቱ ወር ማብቂያ በመሆኑ ዕለተ ምጽአት ስለሚታሰብበት በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ከሌሊት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ተገኝተን ጠበል በመጠመቅ፣ በማስቀደስና በመጸለይ እንዲሁም ሥጋ ወደሙን በመቀበል ልናሳልፍ ይገባል።
ዕለተ ምጽአትም ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው ዓለም መሸጋገሪያችን ነውና በቀኙ እንቆም ዘንድ እንጾማለን፡፡
የሚመጣውን አዲስ ዘመንም በንጽሕና ለመቀበል ስላለፈው ዓመት ኃጢአታችን ንስሓ የምንገባበት ጾምም ነው።
ከተጋረጠብን ችግር «እግዚአብሔር ያድነናል» በማለት ልክ እንደ ዮዲት ሱባኤ ገብተን፣ ማቅ ለብሰን፣ አመድ ነስንሰንና ድንጋይ ተንተርሰን አብዝተን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባል፡፡ ሊለያየን፣ ሊነጣጥለን፣ ሊበታትነን እና ሊገድለን ካሰበው እንዲሁም ፍቅርን፣ መተሳሰብንና አንድነትን ሊነፍገን ከቃጣው ጠላትና ሃይማኖታችንን ሊያስተወን ከሚመጣ ፀረ ሃይማኖት እንድናለን።
ስለዚህ ከፊታችን ያለችውን ስድስቱን የጳጉሜን ቀን በፍቅር፣ በአንድነትና በሃይማኖት ጸንተን፣ ጾመን፣ ጸልየን ለዘመነ ማቴዎስ እንድንደርስ እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን፤ አሜን።
ምንጭ፦ ከማኅበረ ቅዱሳን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ጾመ_ዮዲት
በናቡከደነጾር ዘመነ መንግሥት ንጉሡ ሥልጣኑን መከታ በማድረግ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በግድ እያስገደደ እጅ መንሻ ይቀበል ነበር፡፡
የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበለውንም እየገደለ፣ ጭፍሮቹ ኃያልነቱንና ገናናነቱን በዓዋጅ በጦር አዛዦች ጭምር እያሳወጀ፣ በርካታ የጦር ሠራዊቶችን አሰልፎ ከአይሁድ ከተማ ገባ፡፡
በዚያም ነዋሪዎችን በማስፈራራት የመንግሥቱን ትእዛዝ ያልተቀበሉትን ሁሉ እያሳደደ ስላስጨነቃቸው ማቅ ለብሰው፣ አመድ ነስንሰውና ድንጋይ ተንተርሰው ወደ ፈጣሪያቸው በመጮህ መለመን ጀመሩ። በጭካኔ የተሞላው የጦር አበጋዙ ሆሎፎርኒስም ይበልጥ እጅግ እንዲሰቃዩ ውኃ የሚቀዱበትን ስፍራ ተቆጣጠረው፤ በግዴታ ማርኮም እጅ እንዲሰጡ እንዳደረጋቸው በመጽሐፈ ዮዲት ፪፥፪ ላይ ተጽፏል፡፡
በአካባቢው ይኖር የነበረ ዖዝያን የተባለ አንድ ሰው የአባቶቻቸው አምላክ ጸሎታቸውን እንዲሰማቸው ለአምስት ቀናት በትዕግሥት ይጾሙና ይጸልዩ ዘንድ ሕዝቡን መከራቸው፤ እነርሱም በትዕግሥት ሊጠብቁ ተስማሙ፡፡
የእስራኤል ልጆች የናቡከደነጾርን ጦር ብንችል ተዋግተን እንረታለን፤ ካልሆነም እጅ እንሰጣለን በማለት ይመካከሩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ባሏ የሞተባትና በንጽሕና ተጠብቃ፣ በጸሎትና በሕገ እግዚአብሔር የምትኖር ዮዲት የተባለች ሴት ነበረች። (ዮዲት ፯፥፲)
እግዚአብሔርን የምትፈራ ብቸኛዋ ሴት እርሷ ነበረችና ምክክራቸውን ስትሰማ ለምን «እግዚአብሔር ያድነናል አትሉም» ብላ ገሠጸቻቸው፡፡
ማቅ በመልበስ፣ አመድ በመነስነስና ድንጋይ በመንተራስም ሱባኤ ገባች። በሦስተኛው ቀንም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቧን የምታድንበትን ጥበብ ገለጸላት፤ ዮዲትም እግዚአብሔር የሰጣትን ውበት ተጠቅማ ሕዝቧን ከጥፋት የምትታደግበትን ጥበብ ተረዳች።
የክት ልብሷን ለብሳ፣ ሽቱ ተቀብታና ተውባ የጠላት ሠራዊት ወዳሉበት የጦር ሰፈር በድፍረት አመራች፡፡ ሠራዊቱም ውበቷን አይተው እጅግ በመደነቅ «ይህችስ ለአለቃችን ትገባለች» ተባብለው ከጦር መሪያቸው ዘንድ ወሰዷት።
እርሷም ቀድማ ማምለጫ መንገድ አዘጋጅታ ነበርና ወደ አዛዡ ከገባች በኋላ «ክቡር ጌታዬ ሆይ ርስት ተወስዶብኛል፤ እንድትመልስልኝ አስቀድሜ ደጅ ልጠና መጥቻለውና ርዳኝ፤ ትብብርህ አይለየኝ» አለችው፡፡ በስሜት ፈረስ ታውሮ የነበረው የሠራዊቶቹ አዛዥም የጠየቀችውን እንደሚፈጽምላት ቃል ገባላት።
ባማረ ድንካን እንዲያስቀምጧት ሎሌዎቹን አዘዘ። ዮዲትም የተሰጣትን ጥበብ ተጠቅማ፣ መውጣት ስትፈልግ የምትወጣበትን እና የምትገባበትን ዕድል በእግዚአብሔር አጋዥነት ዐወቀች፡፡ ከቀናት በኃላ የጦር አበጋዙ ለሠራዊቱ የምሳ ግብዣ አዘጋጅቶ ዮዲትን ከጎኑ አስቀመጣት፤ ከበሉና ከጠጡ በኋላም ሁሉን ሰው አስወጣ፤ እልፍኙን በመዝጋት ከእርሷ ጋር ብቻውን ሆነ፤ ነገር ግን እንቅልፍ ጣለው፡፡ (ዮዲት ፰፥፪)
እርሷም ወደ አምላኳ ጸለየች፤ ፈጣሪዋ እንዲረዳትም አጥብቃ ለመነች። በኋላም ከራስጌው ሰይፍ አንስታ አንገቱን ቀላችው፤ በድኑንም ከመሬት ጣለችው። የሆሎፎርኒስን ሞት ሠራዊቱ ሲሰሙ አውራ እንደሌለው ንብ ተበተኑ፤ ከፊሎቹ ሞቱ።
እስራኤላውያንም ከሞት ተርፈው በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረጉ፤ በደስታም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ።
ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ የሚያስረዳን ዮዲት ጠላቶቿን ድል ያደረገችው በጾምና በጸሎት እንደሆነ ነው፡፡
ለእኛም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ምንም እንኳ ወርኃ ጳጉሜን የፈቃድ ጾም ቢሆንም በሀገራችን የተጋረጠውን ችግር እናልፍ ዘንድ በፈቃደኝነት እንጾማለን። እግዚአብሔር አምላካችን ለሁላችንም ጥበብ ሰጥቶናል።
ይህም ችግሮችን ሁሉ የምንፈታበት መንገድ ነው። በዚህም የዓመተ መሸጋገሪያና የክረምቱ ወር ማብቂያ በመሆኑ ዕለተ ምጽአት ስለሚታሰብበት በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ከሌሊት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ተገኝተን ጠበል በመጠመቅ፣ በማስቀደስና በመጸለይ እንዲሁም ሥጋ ወደሙን በመቀበል ልናሳልፍ ይገባል።
ዕለተ ምጽአትም ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው ዓለም መሸጋገሪያችን ነውና በቀኙ እንቆም ዘንድ እንጾማለን፡፡
የሚመጣውን አዲስ ዘመንም በንጽሕና ለመቀበል ስላለፈው ዓመት ኃጢአታችን ንስሓ የምንገባበት ጾምም ነው።
ከተጋረጠብን ችግር «እግዚአብሔር ያድነናል» በማለት ልክ እንደ ዮዲት ሱባኤ ገብተን፣ ማቅ ለብሰን፣ አመድ ነስንሰንና ድንጋይ ተንተርሰን አብዝተን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባል፡፡ ሊለያየን፣ ሊነጣጥለን፣ ሊበታትነን እና ሊገድለን ካሰበው እንዲሁም ፍቅርን፣ መተሳሰብንና አንድነትን ሊነፍገን ከቃጣው ጠላትና ሃይማኖታችንን ሊያስተወን ከሚመጣ ፀረ ሃይማኖት እንድናለን።
ስለዚህ ከፊታችን ያለችውን ስድስቱን የጳጉሜን ቀን በፍቅር፣ በአንድነትና በሃይማኖት ጸንተን፣ ጾመን፣ ጸልየን ለዘመነ ማቴዎስ እንድንደርስ እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን፤ አሜን።
ምንጭ፦ ከማኅበረ ቅዱሳን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
+ እግዚአብሔርን ለምን - አልለምንም! +
‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለው ትንቢት ከመነገሩ አስቀድሞ ምክንያት የሆነ አንድ ክስተት ይህ ነበር፡፡
የይሁዳ ንጉሥ አካዝ ዙሪያውን በጠላቶች ተከብቦ ነበር፡፡ ሁለት ነገሥታት ሊወጉትና ኢየሩሳሌምን ሊወርሯት አሰፍስፈው እየጠበቁ ነው፡፡ የጦር ምክራቸውም ‘ወደ ይሁዳ እንውጣ እናስጨንቀው እንስበረው በላዩ ላይም ሌላ ንጉሥ እናንግሥበት’ የሚል ነበር፡፡ ይህን ምክራቸውን አስቀድሞ ይነግረው ዘንድ እግዚአብሔር ነቢዩ ኢሳይያስን ወደ ንጉሥ አካዝ ላከው፡፡ ኢሳይያስም የሚመጣበትን የጠላት ከበባና መጻኢ ፈተናውን ነገረው፡፡
እንደመፍትሔም እንዲህ አለው ‘ከጥልቁም ወይም ከከፍታውም ከእግዚአብሔር ምልክትን ለምን’ የሚል ምክር ነበር፡፡ እግዚአብሔር ወይ ከሰማይ ወይ ከምድር አንዳች ተአምር አድርጎ ከዚህ ጭንቅ እንዲያወጣህ ፈጣሪህን ለምን ብሎ የነገረው ከእግዚአብሔር በቀጥታ የተላከው ነቢይ ነበር፡፡ ‘’ለምነኝ አሕዛብን ለርስትህ እሰጥሃለሁ’ እንደማለት ያለ ዕድል ቀርቦለት ነበር፡፡
ንጉሥ አካዝ ግን ግልጽ እና አጭር ምላሽ ሠጠ ፦ አልለምንም ፤ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም! /ኢሳ 7፡13/
እርግጥ ነው በኦሪት ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፎአል፡፡ ራሱ እግዚአብሔር ነቢዩን ልኮ ለምነኝ ተአምር ልፈጽምልህ እያለህ ‘አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’ ማለት ግን በራሱ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡
ንጉሥ አካዝ እንዲህ በጠላት ተከብቦ እያለ ‘ወደ ፈጣሪ ለምን’ ሲባል እምቢ ያለው እርሱ እንዳለው እግዚአብሔርን ላለመፈታተን አልነበረም፡፡ በዚያ ጦርነት እንዲረዳው ወደ አሶር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር መልእክተኛ ልኮበት ስለነበር ነው፡፡ በታላላቅ ተአምራት ሕዝቡን የታደገ እግዚአብሔርን እንዲለምን ጥሪ እየቀረበለት አካዝ ግን ከፈጣሪ ይልቅ በአሶር ንጉሥ እርዳታ ተስፋ አድርጎ ነበር፡፡ ኢሳይያስም ጸልይ ሲለው የልቡን ሃሳብ ደብቆ ፣ ከፈጣሪ ይልቅ በሰው ለመመካቱም መንፈሳዊ ካባን አልብሶ ‘ፈጣሪን አልፈታተንም’ ብሎ ተናገረ፡፡
አካዝ ይረዳኛል ብሎ የተማመነበት በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ ርዝመት ሁለተኛ የሆነው ቴልጌልቴልፌልሶር በጥያቄው መሠረት ወደ ይሁዳ ቢመጣም እንኳን አስጨነቀው እንጂ አልረዳውም፡፡ ይረዳኛል ብሎ ከቤተ መንግሥቱ ፣ ከመኳንንቱ ግማሹን አሳልፎ ለአሶር ንጉሥ እስከመሥጠት ቢደርስም ቴልጌልቴልፌልሶር ግን እንደ ስሙ የተንዛዛ ቆይታ ቆይቶ በዘበዘው፡፡ ችግር በመፍታት ፈንታ ችግር ሆነበት ፤ አካዝም በዚህ ተበሳጭቶ ‘ለምነኝ‘ ብሎ ሲጠይቀው አልፈልግም ያለውን እግዚአብሔርን መንቀፍ ጀመረ፡፡ ጭራሽ ጠላቶቼ እኔን ድል ያደረጉት አማልክቶቻቸው ከእኔ አምላክ ቢበልጡ ነው ብሎ ለጠላቶቹ አማልክት መሥዋዕት አቀረበ፡፡ መጨረሻውም እጅግ የከፋ ሆነ፡፡ /2ዜና 28፡20/
‘’አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’’ ብዙ ጊዜ የእምነታችንን ማነስ የምንደብቅባት ሽፋን ናት፡፡ ሀገር ሲታመስ ፣ መከራ ሲጸና ፣ ነገሮች ድብልቅልቅ ሲሉ ፣ ጠላት ከግራና ቀኝ ሲበዛ ምንድን ነው መፍትሔው? አካዝን ለምነኝ ያለ አምላክ ለእኛም ‘‘በመከራህ ቀን ጥራኝ እኔም አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ’’ ብሏል፡፡ /መዝ 49፡15/ በደስታችን ቀን ትዝ ብሎን የማያውቀው ፈጣሪያችን ግድ የለም በመከራህ ቀን ጥራኝ ብሎ ለሁላችን ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምንም ዓይነት ፈተና በግላችን ፣ በሀገራችንና በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ሲመጣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መፍትሔዋ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ከእግዚአብሔር መለመን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ዕንባዋን ትረጫለች ፤ የኃያላን ኃያል ፣ ብርቱዎችን ከዙፋናቸው የሚያዋርድ ፣ ትዕቢተኞችን የሚሰብር አምላክ እንዲደርስላት እንደ ኢሳይያስ የፈጣሪ አንደበት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ጸልዩ ትላለች፡፡
ይህን ጊዜ አካዞች እንበሳጫለን ‘አልለምንም ፣ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም’ እንላለን ቤተክርስቲያንን የላካት ኢሳይያስን የላከው አምላክ መሆኑን አናስተውልም፡፡ የጾም ፣ ጸሎት ፣ ስግደት ፣ ምሕላ ጥቅም አይታየንም፡፡ ሌላ መፍትሔ መፈለግ ነው እንጂ ዝም ብሎ ወደ ሰማይ በማንጋጠጥ ጊዜ ማጥፋት የለብንም እንላለን በሆዳችን፡፡ አፋችን ግን ለታዛቢ ይጠነቀቃል ስለዚህ ‘ዝም ብሎ መጸለይማ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው’ እንላለን፡፡ እነ እገሌ ቢረዱን ብለን የምናስባቸው ቴልጌልቴልፌልሶሮች ብዙ ናቸው፡፡ ማናቸውም ግን መጥተው ያስጨንቁናል እንጂ አይረዱንም፡፡ ሰውን ተስፋ ከማድረግ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ብንለምን ጥሩ ነው፡፡
እኛ ባንለምንም ግን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሚሆን እንዲህ ብሎ ተጽፎአል፦
ጌታ ራሱ ምልክትን ይሠጣችኋል ፤ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ይሉታል /ኢሳ 7፡14/
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለው ትንቢት ከመነገሩ አስቀድሞ ምክንያት የሆነ አንድ ክስተት ይህ ነበር፡፡
የይሁዳ ንጉሥ አካዝ ዙሪያውን በጠላቶች ተከብቦ ነበር፡፡ ሁለት ነገሥታት ሊወጉትና ኢየሩሳሌምን ሊወርሯት አሰፍስፈው እየጠበቁ ነው፡፡ የጦር ምክራቸውም ‘ወደ ይሁዳ እንውጣ እናስጨንቀው እንስበረው በላዩ ላይም ሌላ ንጉሥ እናንግሥበት’ የሚል ነበር፡፡ ይህን ምክራቸውን አስቀድሞ ይነግረው ዘንድ እግዚአብሔር ነቢዩ ኢሳይያስን ወደ ንጉሥ አካዝ ላከው፡፡ ኢሳይያስም የሚመጣበትን የጠላት ከበባና መጻኢ ፈተናውን ነገረው፡፡
እንደመፍትሔም እንዲህ አለው ‘ከጥልቁም ወይም ከከፍታውም ከእግዚአብሔር ምልክትን ለምን’ የሚል ምክር ነበር፡፡ እግዚአብሔር ወይ ከሰማይ ወይ ከምድር አንዳች ተአምር አድርጎ ከዚህ ጭንቅ እንዲያወጣህ ፈጣሪህን ለምን ብሎ የነገረው ከእግዚአብሔር በቀጥታ የተላከው ነቢይ ነበር፡፡ ‘’ለምነኝ አሕዛብን ለርስትህ እሰጥሃለሁ’ እንደማለት ያለ ዕድል ቀርቦለት ነበር፡፡
ንጉሥ አካዝ ግን ግልጽ እና አጭር ምላሽ ሠጠ ፦ አልለምንም ፤ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም! /ኢሳ 7፡13/
እርግጥ ነው በኦሪት ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፎአል፡፡ ራሱ እግዚአብሔር ነቢዩን ልኮ ለምነኝ ተአምር ልፈጽምልህ እያለህ ‘አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’ ማለት ግን በራሱ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡
ንጉሥ አካዝ እንዲህ በጠላት ተከብቦ እያለ ‘ወደ ፈጣሪ ለምን’ ሲባል እምቢ ያለው እርሱ እንዳለው እግዚአብሔርን ላለመፈታተን አልነበረም፡፡ በዚያ ጦርነት እንዲረዳው ወደ አሶር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር መልእክተኛ ልኮበት ስለነበር ነው፡፡ በታላላቅ ተአምራት ሕዝቡን የታደገ እግዚአብሔርን እንዲለምን ጥሪ እየቀረበለት አካዝ ግን ከፈጣሪ ይልቅ በአሶር ንጉሥ እርዳታ ተስፋ አድርጎ ነበር፡፡ ኢሳይያስም ጸልይ ሲለው የልቡን ሃሳብ ደብቆ ፣ ከፈጣሪ ይልቅ በሰው ለመመካቱም መንፈሳዊ ካባን አልብሶ ‘ፈጣሪን አልፈታተንም’ ብሎ ተናገረ፡፡
አካዝ ይረዳኛል ብሎ የተማመነበት በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ ርዝመት ሁለተኛ የሆነው ቴልጌልቴልፌልሶር በጥያቄው መሠረት ወደ ይሁዳ ቢመጣም እንኳን አስጨነቀው እንጂ አልረዳውም፡፡ ይረዳኛል ብሎ ከቤተ መንግሥቱ ፣ ከመኳንንቱ ግማሹን አሳልፎ ለአሶር ንጉሥ እስከመሥጠት ቢደርስም ቴልጌልቴልፌልሶር ግን እንደ ስሙ የተንዛዛ ቆይታ ቆይቶ በዘበዘው፡፡ ችግር በመፍታት ፈንታ ችግር ሆነበት ፤ አካዝም በዚህ ተበሳጭቶ ‘ለምነኝ‘ ብሎ ሲጠይቀው አልፈልግም ያለውን እግዚአብሔርን መንቀፍ ጀመረ፡፡ ጭራሽ ጠላቶቼ እኔን ድል ያደረጉት አማልክቶቻቸው ከእኔ አምላክ ቢበልጡ ነው ብሎ ለጠላቶቹ አማልክት መሥዋዕት አቀረበ፡፡ መጨረሻውም እጅግ የከፋ ሆነ፡፡ /2ዜና 28፡20/
‘’አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’’ ብዙ ጊዜ የእምነታችንን ማነስ የምንደብቅባት ሽፋን ናት፡፡ ሀገር ሲታመስ ፣ መከራ ሲጸና ፣ ነገሮች ድብልቅልቅ ሲሉ ፣ ጠላት ከግራና ቀኝ ሲበዛ ምንድን ነው መፍትሔው? አካዝን ለምነኝ ያለ አምላክ ለእኛም ‘‘በመከራህ ቀን ጥራኝ እኔም አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ’’ ብሏል፡፡ /መዝ 49፡15/ በደስታችን ቀን ትዝ ብሎን የማያውቀው ፈጣሪያችን ግድ የለም በመከራህ ቀን ጥራኝ ብሎ ለሁላችን ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምንም ዓይነት ፈተና በግላችን ፣ በሀገራችንና በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ሲመጣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መፍትሔዋ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ከእግዚአብሔር መለመን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ዕንባዋን ትረጫለች ፤ የኃያላን ኃያል ፣ ብርቱዎችን ከዙፋናቸው የሚያዋርድ ፣ ትዕቢተኞችን የሚሰብር አምላክ እንዲደርስላት እንደ ኢሳይያስ የፈጣሪ አንደበት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ጸልዩ ትላለች፡፡
ይህን ጊዜ አካዞች እንበሳጫለን ‘አልለምንም ፣ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም’ እንላለን ቤተክርስቲያንን የላካት ኢሳይያስን የላከው አምላክ መሆኑን አናስተውልም፡፡ የጾም ፣ ጸሎት ፣ ስግደት ፣ ምሕላ ጥቅም አይታየንም፡፡ ሌላ መፍትሔ መፈለግ ነው እንጂ ዝም ብሎ ወደ ሰማይ በማንጋጠጥ ጊዜ ማጥፋት የለብንም እንላለን በሆዳችን፡፡ አፋችን ግን ለታዛቢ ይጠነቀቃል ስለዚህ ‘ዝም ብሎ መጸለይማ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው’ እንላለን፡፡ እነ እገሌ ቢረዱን ብለን የምናስባቸው ቴልጌልቴልፌልሶሮች ብዙ ናቸው፡፡ ማናቸውም ግን መጥተው ያስጨንቁናል እንጂ አይረዱንም፡፡ ሰውን ተስፋ ከማድረግ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ብንለምን ጥሩ ነው፡፡
እኛ ባንለምንም ግን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሚሆን እንዲህ ብሎ ተጽፎአል፦
ጌታ ራሱ ምልክትን ይሠጣችኋል ፤ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ይሉታል /ኢሳ 7፡14/
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
+ ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል +
ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል:: ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!"
ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::
ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5)
ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር::
ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር::
ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ከኃጢአትህ እንጂ ካንተ ጋር ጸብ የለውም::
"በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23)
እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ::
ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ በዐቢይ ጾም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን?
ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል::
እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው::
ጾም ዲያቢሎስ ድል የተደረገበት የጦር ዐውድማ ነው:: በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም:: ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል እንደሚባለው በጾም የተኛ ክርስቲያን መቼም አይነቃም:: በጾም ያልተገራ አንደበት መቼም አይገራም:: በጾም ያልተፈወሰ ቂም መቼም አይፈወስም::
ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ "ይህ ዓይነቱ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም" ብሎ ነበር:: ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም::
ወዳጄ ከቁስልህ የምትፈወስበት ወር እንደደረሰ ዕወቅ:: አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ይህ ዓይነቱ ወገን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው:: ይህ ጾም ሸክም ማራገፊያ ጾም ነው:: እንደ ሕዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንስሓ አስተካክል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል:: ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!"
ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::
ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5)
ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር::
ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር::
ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ከኃጢአትህ እንጂ ካንተ ጋር ጸብ የለውም::
"በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23)
እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ::
ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ በዐቢይ ጾም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን?
ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል::
እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው::
ጾም ዲያቢሎስ ድል የተደረገበት የጦር ዐውድማ ነው:: በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም:: ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል እንደሚባለው በጾም የተኛ ክርስቲያን መቼም አይነቃም:: በጾም ያልተገራ አንደበት መቼም አይገራም:: በጾም ያልተፈወሰ ቂም መቼም አይፈወስም::
ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ "ይህ ዓይነቱ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም" ብሎ ነበር:: ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም::
ወዳጄ ከቁስልህ የምትፈወስበት ወር እንደደረሰ ዕወቅ:: አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ይህ ዓይነቱ ወገን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው:: ይህ ጾም ሸክም ማራገፊያ ጾም ነው:: እንደ ሕዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንስሓ አስተካክል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
+ ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባችው እንስሳ +
የኖኅ መርከብ ጉዳይ በጣም አስገራሚ ከሚሆኑብኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች አንዱ ነው:: በዓለማችን አሁን ያሉ እንስሳት ሁሉ "ከነ ባለቤትዎ" እንዲገኙልን እንደሚባልበት ሰርግ ጥንድ ጥንድ ሆነው የገቡባት ትልቅ መርከብ ታሪክ : ዳግም ለሰው ልጆች ወላጆች ለመሆን የተመረጡ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ብቻ የተሳፈሩባት ትልቅ መርከብ ሁኔታ ትኩር ብሎ ላየው አስገራሚ እውነቶችን ያዘለ ነው::
ከሁሉም በላይ ግን መርከቢቱ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ ብዙ ነገር እንድናስብ ያግዘናል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ወደ ኖኅ መርከብ ተኩላ ገብቶ ሲወጣም ተኩላ ሆኖ ይወጣል:: ወደ ቤተክርስቲያን ግን ተኩላ ሆነው ገብተው በግ ሆነው የወጡ ብዙዎች ናቸው" ብሎአል::
እውነትም ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን መለወጥ የምትችል መርከብ ናት:: ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ጅብ ሆዳም ሆነው ገብተው ጾመኞች ሆነው የወጡ አሉ:: እንደ የሌሊት ወፍ በቀን መኖር አቅቶአቸው ሌሊቱን የልባቸው ዓይን ታውሮ በኃጢአት ጨለማ ሲደናበሩ የኖሩ ሰዎች ወደ መርከቢቱ ገብተው እንደ ንስር አርቀው አጥርተው ቀኑን የሚያዩ ሆነዋል:: ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን የምትለውጥ መርከብ ናት:: ውኃ ወደ እርስዋ ሲገባ ጠበል ይሆናል:: አፈር ወደ እርስዋ ሲገባ እምነት (እመት) ይሆናል:: ዘይት ወደ እርስዋ ሲገባ ቅዱስ ቅባት ይሆናል:: ኅብስትና ወይን ወደ እርስዋ ሲገባ ወደ ቅዱስ ቁርባን ይለወጣል::
ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ያልተለወጠ ሰው ግን ሲገባም ጅብ ሲወጣም ጅብ ሆኖአል:: ኖኅ ከመርከብ መልእክት ልኮት የቀረው የቁራ ነገርስ? ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ስንቶች በዚያው ቀርተዋል? ለዓለም ጨው እንዲሆኑ ተልከው በዚያው ሟሙተው የቀሩ ስንት አሉ:: ርግብ ግን ማረፊያ ስታጣ ተመልሳ ነበር:: ከመርከቢቱ የራቅን ሁላችን "ልባችን በእግዚአብሔር እስካላረፈ ድረስ ዕረፍት የለውም" እንዳለ ሊቁ ወደ መርከቢቱ ፈጥነን መመለስ አለብን::
ሰሞኑን ደግሞ አንድ ጥያቄ በአእምሮዬ ተመላለሰብኝ:: "ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባው እንስሳ ማን ሊሆን ይችላል?" የሚል:: ይህን ጥያቄ በግልም በጉባኤ ላይም ሰዎችን ጠይቄ ነበር:: መቼም ለዚህ ጥቅስ አያስፈልገውም:: ኖኅ ቆሞ እንስሳቱ እስኪገቡ ድረስ እንደጠበቀና ማንንም እንስሳ ጥሎ እንዳልገባ የታወቀ ነው::
በዚህ ምክንያት እንስሳቱ ወደ መርከቢቱ የሚገቡት እንደደረሱበት ቅደም ተከተል ነው:: ክንፍ ያላቸው በርረው ቀድመው ይገባሉ:: እንደ ጥንቸል እንደ ካንጋሮ እንደ ሚዳቁዋ ያሉትም እየዘለሉ ፈጥነው ይገባሉ::
ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነፍሳቸውን ለማዳን ፈጥነው በርረው የገቡ እንደ ሚዳቋ ዘልለው የደረሱ ብርቱዎች አሉ:: እንደ ፒኮክ ያሉ ባለ ውብ ክንፎች : እንደ ቀጭኔ ያሉ ባለ ረዥም አንገቶች እንደ ጃርት ያሉ ሌላው ላይ የሚሰኩት እሾኽ የለበሱ እንስሳት ወደ መርከብዋ ገብተዋል:: በቤተክርስቲያን እንደ ፒኮክ አምሮ መታየት መዘባነን የሚወዱ ለታይታ የሚገዙ ብዙዎች ገብተዋል:: እንደ ቀጭኔ አንገታቸውን ከፍ አድርገው ሰውን ቁልቁል የሚመለከቱና "አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የዕብራውያን ሴቶች" ዓይነት ሕይወት ያላቸውም ገብተዋል:: እንደ ጃርት በክፉ ንግግር የሰው ልብ ላይ የሚሰኩት ጥላቻ የተላበሱ ሰዎችም ገብተዋል:: የኖኅ መርከብ ያልያዘችው እንስሳ እንደሌለ ቤተ ክርስቲያንም ያልተሸከመችው ዓይነት ሰው የለም::
ወደ ጥያቄው ስመለስ በእኔ ግምት ወደ መርከቡ በጣም ዘግይታ የገባችው ኤሊ ነበረች:: በላይዋ ድንጋይ የተጫናት እጅግ ቀርፋፋዋ ኤሊን የማይቀድም እንስሳ መቼም አይኖርም:: ምንም ብትዘገይም ኖኅ እስከመጨረሻው ጠብቆ አስገብቶ ለዘር አትርፎአታል:: የኤሊ ዘሮችም "ኖኅ ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ዳይኖሰር በጠፋን ነበር" ብለው ኖኅን ማመስገናቸው አይቀርም:: እግዚአብሔር ምንም ብትዘገይ ኤሊ ሳትገባ መርከቡን አልዘጋውም::
የኤሊ በመርከቡ መትረፍ በቤተ ክርስቲያን ልንተርፍ ተስፋ ለምናደርግ ለእኛ ትልቅ መጽናኛችን ነው::
ወዳጄ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት እንደ ወፍ ትበርራለህ? እንደ ሚዳቋ ትዘልላለህ? ወይንስ እንደ ኤሊ ትጎተታለህ? እግሮችህ ለመንፈሳዊ ነገር ሲሆን አቅም እያጡ አልተቸገርህም?
ልብህ ቢፈልግም እንደ ኤሊዋ የተጫነህ የኃጢአት ድንጋይ አላንቀሳቅስ ብሎህ አልዘገየህም?
እንዲህ ከሆነ አትጨነቅ መርከብዋ ቤተ ክርስቲያን አንተን ሳትይዝ ጥላህ ወዴትም አትሔድም:: ጉዞህን እስካላቆምህ ድረስ ትጠብቅሃለች:: እየተጎተትህም እየተሳብህም ቢሆን አንተ ብቻ ወደ ደጁ ገስግስ::
አንተ ብቻ መንገድ ጀምር እንጂ ፈጣሪ በሩን የሚዘጋው አንተ እስክትገባ ጠብቆ ነው::
ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እንዲህ ብለህ ለምነው :-
"ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው:: እየተጎተትሁም ቢሆን አሁንም የምጉዋዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው"
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 5 2013 ዓ ም
የኖኅ መርከብ ጉዳይ በጣም አስገራሚ ከሚሆኑብኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች አንዱ ነው:: በዓለማችን አሁን ያሉ እንስሳት ሁሉ "ከነ ባለቤትዎ" እንዲገኙልን እንደሚባልበት ሰርግ ጥንድ ጥንድ ሆነው የገቡባት ትልቅ መርከብ ታሪክ : ዳግም ለሰው ልጆች ወላጆች ለመሆን የተመረጡ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ብቻ የተሳፈሩባት ትልቅ መርከብ ሁኔታ ትኩር ብሎ ላየው አስገራሚ እውነቶችን ያዘለ ነው::
ከሁሉም በላይ ግን መርከቢቱ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ ብዙ ነገር እንድናስብ ያግዘናል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ወደ ኖኅ መርከብ ተኩላ ገብቶ ሲወጣም ተኩላ ሆኖ ይወጣል:: ወደ ቤተክርስቲያን ግን ተኩላ ሆነው ገብተው በግ ሆነው የወጡ ብዙዎች ናቸው" ብሎአል::
እውነትም ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን መለወጥ የምትችል መርከብ ናት:: ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ጅብ ሆዳም ሆነው ገብተው ጾመኞች ሆነው የወጡ አሉ:: እንደ የሌሊት ወፍ በቀን መኖር አቅቶአቸው ሌሊቱን የልባቸው ዓይን ታውሮ በኃጢአት ጨለማ ሲደናበሩ የኖሩ ሰዎች ወደ መርከቢቱ ገብተው እንደ ንስር አርቀው አጥርተው ቀኑን የሚያዩ ሆነዋል:: ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን የምትለውጥ መርከብ ናት:: ውኃ ወደ እርስዋ ሲገባ ጠበል ይሆናል:: አፈር ወደ እርስዋ ሲገባ እምነት (እመት) ይሆናል:: ዘይት ወደ እርስዋ ሲገባ ቅዱስ ቅባት ይሆናል:: ኅብስትና ወይን ወደ እርስዋ ሲገባ ወደ ቅዱስ ቁርባን ይለወጣል::
ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ያልተለወጠ ሰው ግን ሲገባም ጅብ ሲወጣም ጅብ ሆኖአል:: ኖኅ ከመርከብ መልእክት ልኮት የቀረው የቁራ ነገርስ? ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ስንቶች በዚያው ቀርተዋል? ለዓለም ጨው እንዲሆኑ ተልከው በዚያው ሟሙተው የቀሩ ስንት አሉ:: ርግብ ግን ማረፊያ ስታጣ ተመልሳ ነበር:: ከመርከቢቱ የራቅን ሁላችን "ልባችን በእግዚአብሔር እስካላረፈ ድረስ ዕረፍት የለውም" እንዳለ ሊቁ ወደ መርከቢቱ ፈጥነን መመለስ አለብን::
ሰሞኑን ደግሞ አንድ ጥያቄ በአእምሮዬ ተመላለሰብኝ:: "ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባው እንስሳ ማን ሊሆን ይችላል?" የሚል:: ይህን ጥያቄ በግልም በጉባኤ ላይም ሰዎችን ጠይቄ ነበር:: መቼም ለዚህ ጥቅስ አያስፈልገውም:: ኖኅ ቆሞ እንስሳቱ እስኪገቡ ድረስ እንደጠበቀና ማንንም እንስሳ ጥሎ እንዳልገባ የታወቀ ነው::
በዚህ ምክንያት እንስሳቱ ወደ መርከቢቱ የሚገቡት እንደደረሱበት ቅደም ተከተል ነው:: ክንፍ ያላቸው በርረው ቀድመው ይገባሉ:: እንደ ጥንቸል እንደ ካንጋሮ እንደ ሚዳቁዋ ያሉትም እየዘለሉ ፈጥነው ይገባሉ::
ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነፍሳቸውን ለማዳን ፈጥነው በርረው የገቡ እንደ ሚዳቋ ዘልለው የደረሱ ብርቱዎች አሉ:: እንደ ፒኮክ ያሉ ባለ ውብ ክንፎች : እንደ ቀጭኔ ያሉ ባለ ረዥም አንገቶች እንደ ጃርት ያሉ ሌላው ላይ የሚሰኩት እሾኽ የለበሱ እንስሳት ወደ መርከብዋ ገብተዋል:: በቤተክርስቲያን እንደ ፒኮክ አምሮ መታየት መዘባነን የሚወዱ ለታይታ የሚገዙ ብዙዎች ገብተዋል:: እንደ ቀጭኔ አንገታቸውን ከፍ አድርገው ሰውን ቁልቁል የሚመለከቱና "አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የዕብራውያን ሴቶች" ዓይነት ሕይወት ያላቸውም ገብተዋል:: እንደ ጃርት በክፉ ንግግር የሰው ልብ ላይ የሚሰኩት ጥላቻ የተላበሱ ሰዎችም ገብተዋል:: የኖኅ መርከብ ያልያዘችው እንስሳ እንደሌለ ቤተ ክርስቲያንም ያልተሸከመችው ዓይነት ሰው የለም::
ወደ ጥያቄው ስመለስ በእኔ ግምት ወደ መርከቡ በጣም ዘግይታ የገባችው ኤሊ ነበረች:: በላይዋ ድንጋይ የተጫናት እጅግ ቀርፋፋዋ ኤሊን የማይቀድም እንስሳ መቼም አይኖርም:: ምንም ብትዘገይም ኖኅ እስከመጨረሻው ጠብቆ አስገብቶ ለዘር አትርፎአታል:: የኤሊ ዘሮችም "ኖኅ ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ዳይኖሰር በጠፋን ነበር" ብለው ኖኅን ማመስገናቸው አይቀርም:: እግዚአብሔር ምንም ብትዘገይ ኤሊ ሳትገባ መርከቡን አልዘጋውም::
የኤሊ በመርከቡ መትረፍ በቤተ ክርስቲያን ልንተርፍ ተስፋ ለምናደርግ ለእኛ ትልቅ መጽናኛችን ነው::
ወዳጄ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት እንደ ወፍ ትበርራለህ? እንደ ሚዳቋ ትዘልላለህ? ወይንስ እንደ ኤሊ ትጎተታለህ? እግሮችህ ለመንፈሳዊ ነገር ሲሆን አቅም እያጡ አልተቸገርህም?
ልብህ ቢፈልግም እንደ ኤሊዋ የተጫነህ የኃጢአት ድንጋይ አላንቀሳቅስ ብሎህ አልዘገየህም?
እንዲህ ከሆነ አትጨነቅ መርከብዋ ቤተ ክርስቲያን አንተን ሳትይዝ ጥላህ ወዴትም አትሔድም:: ጉዞህን እስካላቆምህ ድረስ ትጠብቅሃለች:: እየተጎተትህም እየተሳብህም ቢሆን አንተ ብቻ ወደ ደጁ ገስግስ::
አንተ ብቻ መንገድ ጀምር እንጂ ፈጣሪ በሩን የሚዘጋው አንተ እስክትገባ ጠብቆ ነው::
ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እንዲህ ብለህ ለምነው :-
"ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው:: እየተጎተትሁም ቢሆን አሁንም የምጉዋዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው"
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 5 2013 ዓ ም
+ ለምን ትቀናለህ? +
በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል። መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር። የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ። ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉት። በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ። አልተሳካም። በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም።
አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት። በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት። እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው
ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ' ብዬ ነገርኩትና
ወጣሁ። አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደሰታ
ጨፈሩ፡፡
ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል። መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን
ሲገልጸው በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ ይለዋል። ሰይጣን በሰው
ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን
እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል
ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት።
መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ነው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው::
ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ። ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር። አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና
ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ።
ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም። እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡
ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል። ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ። ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል። ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ።
ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት
የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ “ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ
ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር
አስወረወረች። ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት
በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው። (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት
ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ። ወዳጄ ቅናት
ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል። የሌላው
ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር
እየጫርክ 'እምቢየው አልገባም' እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ።
ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር። ጲላጦስ እንኳን “በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ። ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ። የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መክፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ
መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ “የቤትህ ቅናት በላኝ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች።
ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ
ካንሰር ራስህን አድን።
ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር። በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም። ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር።
ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው። ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ። መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ
አንተን ሁን።
በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው። ከወደድሃቸው ፍቅር አይቀናም'ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ' ብለህ ለምነው፡፡ በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን' ሮሜ 13፡13
✍️ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል። መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር። የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ። ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉት። በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ። አልተሳካም። በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም።
አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት። በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት። እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው
ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ' ብዬ ነገርኩትና
ወጣሁ። አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደሰታ
ጨፈሩ፡፡
ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል። መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን
ሲገልጸው በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ ይለዋል። ሰይጣን በሰው
ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን
እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል
ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት።
መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ነው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው::
ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ። ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር። አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና
ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ።
ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም። እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡
ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል። ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ። ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል። ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ።
ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት
የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ “ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ
ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር
አስወረወረች። ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት
በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው። (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት
ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ። ወዳጄ ቅናት
ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል። የሌላው
ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር
እየጫርክ 'እምቢየው አልገባም' እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ።
ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር። ጲላጦስ እንኳን “በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ። ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ። የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መክፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ
መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ “የቤትህ ቅናት በላኝ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች።
ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ
ካንሰር ራስህን አድን።
ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር። በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም። ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር።
ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው። ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ። መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ
አንተን ሁን።
በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው። ከወደድሃቸው ፍቅር አይቀናም'ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ' ብለህ ለምነው፡፡ በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን' ሮሜ 13፡13
✍️ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ