Telegram Web
ወደ ቻናሉ የምትገቡ አዳዲስ አንባቢያን በቅድሚያ እንኳን ደህና መጣችሁ! ለሃይማኖታዊ ንጽጽር ከላይ ጀምሩ፦ https://www.tgoop.com/Wahidcom/18
ሕይወትን መስጠት

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥49 "በአሏህም ፈቃድ ዕውር ኾኖ የተወለደን፤ ለምጸኛንም አድናለሁ፡፡ ሙታንንም አስነሳለሁ"፡፡ وَأُبْرِئُ الْأَكْمَهَ وَالْأَبْرَصَ وَأُحْيِي الْمَوْتَىٰ بِإِذْنِ اللَّهِ ۖ

የናዝሬቱ ኢየሱስ በአምላክ እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ ነበር፥ ኢየሱስ አምላክ ሲያደርግ እያየ የሚያደርግ እንጂ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም፦
ሉቃስ 24፥19 እርሱም፦ ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት፦ “በአምላክ እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ”።
ዮሐንስ 5፥19 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህም አላቸው፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ ወልድ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም፥ ያ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድ ደግሞ ይህን እንዲሁ ያደርጋልና።

"ያ" የሚለውን የሩቅ አመልካችን ተውላጠ ስም አብ ለኢየሱስ ለማሳየት የሚያደርገውን ሥራ ያመላክታል፥ “ይህን” የሚለው የቅርብ አመልካችን ተውላጠ ስም “ያ” የሚለውን ተክቶ የመጣ ሲሆን አብ ለወልድ እንዲያደርግ የሚያሳየውን ሥራ ያመላክታል፦
ዮሐንስ 14፥31 አብም እንዳዘዘኝ እንዲሁ አደርጋለሁ።

አንድ አምላክነት ያለው ማንነት ምን መሥራት እንዳለበት ሌላ ማንነት እንዴት ያሳየዋል? አብ ወልድ ምን ማድረግ እንዳለበት ያሳየዋል፦
ዮሐንስ 5፥20 አብ ወልድን ይወዳልና፥ የሚያደርገውንም ሁሉ ያሳየዋል፤ እናንተም ትደነቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ሥራ ያሳየዋል።

ኢየሱስ የሚያደርገውን ሁሉ አብ እያሳየው ብቻ ነው፥ “ከዚህ የሚበልጥ ሥራ ያሳየዋል” ሲል የሚሠራውን ሥራ ፈጣሪ እያሳየው ያደርጋል ማለት ነው። ከፈጣሪ እያየ የሚሠራ ማንነት እራሱ ፈጣሪ ከሆነ አንዱ የሚያሳይ ሁለተኛው እያየ የሚኮርጅ ሁለት ፈጣሪ ይሆን ነበር። ወልድ ምን ምን ማድረግ እንዳለበት አብ ያሳየዋል ማለት ወልድ ሙታንን እንዲያስነሳ፣ ለምጻም እንዲያነጻ፣ ሽባ እንዲተረትር መመሪያ፣ ሥልጣን እና ኃይል ይሰጠዋል ማለት ነው፥ ለምሳሌ ፈሪሳውያን በሰይጧን ዘንድ ያዩት ያደርጋሉ ማለት ሰይጧን መመሪያ እየሰጣቸው ያደርጋሉ ማለት እንደሆነ ሁሉ ኢየሱስም በአብ ዘንድ ያየውን ያደርጋል ማለት አብ መመሪያ እየሰጠው ያደርጋል ማለት ነው፦
ዮሐንስ 8፥38 እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።

ኢየሱስ ተአምር እንዲሠራ የጌታ ኃይል ሆኖሎት እንጂ ከራሱ አንዳች ሊያደርግ አይቻለውም። ኢየሱስ ከራሱ ምንም ማድረግ ካልቻለ ሁሉን ቻይ አምላክ አይደለም፦
ሉቃስ 5፥17 እርሱም እንዲፈውስ የጌታ ኃይል ሆነለት።
ዮሐንስ 5፥30 እኔ “ከ”-“ራሴ” አንዳች ላደርግ አይቻለኝም።

“እኔ” የሚለው ባለቤት ተውላጠ ስም እና "እራሴ" የሚለው ድርብ ተውላጠ ስም የኢየሱስን ሙሉ "እኔነትን" እንጂ ሥጋን አያሳይም፥ ሥጋ ብቻውን ማንነት ስላልሆነ “እኔ” እና "እራሴ" ሰለማይል ኢየሱስ ከማንነቱ ምንም ማድረግ አይችልም። ኢየሱስ በአምላክ የተደገፈ ጥገኛ ባሪያ ነው፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ "ደግፌ የያዝሁት" ባሪያዬ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት "ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል።

መንፈሱን ያሳረፈበት ተአምር እንዲሠራ ነው። ጭራሽ ኢየሱስ የሚያደርገው ሥራ በፈጣሪ ስም ሲሆን እርሱ ነቢይ ስለመሆኑ የሚመሰክር ነው፦
ዮሐንስ 10፥25 እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ስለ እኔ ይመሰክራል።
ዮሐንስ 5፥36 አብ ልፈጽመው የሰጠኝ ሥራ ይህ የማደርገው ሥራ አብ እንደ ላከኝ ስለ እኔ ይመሰክራልና።

ኢየሱስ የሚያደርገው ሥራ ሁሉ እርሱ መልእክተኛ ስለመሆኑ ምስክር እንዲሆን በስጦታ ያገኘው ስለሆነ “አብ ልፈጽመው የሰጠኝ ሥራ” በማለት እንቅጩን ፍርጥ አድርጎ ይናገራል፦
ዮሐንስ 17፥4 እኔ ላደርገው "የሰጠኸኝን ሥራ" ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤

“የሰጠኸኝን ሥራ” የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! ሁሉን ማድረግ የሚችል ማንነት ከሌላ ማንነት የሚሠራበትን ዐቅም በስጦታ በፍጹም አይቀበልም፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን አብ እንዳዘዘው ኢየሱስ ያደርጋል። ኢየሱስ ሲያደርግ የነበረውን ሥራ ሙት ማስነሳት፣ ሽባ መተርተር፣ ዕውር ማብራት ወዘተ በእርሱ የሚያምን ሰው ሊያደርገው ይችላል፥ እረ ኢየሱስ ካደረገው በላይ የሚበልጥ ያደርጋል፦
ዮሐንስ 14፥13 እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፥ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል።

እውነት ኢየሱስ ሁሉን ቻይ አምላክ ቢሆን ኖሮ ሁሉን የሚችል አምላክ ሊያደርግ የሚችለውን ሰው ሊያደርግ ይችላልን? ከሁሉን የሚችል አምላክ በላይ የሚበልጥ ሥራ ሊሠራ ይችላልን? ነገሩ ኢየሱስ፦ "የሚሳናችሁም ነገር የለም" ብሏል፦
ማቴዎስ 17፥20 የሚሳናችሁም ነገር የለም።
ስለዚህ ኢየሱስ የሚያደርገው ሥራ የአምላክነት ሥራ ሳይሆን በጸጋ እና በስጦታ እንዲሥራ የታዘዘው ሥራ ነው፥ ምክንያቱም ኢየሱስ ከሚያደርገው የሚበልጥ ተከታዮቹ ለማድረግ የሚሳናቸው ምንም ነገር እንደሌለ ተናግሯልና። ኢየሱስ ሙታንን ብዙ ጊዜ ማስነሳቱ በራሱ ለትንሣኤ ዘጉባኤ ናሙና ነው፥ እርሱ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያትም ሙታንን አስነስተዋል፦
ማቴዎስ 10፥8 ድውዮችን ፈውሱ፣ "ሙታንን አስነሡ"፣ ለምጻሞችን አንጹ፣ አጋንንትን አውጡ፣ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።

"ሙታንን አስነሡ" የሚለው ይሰመርበት! በኢየሱስ ነቢይነት የሚያምኑት ሐዋርያት ኢየሱስ የሚያደርገውን አድርገዋል፦
ዮሐንስ 14፥13 እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፥ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል።

ኢየሱስ ሲያደርግ የነበረው ሥራ ለምጻም ማንጻት፣ ድውይ መፈወስ፣ ሙት ማስነሳት ወዘተ ነው፥ “ማኅየዊ” ማለትም “አስነሺ” “ሕይወት ሰጪ” ማለት ነው፦
ዮሐንስ 5፥21 አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል።

ወልድ "ሕይወት ይሰጣል" ማለት በዚህ ዐውድ "ሙታን ያስነሳል" ማለት ነው። ኢየሱስ፦ "ከደቀ መዛሙርቴ አንዱን እልክላችኃለው፥ ይፈውሳችኃል ሕይወት ይሰጣችኃል" ብሏል፦
"ኢየሱስም፦ "ከደቀ መዛሙርቴ አንዱን እልክላችኃለው፥ ይፈውሳችኃል ሕይወት ይሰጣችኃል" አለ"።
Church History (Eusebius) Book I(1) Chapter 13 Number 14

ኢየሱስ "ከደቀ መዛሙርቴ አንዱን እልክላችኃለው፥ ይፈውሳችኃል ሕይወት ይሰጣችኃል" የሚለው ቃል አራቱ ወንጌላት ላይ ያልሰፈረ ተብሎ የተዘገበ እውነት ነው፥ ሙግቱን እናጥብበውና ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ "ሕይወትን ይሰጣል" ሲባል "ሙት ያስነሳል" ከሆነ ልክ እንደ ኢየሱስ የሐዋርያው አለቃ የሆነው ጴጥሮስ ሙት አስነስቷል፦
ሐዋርያት 9፥40 ጴጥሮስም ሁሉን ወደ ውጭ አስወጥቶ ተንበርክኮም ጸለየ፥ ወደ ሬሳውም ዘወር ብሎ፦ ጣቢታ ሆይ፥ ተነሺ አላት። እርስዋም ዓይኖችዋን ከፈተች ጴጥሮስንም ባየች ጊዜ ተቀመጠች።

ኢየሱስ "ሕይወት ይሰጣል" ብላችሁ ጮቤ ስትረግጡ የነበራችሁ ሰዎች የጴጥሮስን ሕይወት መስጠት ስትሰሙ ምን ይውጣችሁ ይሆን? በእርግጥ ኢየሱስ በአሏህ ፈቃድ ሙታንን አስነስቷል፦
3፥49 "በአሏህም ፈቃድ ዕውር ኾኖ የተወለደን፤ ለምጸኛንም አድናለሁ፡፡ ሙታንንም አስነሳለሁ"፡፡ وَأُبْرِئُ الْأَكْمَهَ وَالْأَبْرَصَ وَأُحْيِي الْمَوْتَىٰ بِإِذْنِ اللَّهِ ۖ

ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ ያመለከው አምላክ አምልካችሁ ለመዳን ወደ ዲኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
Photo
ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር

ማኅበራችን ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር በርካታ ሥራዎችን እየከወነ የሚገኝ ማኅበር ነው። ለአብነት፦

● የኢሥላምን ጥንፍፍ መልእክት ለሙሥሊሙ እና ሙሥሊም ላልሆነው ማኅበረሰብ በተለያዩ መዳረሻ መንገዶች ተደራሽ ማድረግ፣

● የዳዕዋ ክህሎት ስልጠና መስጠት፣

● ሙሥሊም ያልሆኑ ወገኖች ስለ ኢሥላም ያላቸውን ጥያቄዎች የሚያቀርቡበትን መድረክ ማመቻቸት እና አጥጋቢ ምላሾችን መስጠት፣

● የሃይማኖት ንጽጽር ኮርሶችን መስጠት፣

● አዳዲስ ሠለምቴዎችን ተቀብሎ መሠረታዊ የኢሥላም ትምህርቶችን መስጠት፣

● ከቤታቸው ለሚባረሩ ሠለምቴ ወንድሞች እና እኅቶች ማረፊያ ቦታ አዘጋጅቶ መቀበል፣

● ከቤት የሚባረሩ ሠለምቴዎችን ከተቀበለ በኋላ ለእነርሱ መሠረታዊ ፍላጎቶችን (ቤት፣ ቀለብ እና ትራንስፖርት) ማሟላት እና ክትትል ማድረግ፣

● ለሠለምቴዎች ማረፊያ፣ ዲናቸውን መማርያ እና ማስተዳደሪያ የሚሆን ሕንጻ መገንባት፣

● የኢሥላምን መልእክት የሚያንጸባርቁ መጻሕፍትን መጻፍ እና ማሳተም፣

እዚህ ማኅበር አባል ለመሆን እና በአሳብ፣ በጉልበት፣ በገንዘብ ለማገዝ እንመዘግባለን። የአባልነት መስፈርቶች፦
1ኛ. ሙሥሊም መሆን፣
2ኛ. ኢኽላስ፣
3ኛ. ቆራጥነት፣
4ኛ. ታማኝነት፣
5ኛ. የዲን ወኔ እና የኩፍር ኃይላት ጥቃት ቁጭት ያለው ሙሥሊም መሆን ብቻ እና ብቻ ነው።

ሠለምቴዎችን በወራዊ መዋጮ በቋሚነት መደገፍ የምትፈልጉ እና የበለጠ መረጃ ለማግኘት ሙሥሊም ወንድሞች እና እኅቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አድሚናት በቴሌ ግራም ያግኙ፦
1. ወንድም አቡ ኑዓይም፦ https://www.tgoop.com/arhmanu
2. እኅት ዘሃራ፦ https://www.tgoop.com/Zhara_mustefa
3. ወንድም ሑሤይን፦ https://www.tgoop.com/Hussu707
4. እኅት ሐዊ፦ https://www.tgoop.com/hawin922
5. ወንድም ዐብዱ፦ https://www.tgoop.com/Abi_Abik
6. እኅት ጀሙቲ፦ https://www.tgoop.com/Jemuti12
7. ወንድም ኢብኑ ረሻድ፦ https://www.tgoop.com/IbunReshed
8.እኅት እናት፦ https://www.tgoop.com/enattenat
9. ወንድም እስሚዞ፦ https://www.tgoop.com/Esmitiz_hubi
10. እኅት መርየም፦ https://www.tgoop.com/J_y_A_M
11. ኡሥታዝ አቡ ሩመይሳ፦ https://www.tgoop.com/aburumaisa037
12. እኅት ሹሹ፦ https://www.tgoop.com/umusara45
13. ወንድም ፈይሰል፦ https://www.tgoop.com/feyselsan
14. እኅት ፈቲ፦ https://www.tgoop.com/Feti_12
15. ወንድም ሙከሚል፦ https://www.tgoop.com/Mukamil_Hussan
16. እኅት አሲያ፦ https://www.tgoop.com/Ccccftb3
የኢየሱስ ጌታ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَا أَمَرْتَنِي بِهِ أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ

በኢሥላም አስተምህሮት የኢየሱስ ጌታ አሏህ ነው፥ ኢየሱስ ከአሏህ የተሰጠው ተልእኮ "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" የሚል ነበር፦
5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَا أَمَرْتَنِي بِهِ أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ

በባይብል ደግሞ "ኩሪዮስ" κύριος ማለት "ጌታ" ማለት ሲሆን ለአንዱ ፈጣሪ የሚውል ቢሆንም ለፍጡራን ክብር እና ማዕረግ፣ እልቅና እና ልዕልና፣ ሥልጣን እና ሹመት ለማመልከት ይገባል፥ ለምሳሌ፦ ሣራ ለአብርሃም፦ "ጌታ" ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፦
1 ጴጥሮስ 3፥6 እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ "ጌታ" ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት። ὡς Σάρρα ὑπήκουσεν τῷ Ἀβραάμ, κύριον αὐτὸν καλοῦσα·

እዚህ አንቀጽ ላይ "ጌታ" ለሚለው የገባው ቃል በግሪክ ኮይኔ "ኩሪዮስ" κύριος ሲሆን ሳራ አብርሃምን "ጌታዬ" ስትለው የገባው ቃል "አዶኒ" אדֹנִ֗י ነው፦
ዘፍጥረት18፥12 ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች። ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? "ጌታዬም" ፈጽሞ ሸምግሎአል። וַתִּצְחַ֥ק שָׂרָ֖ה בְּקִרְבָּ֣הּ לֵאמֹ֑ר אַחֲרֵ֤י בְלֹתִי֙ הָֽיְתָה־לִּ֣י עֶדְנָ֔ה וַֽאדֹנִ֖י זָקֵֽן׃

እዚህ አንቀጽ ላይ ሳራ አብርሃም በዕብራይስጥ "አዶኒ" אדֹנִ֗י ስትለው "አዶኒ" אדֹנִ֗י የሚለው ለፍጡራን የሚውል ማዕረግ ነው። የኢየሱስ ጌትነት በመደረግ ላይ የተመሠረተ መነሾ እና ጅማሮ ያለው ስለሆነ የባሕርይ ጌትነት በፍጹም አይደለም፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። ἀσφαλῶς οὖν γινωσκέτω πᾶς οἶκος Ἰσραὴλ ὅτι καὶ Κύριον αὐτὸν καὶ Χριστὸν ἐποίησεν ὁ Θεός, τοῦτον τὸν Ἰησοῦν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" ባለቤት ሲሆን "ኢየሱስ" ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "እንዳደረገው" የሚል ተሻጋሪ ግሥ አለ። ጌታ አድራጊው አንዱ አምላክ ሲሆን ጌታ ተደራጊው ኢየሱስ ነው፥ አምላክ ኢየሱስን ጌታ ካረደገው የኢየሱስ ጌትነት መነሾ እና ጅማሮ ያለው ስለሆነ እና ጌታ ከመደረጉ በፊት በባዶነት ስለሚቀደም ጌትነቱ ክብር እና ማዕረግ፣ እልቅና እና ልዕልና፣ ሥልጣን እና ሹመት ያሳያል። ምክንያቱም "እንዳደረገው" ለሚለው የገባው ቃል "ኤፓዬሴን" ἐποίησεν ሲሆን ከዚህ በፊት ያልሆነ ወደ መሆን በመደረግ ለመጣ ነገር በግሪክ ኮይኔ ይጠቀምበታል፦
ዘፍጥረት 45፥9 "አምላክ" በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ "ጌታ" አደረገኝ። ἐποίησέ με ὁ Θεὸς κύριον πάσης γῆς Αἰγύπτου·

የግሪክ ሰፕቱአጀንት ዮሴፍ "አደረገኝ" ላለበት የተጠቀመበት ቃል "ኤፓዬሴ" ἐποίησέ እንደሆነ ልብ አድርግ! አምላክ ዮሴፍን ጌታ ማድረጉ ክብር እና ማዕረግ፣ እልቅና እና ልዕልና፣ ሥልጣን እና ሹመት ያሳያል ከተባለ እንግዲያውስ አምላክ ኢየሱስን ጌታ ማድረጉ ክብር እና ማዕረግ፣ እልቅና እና ልዕልና፣ ሥልጣን እና ሹመት ያሳያል። "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ማለት "ጌታዬ" ማለት ነው፥ መሢሑ በትንቢት መነጽር ያህዌህን "ጌታዬ" ብሎታል፦
ኢሳይያስ 61፥1 "የ-"ጌታዬ" የያህዌህ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ ያህዌህ ቀብቶኛልና። ר֛וּחַ אֲדֹנָ֥י יְהוִ֖ה עָלָ֑י יַ֡עַן מָשַׁח֩ יְהוָ֨ה אֹתִ֜י לְבַשֵּׂ֣ר עֲנָוִ֗ים

እዚህ አንቀጽ ላይ "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ማለት "ጌታዬ" ማለት ከሆነ ኢየሱስ አምላኩን "ጌታዬ" ማለቱ በራሱ የሚገዛለት ጌታ እንዳለው አመላካች ነው፥ ኢየሱስ አንድም ጊዜ "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י አልተባለም። ኢየሱስ በትንቢት መነጽር የፈጠረው ጌታ እንዳለው ተናግሯል፦
ምሳሌ 8፥22 "ጌታ" በቀድሞ ተግባሩ "ፈጠረኝ"። κύριος ἔκτισέν με ἀρχὴν ὁδῶν αὐτοῦ εἰς ἔργα αὐτοῦ

በግሪክ ሰፕቱአጀንት እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈጠረኝ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤክቲሴን ሜ" ἔκτισέν με ሲሆን፣ በዕብራይስጥ ማሶሬት "ካናኒ" קָ֭נָנִי ሲሆን፣ በግዕዝ ደግሞ "ፈጠረኒ" ነው፥ ቀደምት የቤተክርስቲያን አበው ምሳሌ 8፥22 ላይ "ፈጠረኝ" የሚለው ኢየሱስ እንደሆነ ያለምንም ልዩነት በወጥ ፍሰት አብራርተዋል። ኢየሱስን የፈጠረ ጌታ ጌትነቱ የባሕርይ ሲሆን የዓለማቱ ጌታ ነው፥ በጌትነቱ ላይ ባርነት የሌለበት ይህ ጌታ ኢየሱስን "ባሪያዬ" ይለዋል፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል። הֵ֤ן עַבְדִּי֙ אֶתְמָךְ־בֹּ֔ו בְּחִירִ֖י רָצְתָ֣ה נַפְשִׁ֑י נָתַ֤תִּי רוּחִי֙ עָלָ֔יו מִשְׁפָּ֖ט לַגֹּויִ֥ם יֹוצִֽיא׃
በጌትነቱ ላይ ባርነት ያለበት ኢየሱስ የባሕርይ ጌታ አለመሆኑን ይህ ጥቅስ በቂ አስረጅ ነበር። ማርያም እና ዮሴፍ ኢየሱስ በጌታው ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፦
ሉቃስ 2፥24 "በጌታ ፊት ሊያቆሙት"፥ በጌታም ሕግ፦ “ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች፡” እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት።

"በጌታ ፊት ሊያቆሙት" የሚለው ይሰመርበት! የተወሰደው ኢየሱስ እና ጌታው በማንነት ሆነ በምንነት ሁለት ለየቅል የሆኑ ሃልዎት ናቸው፥ "የባሕርይ ጌታ" ማለት ጌትነቱ በራሱ የተብቃቃ እና ጌትነቱ የራሱ ገንዘቡ የሆነ ማለት ነው። ይህ የኢየሱስ ጌታ እና አምላክ አንዱ ጌታ አምላክ ነው፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ ስማ! አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד.
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ “ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ "እስራኤል ሆይ ስማ!  ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው"። ἀπεκρίθη ὁ Ἰησοῦς ὅτι Πρώτη ἐστίν Ἄκουε, Ἰσραήλ, Κύριος ὁ Θεὸς ἡμῶν Κύριος εἷς ἐστιν,

እዚህ አንቀጽ ሆነ ዘዳግም 6፥4 ግሪክ ሰፕቱአጀት ላይ "አንድ" ለሚል የገባው ቃል "ሄይስ" εἷς ሲሆን ለአንድ ማንነት የሚል አንስታይ መደብ ነው። ከ 130 እስከ 202 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ኢራንዮስ ዘልዮን"Irenaeus of Lyon" የፖሊካርፐስ ዘሰርምኔስ ተማሪ ሲሆን "እስራኤል ሆይ ስማ! ጌታ አምላካችን አንድ አምላክ ነው" የተባለው የኢየሱስ አባት እንደሆነ በግልጽ አስቀምጧል፦
"ኦሪት ያወጀው፣ ነቢያት ያስተማሩት፣ እንዲሁ ክርስቶስ አባቱ እንደሆነ የመሰከረለት፦ "እስራኤል ሆይ ስማ! ጌታ አምላካችን አንድ አምላክ ነው" የሚል አይደለምን?" ዘዳግም 6፥4 ።
Against Heresies (St. Irenaeus) Book V(5) Chapter 11 Number 1

የአይሁድ ሕግ ዐዋቂ ኢየሱስን "አንድ ነው ከእርሱም በቀር ሌላ የለም" ብለህ መልካም ተናገር በማለት የኢየሱስ ተልእኮ ከጥንት ነቢያት የተለየ እንዳልሆነ አረጋግጦአል፦
ማርቆስ 12፥32 ጻፊውም፦ “መልካም ነው፥ መምህር ሆይ! "አንድ ነው ከእርሱም በቀር ሌላ የለም" ብለህ በእውነት ተናገርህ።

አሁንም እዚህ አንቀጽ "አንድ" ለሚል የገባው ቃል "ሄይስ" εἷς ሲሆን ይህ አንዱ ጌታ አምላክ ለኢየሱስ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን የሚሰጥ ነው፦
ሉቃስ 1፥32 ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል።

ሰጪ አንዱ ጌታ አምላክ ባለቤት ሲሆን ተሰጪ ማርያም የፀነሰችው ወንድ ልጅ ተሳቢ ነው፥ "ይሰጠዋል" የሚል ተሻጋሪ ግሥ"Transitive Verb" በባለቤት እና በተሳቢ መካከል መኖሩ ጌታ አምላክን ከወንድ ልጅ በምንነት ሆነ በማንነት ይለየዋል፦
ራእይ 21፥22 ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እና በጉ መቅደስዋ ናቸው።

ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ አብ እና በጉ መሢሑ "እና" በሚል መስተጻምር መለየታቸው እና "ናቸው" በሚል የብዜት አያያዥ ግሥ መቀመጣቸው የኢየሱስ ጌታ እና አምላክ ከኢየሱስ በሰዋስው ተለይቶ ተቀምጧል፦
ማቴዎስ 4፥10 ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ።

ኢየሱስ ጠቅሶ እና አጣቅሶ "እርሱንም ብቻ አምልክ" ብሎ ካስተማረ "እርሱ" ተብሎ በነጠላ ተውላጠ ስም የተቀመጠውን ጌታ አምላክ ማምለክ ከጀሀነም ዘውታሪነት ነጻ ያወጣል። እንግዲህ ኢየሱስ ጌታ ካለው፣ ለጌታው ባሪያ ከሆነ፣ ጌትነቱ በመደረግ ላይ የተመሠረተ መነሻ እና ጅማሮ ካለው እንግዲያውስ በጌትነቱ ባርነት የሌለበትን የባሕርይ ጌታ የሆነውን አሏህን በብቸኝነት አምልኩ! እንደ ኢየሱስ ለጌታችን ባሪያ መሆን ምንኛ መታደል ነው? ስለዚህ የኢየሱስን ጌታ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ጌታችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ኩፋሮች የሚያነሱትን ጥያቄዎች ከበቂ መልስ እና ከበቂ ማብራሪያ ጋር እንዲሁ የእኛን በጨዋ ደንብ ያቀረብነውን ሙግት ይጎብኙት፦
ክፍል አንድ
ክፍል ሁለት
ክፍል ሦስት
ክፍል አራት
ክፍል አምስት
ክፍል ስድስት
ክፍል ሰባት

ለሌሎች ሠበቡል ሂዳያህ ይሆን ዘንድ ኢንሻላህ ሼር አርጉት!
ማኢዳህ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ

የቁርባን ነገረ መለኮት"Eucharistic Theology" በክርስትና ዐበይት ከሚባሉ አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት መካከል አንዱ ነው፥ አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት"Five Fundamental Sacraments" የሚባሉት፦ ምሥጢረ ሥላሴ፣ ምሥጢረ ሥጋዌ፣ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ቁርባን እና ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው። በምሥጢረ ቁርባን እሳቤ ውስጥ ዐበይት ክርስቲያኖች "ክርስቶስ ከሰማይ የወረደ እንጀራ ነው" ብለው ያምናሉ፦
ዮሐንስ 6፥51 ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።

"ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ ሥጋዬ ነው" ስለሚል ክርስቶስ እራሱ የሚበላ ማዕድ እንደሆነ ይናገራሉ፥ ይህም ማዕድ ሥጋ መብላት እና ደም መጠጣት እንደሆነ ተነግሯል፦
ዮሐንስ 6፥53 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።

"ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነው" ብሏል ተብሏል፦
ዮሐንስ 6፥54 ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።

"የክርስቶስ ሥጋ እና ደም ምሳሌአዊ ሳይሆን እውነተኛ መብል እና መጠጥ ነው፥ የጌታ እራት የሚባለው እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም ይለወጣል" የሚል እምነት በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ትምህርት ውስጥ አለ፦
ማቴዎስ 26፥26 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ።

ነገር ግን ጠርጡሊያኖስ ዘካርቴጅ እንጀራው የሥጋው ምሳሌ እንደሆነ ተርጉሞታል፦
"እንጀራውን አንሥቶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ "ሥጋዬም ይህ ነው፥ እርሱም የሥጋዬ ምሳሌ ነው" ብሎ የራሱን ሥጋ አደረገው"።
Against Marcion (Tertullian) Book IV(4) Chapter 40

በጽዋ ውስጥ ያለውን ወይን ደግሞ "ደሜ ይህ ነው" እንዳለ ተዘግቧል፦
ማቴዎስ 26፥27-28 ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።

አውግስጢኖስ ዘሂፓ ወይኑ የደሙ ምሳሌ እንደሆነ ተርጉሞታል፦
"የሥጋው እና የደሙን ምሳሌ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ"።
Expositions on the Psalms (Augustine) Psalm Chapter 3 Number 1

ካቶሊክ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በኑባሬ ደረጃ ይለወጣል" የሚል ትምህርታቸው "የኑባሬ ለውጥ"Tran Substantiation" ሲባል በኦርቶዶክስ ደግሞ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በተማልሎአዊ ይለወጣል" ሲባል ተማልሎአዊ ለውጥ"Mystical Change" ነው፥ በሁለቱም እምነት "የበቃ ሰው በከለር፣ በጣዕም፣ በይዘት ተቀይሮ ያየዋል" የሚል እምነት አላቸው። ሰዎች ጠፍጥፈው የሠሩት እንጀራ እና የጠመቁት ወይንን "የአምላክ ሥራ የሆነው ኢየሱስ ነው" ማለት የጤና ነው? መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው ሥጋ ከሰው ሰውነት ጋር ሲዋሐድ የሰው ሰውነት አምላክ ይሆናልን? ቁርባን በልተው ሲጸዳዱት ያ መለኮት ይጸዳዱታልን?

በፕሮቴስታንት ደግሞ ሁሉም ባይሆንም "ኅብስቱ ከሥጋው ጋር እንዲሁ ወይኑ ከደሙ ጋር ኅብረት ብቻ አለው እንጂ አይለወጥም" የሚል ትምህርታቸው አላቸው፥ ይህም "የኑባሬ ኅብረት"Con Substantiation" ይባላል።

"ፋሲካ" በሚባል "በዓል" ላይ በመሸም ጊዜ ኢየሱስ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ እንደተቀመጠ ይናገራል፦
ማቴዎስ 26፥20 በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ። Ὀψίας δὲ γενομένης ἀνέκειτο μετὰ τῶν δώδεκα μαθητῶν

"ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ማዕድ" ወይም "ገበታ" ማለት እንጂ ባለ አራት እግር ያለው "ጻሕል(ሳሕን) ወይም "ወጭት" አይደለም፥ "ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ትራፔዛ" τράπεζα ከሚል ግሪክ ኮይኔ የመጣ ሲሆን "ማዕድ" ማለት ነው። ለምሳሌ፦
የሐዋርያት ሥራ 16፥34 ወደ ቤቱም አውጥቶ ማዕድ አቀረበላቸው። ἀναγαγών τε αὐτοὺς εἰς τὸν οἶκον παρέθηκεν τράπεζαν, 

እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛን" τράπεζα እንደሆነ ልብ አድርግ!
እዚህ ድረስ ከተግባባን ወደ ቁርኣን ስንመጣ "ማኢዳህ" مَائِدَة ማለት "ማዕድ" ማለት ሲሆን ሐዋርያት ኢየሱስን፦ «የመርየም ልጅ ዒሣ ሆይ! ጌታህ በእኛ ላይ ከሰማይ ማዕድን ሊያወርድልን ይችላልን?» ብለው ጠየቁት፦
5፥112 ሐዋርያት፡- «የመርየም ልጅ ዒሣ ሆይ! ጌታህ በእኛ ላይ ከሰማይ ማዕድን ሊያወርድልን ይችላልን?» ባሉ ጊዜ አስታውስ፡፡ «ምእመናን እንደ ኾናችሁ አሏህን ፍሩ» አላቸው፡፡ إِذْ قَالَ الْحَوَارِيُّونَ يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ هَلْ يَسْتَطِيعُ رَبُّكَ أَن يُنَزِّلَ عَلَيْنَا مَائِدَةً مِّنَ السَّمَاءِ ۖ قَالَ اتَّقُوا اللَّهَ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ
5፥113 «ከእርሷ ልንበላ ልቦቻችንም ሊረኩ እውነት ያልከንም መኾንህን ልናውቅና በእርሷም ላይ ከመስካሪዎች ልንኾን እንፈልጋለን» አሉ፡፡ قَالُوا نُرِيدُ أَن نَّأْكُلَ مِنْهَا وَتَطْمَئِنَّ قُلُوبُنَا وَنَعْلَمَ أَن قَدْ صَدَقْتَنَا وَنَكُونَ عَلَيْهَا مِنَ الشَّاهِدِينَ

ኢየሱስም ወደ አሏህ «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ፦
5፥114 የመርየም ልጅ ዒሣ አለ፡- «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ። قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا أَنزِلْ عَلَيْنَا مَائِدَةً مِّنَ السَّمَاءِ تَكُونُ لَنَا عِيدًا لِّأَوَّلِنَا وَآخِرِنَا وَآيَةً مِّنكَ ۖ وَارْزُقْنَا وَأَنتَ خَيْرُ الرَّازِقِينَ

"ዒድ" عِيد ማለት "በዓል" ማለት ሲሆን ይህም በዓል ፋሲካ ነው፥ በዚህ በዓል ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን በተአምር ከሰማይ የመጣ ማዕድ ነው፦
5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ

ስለዚህ ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን ለኢየሱስ እና ለሐዋርያት ለበዓሉ እንዲበሉት የተሰጠ ማዕድ ነው፥ ቁርኣን ባይብል ላይ የገባውን የተሳሳተ "የጌታ ማዕድ" በዚህ መልኩ አስተካክሎታል። ከሰማይ ማዕድ ማውረድ ለአሏህ ቀላል ነው፥ ምነው እስራኤላውያን በምድረ በዳ እያሉ አሏህ መናን እና ድርጭትን ከሰማይ አውርዷል እኮ፦
20፥80 በእናንተም ላይ መና እና ድርጭትን አወረድንላችሁ፡፡ وَنَزَّلْنَا عَلَيْكُمُ الْمَنَّ وَالسَّلْوَىٰ
2፥57 በእናንተም ላይ ደመናን አጠለልን፥ በእናንተ ላይ መናን እና ድርጭትን አወረድን፡፡ وَظَلَّلْنَا عَلَيْكُمُ الْغَمَامَ وَأَنزَلْنَا عَلَيْكُمُ الْمَنَّ وَالسَّلْوَىٰ

በባይብልም ቢሆን እስራኤላውያን በምድረ በዳ እያሉ የሰማይ ኅብስት የሆነ መና እና ድርጭት እንደወረደላቸው ይናገራል፦
መዝሙር 78፥24 ይበሉም ዘንድ "መናን" አዘነበላቸው፥ የሰማይንም እንጀራ ሰጣቸው።
መዝሙር 105፥40 ለመኑ፥ "ድርጭትን" አመጣላቸው፥ የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው።
መዝሙር 77(78)፥19 አምላክን እንዲህ ብለው አሙት፦ "አምላክ በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን? καὶ κατελάλησαν τοῦ Θεοῦ καὶ εἶπαν· μὴ δυνήσεται ὁ Θεὸς ἑτοιμάσαι τράπεζαν ἐν ἐρήμῳ;

እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛን" τράπεζαν ሲሆን በዐረቢኛ ባይብል ላይ "ማኢዳህ" مَائِدَة ነው፥ በክርስትና ላይ ያለው የጌታ እራት ትምህርት በአራት አናቅጽ ታርሟል። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዲኑል ኢሥላም ከፍ እንዲል የላ ኢላሃ ኢለል ሏህ ባንዲራ እንዲውለበለብ መማር እና ማስተማር የአንድ ሙሥሊም መርሕ መሆን አለበት።

አሏህ ዒባደቱል ቀውሊያህ የሆነውን ደዕዋችሁን በኢኽላስ ይቀበላችሁ! አሚን።
ከሰማይ ነው!

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥49 ወደ እስራኤልም ልጆች መልእክተኛ ያደርገዋል፡፡ ይላልም፡- "እኔ ከጌታችሁ በተአምር ወደ እናንተ መጣሁ"፡፡ وَرَسُولًا إِلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنِّي قَدْ جِئْتُكُم بِآيَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ

"ከ-ሰማይ" ማለት በቀላሉ "ከ-አምላክ" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ ዮሐንስ በውኃ ያጠምቅ ነበር፥ ይህ የዮሐንስ በውኃ ማጥመቅ ወይም የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበረች፦
ዮሐንስ 1፥26 ዮሐንስ መልሶ፦ "እኔ በውኃ አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሞአል።
ማርቆስ 11፥30 የዮሐንስ ጥምቀት "ከ-ሰማይ" ነበረችን ወይስ "ከ-ሰው"? መልሱልኝ።

መልሱ "ከ-ሰማይ" ነበረች፥ "ከ-ሰማይ" ሲባል "ከ-አምላክ" ማለት ነው። ምክንያቱም "ከ-ሰማይ" ለሚለው ተቃራኒ "ከ-ሰው" የሚል ቃል አለ፥ ስለዚህ "የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበረች" ማለት ቃል በቃል ዮሐንስ የሚያጠምበት ውኃ አምላክ ዘንድ በቅድመ ህልውና"Pre Existence" ትኖር ነበር ማለት አይደለም። የዮሐንስ ጥምቀት ብቻ ሳይሆን ዮሐንስ እራሱ "ከ-አምላክ" ነው፦
ዮሐንስ 1፥6 "ከ-አምላክ" የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ "ሰው" ነበረ። Ἐγένετο ἄνθρωπος, ἀπεσταλμένος παρὰ Θεοῦ, ὄνομα αὐτῷ Ἰωάνης·

ዮሐንስ አምላክ ጋር ኖሮ ኖሮ የተላከ ሳይሆን አምላክ የሚለውን እና የሚናገረው መልእክት ሰቶት የተላከ ነቢይ ነው፥ በተጨማሪ "ሰው" ለሚለው የገባው ቃል "አንትሮፓስ" ἄνθρωπος ሲሆን "ሰው" መባሉ በራሱ ከተወለደ በኃላ "ከ-አምላክ" የተላከ መሆኑን ቁልጭ አርጎ ያሳያል። የአምላክን ቃል የሚሰማ "ከ-አምላክ ነው፣ የማይሰማ ደግሞ "ከ-አምላክ አይደለም፣ በጎ የሚያደርግ "ከ-አምላክ ነው። ያ ማለት የአምላክን ቃል የሚሰማ ሰው እና በጎ የሚያደርግ ሰማይ ላይ ከአምላክ ጋር አብሮ ኖሮ የመጣ ነው ማለት አይደለም፦
ዮሐንስ 8፥47 "ከ-አምላክ የሆነ" የአምላክን ቃል ይሰማል፤ እናንተ "ከ-አምላክ አይደላችሁምና" ስለዚህ አትሰሙም።
3 ዮሐንስ 1፥11 በጎ የሚያደርግ "ከ-አምላክ ነው"።
1 ዮሐንስ 4፥4: ልጆች ሆይ! እናንተ "ከ-አምላክ ናችሁ።
1 ዮሐንስ 4፥6 እኛ "ከ-አምላክ ነን"።

አይሁዳውያን፦ "ሰው ከመፈጠሩ በፊት ቅድመ ህልውና አለው" ብለው አያምኑም፥ ቅሉ ግን ኢየሱስ፦ "ይህ ሰው ከ-አምላክ አይደለም" "ይህ ሰው ከ-አምላክ ነው" ብለው ሲከራከሩ "ይህ ሰው ሰማይ ላይ ከአምላክ ጋር አብሮ ኖሮ የመጣ ነው ወይም አይደለም" ማለታቸው አልነበረም፦
ዮሐንስ 9፥16"ከፈሪሳውያንም አንዳንዶቹ፦ ይህ ሰው ሰንበትን አያከብርምና "ከ-አምላክ አይደለም" አሉ።
ዮሐንስ 9፥33 ይህ ሰው "ከ-አምላክ ባይሆን ምንም ሊያደርግ ባልቻለም ነበር።

እዚህ ድረስ በቅጡ እና በአግባብ ከተግባባን ዘንድ ኢየሱስም "ከ-ሰማይ" የሆነ "ሰው" ነው፦
1 ቆሮንቶስ 15፥47 ሁለተኛው "ሰው" "ከ-ሰማይ" ነው። ὁ δεύτερος ἄνθρωπος ἐξ οὐρανοῦ.

"ሰው" የሚለው ይሰመርበት! "ሰው" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "አንትሮፓስ" ἄνθρωπος ሲሆን ኢየሱስ ሰው የሆነው ከማርያም ሆኖ ሳለ ከተወለደ በኃላ ከአምላክ ስለተላከ "ከ-ሰማይ ነው" ተባለ እንጂ የተላከው ከተወለደ በኃላ ነው፦
ገላትያ 4፥4 አምላክ “ከ-ሴት የተወለደውን” ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ። ἐξαπέστειλεν ὁ Θεὸς τὸν Υἱὸν αὐτοῦ, γενόμενον ἐκ γυναικός, γενόμενον ὑπὸ νόμον,

“የተወለደው” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ጌኖሜኖን” γενόμενον ሲሆን “ጊኖማይ” γίνομαι ማለትም “ሆነ” ወይም “ተወለደ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “የሆነውን” ማለት ነው፥ ኢየሱስ ከማርያም ሰው መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ታዲያ ያ ሰው ለምን "ከ-ሰማይ" ተባለ? "ከ-ሰማይ" ማለትም "ከ-አምላክ" የተላከ ስለሆነ ነው፦
ዮሐንስ 7፥29 እኔ ግን "ከ-እርሱ ዘንድ ነኝ፥ እርሱም "ልኮኛልና" አውቀዋለሁ።
ዮሐንስ 6፥51 "ከ-ሰማይ" የወረደ ሕያው "እንጀራ" እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው "እንጀራ ሥጋዬ ነው"።

"እንጀራ ሥጋዬ ነው" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! "እንጀራ" በፍካሬአዊ "ሥጋውን" ካመላከተ "ከ-ሰማይ" የወረደ "እንጀራ" እኔ ነኝ" ሲል "ከ-ሰማይ" የወረደ "ሥጋ" እኔ ነኝ" ማለቱ ነው፥ ሥጋ የሆነ ከማርያም ከሆነ ከድንግል ማርያም ሰው ሆኖ የተወለደው ሕፃን ነው። ምክንያቱም አንድ ሰው ወንድ ወይም ሴት የሚሰኘው በማሕፀን ሲፀነስ ነውና፥ እውነተኛ እንጀራ የተባለውን የሥጋ መደብ እና የፆታ አንቀጽ ያለው ወንድ ልጅ ሲሆን ይህም ወንድ ልጅ "ከ-ሰማይ" የሰጠው አብ ነው። ለምሳሌ፦ ልጆች የአምላክ በጎ ስጦታ ናቸው፥ አስተዋይ ሚስት ደግሞ ፍጹም በረከት ናት፦
መዝሙር 127፥3 እነሆ ልጆች የአምላክ ስጦታ ናቸው።
ምሳሌ 18፥22 ሚስት ያገኘ በረከትን አገኘ።
ምሳሌ 19፥14 አስተዋይ "ሚስት ግን "ከ-አምላክ ዘንድ ናት"።

ስለዚህ በጎ ስጦታ ልጆች እና ፍጹም በረከት አስተዋይ ሚስት ከሰማይ ይወርዳሉ፦
ያዕቆብ 1፥17 በጎ ስጦታ ሁሉ እና ፍጹም በረከት ሁሉ "ከ-ላይ ናቸው"፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ "ከ-ብርሃናት አባት ይወርዳሉ"።

"ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ" የሚለው ይሰመርበት! በጎ ስጦታ ልጆች እና ፍጹም በረከት አስተዋይ ሚስት ከአብ ስለሚወርዱ ከመፈጠራቸው በፊት ቅድመ ህልውና አላቸውን? ወይስ ቃል በቃል ልጆች እና ሚስት ከሰማይ ወርደዋል? ኒቆዲሞስ ኢየሱስን "መምህር ሆነህ ከአምላክ ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን" ሲለው ተልኮ መምጣቱን እንጂ ቅድመ ህልውናን በፍጹም አያመለክትም፦
ዮሐንስ 3፥2 መምህር ሆነህ ከአምላክ ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን” አለው።

በእርግጥ መሢሑ ዒሣ ከጌታው በተአምር ወደ እስራኤል ልጆች የመጣ መልእክተኛ ነው፦
3፥49 ወደ እስራኤልም ልጆች መልእክተኛ ያደርገዋል፡፡ ይላልም፡- "እኔ ከጌታችሁ "በተአምር ወደ እናንተ መጣሁ"፡፡ وَرَسُولًا إِلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنِّي قَدْ جِئْتُكُم بِآيَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ

"ከጌታችሁ በተአምር ወደ እናንተ መጣሁ" የሚል ይሰመርበት! ነቢዩ ሙሣም በተመሳሳይ "ከጌታችሁ በተአምር ወደ እናንተ መጣሁ" በማለት ይናገራል፦
7፥105 "ከጌታችሁ ወደ እናንተ በተአምር መጣሁ"፡፡ የእስራኤልንም ልጆች ከእኔ ጋር ልቀቅ፡፡ قَدْ جِئْتُكُم بِبَيِّنَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ فَأَرْسِلْ مَعِيَ بَنِي إِسْرَائِيلَ

ሙሣ "ከጌታችሁ ወደ እናንተ በተአምር መጣሁ" ስላለ ቅድመ ህልውና እንደማያሳይ ሁሉ ዒሣም "ከጌታችሁ ወደ እናንተ በተአምር መጣሁ" ሲል ቅድመ ህልውናን አያሳይም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የጌታ መልአክ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

19፥19 «ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ፥ እኔ የጌታሽ መልእክተኛ ብቻ ነኝ» አላት፡፡ قَالَ إِنَّمَا أَنَا رَسُولُ رَبِّكِ لِأَهَبَ لَكِ غُلَامًا زَكِيًّا

"ጌታ" በግሪክ ሰፕቱጀንት"LXX" ውስጥ "ኩሪዮስ" κύριος ሲሆን "ዮድ ሄ ቫቭ ሔ" יְהוָֹה የሚለውን ቴትራ ግራማቶን ተክቶ መጥቷል፥ ብሉይ ኪዳን ላይ "የጌታ መልአክ" በኢ-አመልካች ውስን መስተአምር "አንጌሎስ ኩርዩ" ἄγγελος Κυρίου በሚል አሊያም "በአመልካች ውስን መስተአምር "ሆ አንጌሎስ ኩርዩ" ὁ ἄγγελος Κυρίου በሚል መጥቷል። ለምሳሌ፦ "የያህዌህ መልአክ" የሚለው "የጌታ መልአክ" በሚል መጥቷል፦
ዘፍጥረት 16፥7 የጌታ መልአክ በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት፤ ምንጩም ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ ነው። Εὗρε δὲ αὐτὴν ἄγγελος Κυρίου ἐπὶ τῆς πηγῆς τοῦ ὕδατος ἐν τῇ ἐρήμῳ, ἐπὶ τῆς πηγῆς ἐν τῇ ὁδῷ Σούρ.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ጌታ" ለሚለው የገባው ቃል "ኩሪዮስ" κύριος ሲሆን "ያህዌህ" יְהוָֹה የሚለውን ቴትራ ግራማቶን ተክቶ የመጣ ነው፥ "መልአክ" ለሚለው የገባው ቃል "አንጌሎስ" ἄγγελος ሲሆን "መልእክተኛ" ማለት ነው። መልአኩ ከጌታ ይዞት የመጣው መልእክት "ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ፥ ከብዛቱም የተነሣ አይቆጠርም" የሚል ነው፦
ዘፍጥረት 16፥10 የጌታ መልአክ፦ “ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ፥ ከብዛቱም የተነሣ አይቆጠርም” አላት። καὶ εἶπεν αὐτῇ ὁ ἄγγελος Κυρίου· πληθύνων πληθυνῶ τὸ σπέρμα σου, καὶ οὐκ ἀριθμηθήσεται ὑπὸ τοῦ πλήθους.

"የጌታ መልአክ" ማንኛውንም ከአንዱ ጌታ አምላክ የሚላክ ሰማያዊ እና መንፈሳዊ ፍጡር ሊያመለክት የሚችል ቃል ነው። አብርሃም ልጁን ሊሠዋ የነበረው ለጌታ አምላክ ሆኖ ሳለ መልአኩ መልእክተኛ ነውና የጌታን መልእክት፦ "አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና" በማለት ተናግሯል፦
ዘፍጥረት 22፥11 የጌታ መልአክ ከሰማይ ጠራና፦ “አብርሃም አብርሃም፡” አለው፤ እርሱም፦ “እነሆኝ፡” አለ። እርሱም፦ “በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፥ አንዳችም አታድርግበት፤ "አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና" አምላክን የምትፈራ እንደ ሆንህ አሁን አውቄአለሁ፡” አለ። καὶ ἐκάλεσεν αὐτὸν ἄγγελος Κυρίου ἐκ τοῦ οὐρανοῦ καὶ εἶπεν· ῾Αβραάμ, ῾Αβραάμ. ὁ δὲ εἶπεν· ἰδοὺ ἐγώ. καὶ εἶπε· μὴ ἐπιβάλῃς τὴν χεῖρά σου ἐπὶ τὸ παιδάριον μηδὲ ποιήσῃς αὐτῷ μηδέν· νῦν γὰρ ἔγνων, ὅτι φοβῇ σὺ τὸν Θεὸν καὶ οὐκ ἐφείσω τοῦ υἱοῦ σου τοῦ ἀγαπητοῦ δι᾿ ἐμέ.

"አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና" የሚለው መልእክት ከጌታ በመልአኩ የተላለፈ መልእክት መሆኑን የምንረዳው ይህ የጌታ መልአክ ለአብርሃም ከሰማይ ሁለተኛ ጊዜ ጠርቶ “ጌታም፦ ‘በራሴ ማልሁ፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና" ይላል" ማለቱ ነው፦
ዘፍጥረት 22፥15 የጌታ መልአክም አብርሃምን ከሰማይ ሁለተኛ ጊዜ ጠራው፥ እንዲህም አለው፦ “ጌታም፦ ‘በራሴ ማልሁ፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና" "ይላል"። καὶ ἐκάλεσεν ἄγγελος Κυρίου τὸν ῾Αβραὰμ δεύτερον ἐκ τοῦ οὐρανοῦ, λέγων· κατ᾿ ἐμαυτοῦ ὤμοσα, λέγει Κύριος, οὗ εἵνεκεν ἐποίησας τὸ ρῆμα τοῦτο, καὶ οὐκ ἐφείσω τοῦ υἱοῦ σου τοῦ ἀγαπητοῦ δι᾿ ἐμέ,

"ይላል" የሚለው ይሰመርበት! መልአኩ "ይላል" ካለ "አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና" ያለው ጌታ አምላክ ነው፥ አስተላላፊው ደግሞ የጌታ መልአክ ነው። "አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና" መልእክቱ የላኪው እንጂ የተላኪው አይደለም።
ወደ አዲስ ኪዳን ስንማትር የጌታ መልአክ ወደ ዘካርያስ የተላከ መልአክ ነው፥ ይህም መልአክ "እኔ በአምላክ ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" ብሎአል፦
ሉቃስ 1፥11 የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው።
ሉቃስ 1፥19 መልአኩም መልሶ፦ “እኔ በአምላክ ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር።

ብሉይ ኪዳን ላይ "የጌታ መልአክ" የተባለውን ሁሉ ለኢየሱስ የሚሰጡ ሰዎች አዲስ ኪዳን ላይ ገብርኤል "የጌታ መልአክ" መባሉን ሲያውቁ ምን ይውጣቸው ይሆን? ይህ የጌታ መልአክ ለዮሴፍ በሕልም የታየው ነው፦
ማቴዎስ ፥1፥20 እርሱ ግን ይህን ሲያስብ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው።

ይህ ጥቅስ የጌታ መልአክ ኢየሱስ ሳይሆን ሰማያዊ ፍጡር የሆነ መልአክ ነው፥ የጌታ መልአክ ኢየሱስ ሲወለድ ለማብሰር መጥቶ ነበረ፦
ሉቃስ 2፥9 እነሆም "የጌታ መልአክ" ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ።

የጌታ መልአክ ሰብአ ሰገል ከሄዱ በኋላ እና ሄሮድስም ከሞተ በኋላ እነሆ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶታል፦
ማቴዎስ 2፥13 እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ፦
ማቴዎስ 2፥19 ሄሮድስም ከሞተ በኋላ እነሆ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፦

ኢየሱስ በሚያገለግልበት ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ ውኃውን ያናውጥ ነበር፦
ዮሐንስ 5፥4 አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ ውኃውን ያናውጥ ነበርና።

የጌታ መልአክ በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ ሐዋርያትን አወጣቸው፣ የጌታም መልአክ ፊልጶስን አናገረው፣ የጌታ መልአክ ጴጥሮስን አናገረው፣ የጌታ መልአክ ሄሮድስን መታው በትልም ተበልቶ ሞተ፦
የሐዋርያት 5፥19 የጌታ መልአክ ግን በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ አወጣቸውና።
የሐዋርያት 8፥26 የጌታም መልአክ ፊልጶስን፦ "ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ፡፥" አለው።
የሐዋርያት 12፥7 እነሆም የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ፥ ጴጥሮስንም ጎድኑን መትቶ አነቃውና፦ "ፈጥነህ ተነሣ" አለው። ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ።
የሐዋርያት 12፥23 ለአምላክ ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ።

ብሉይ ኪዳን ላይ "የጌታ መልአክ ኢየሱስ ነው" የሚል በቀጥታ ሆነ በተዛዋዋሪ ማስረጃ እና መረጃ የለም፥ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊያን "ብሉይ ኪዳን ላይ "የጌታ መልአክ" የተባለው ኢየሱስ ነው" ብለው በቀጥታ ሆነ በተዛዋዋሪ ስላልተናገሩ "የጌታ መልአክ ኢየሱስ ነው" የሚለው ንግግር ምናባዊ ቅዠት እንጂ ነባራዊ እውነታ አይደለም። በቁርኣን "የጌታ መልአክ" ጂብሪል ነው፦
19፥19 «ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ፥ እኔ የጌታሽ መልእክተኛ ብቻ ነኝ» አላት፡፡ قَالَ إِنَّمَا أَنَا رَسُولُ رَبِّكِ لِأَهَبَ لَكِ غُلَامًا زَكِيًّا

ጂብሪል መልእክተኛነቱ ለጌታ ከሆነ ልጅን የሚሰጥ አሏህ ስለሆነ ከጌታ ይዞት የመጣው መልእክት፦ "ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ" የሚል ነው፥ "መልአክ" مَلْأَك የሚለው ቃል "ለአከ" لَأَكَ ማለትም "ላከ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መልእክተኛ" ማለት ነው። የጌታ መልአክ "ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ" "አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና" የሚል መልእክት ከጌታው ይዞ እንደመጣ የጌታ መልአክ ጂብሪልም "ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ" የሚለውን የጌታን መልእክት ከጌታ አሏህ ይዞ የመጣ ነው። ሊአሀበ" لِأَهَبَ የሚለው የግሥ መደብ "ፊዕሉል ሙዷሪዕ" فِعْل ٱلْمُضَارِع ሲሆን የሚጠጋው ወደ አሏህ ነው፦
42፥49 የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ ለሚሻው ሰው ሴቶችን ይሰጣል፥ ለሚሻውም ሰው ወንዶችን ይሰጣል፡፡ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ يَهَبُ لِمَن يَشَاءُ إِنَاثًا وَيَهَبُ لِمَن يَشَاءُ الذُّكُورَ

ተግባባን? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የያህዌህ መልአክ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

22፥75 አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፥ ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል። አሏህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ اللَّهُ يَصْطَفِي مِنَ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا وَمِنَ النَّاسِ ۚ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِيرٌ

"የሰውን ልጅ የሚመስል" የሚል ቃል እንደየ ዐውዱ ለተለያየ ፍጡር ይውላል፥ ለምሳሌ፦ ለዳንኤል የተገለጠለት መልአክ "የሰው ልጅ የሚመስል" ተብሎአል፦
ዳንኤል 10፥16 እነሆም "የሰው ልጅ የሚመስል" ከንፈሬን ዳሰሰኝ።

ራእይ ላይም አንድ በስም ያልተገለጠ መልአክ "የሰውን ልጅ የሚመስል" ተብሎአል፦
ራእይ 14፥14 አየሁም እነሆም ነጭ ደመና፥ በደመናውም ላይ "የሰውን ልጅ የሚመስል" ተቀምጦአል፥ በራሱም ላይ የወርቅ አክሊል በእጁም ስለታም ማጭድ ነበረው።

ይህ መልአክ በስም ያልተገለጠ ፍጡር መሆኑን የምናውቀው ሌላ ፍጡር መልአክ በትእዛዛዊ ግሥ፦ "ስደድ" "እጨድ" ብሎ ያዘዋል፦
ራእይ 14፥15 "ሌላ" መልአክም ከመቅደሱ ወጥቶ በደመናው ላይ ለተቀመጠው፦ "የማጨድ ሰዓት ስለ ደረሰ ማጭድህን ስደድ እና እጨድ! የምድሪቱ መከር ጠውልጓልና" ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። Καὶ ἄλλος ἄγγελος ἐξῆλθεν ἐκ τοῦ ναοῦ, κράζων ἐν φωνῇ μεγάλῃ τῷ καθημένῳ ἐπὶ τῆς νεφέλης Πέμψον τὸ δρέπανόν σου καὶ θέρισον, ὅτι ἦλθεν ἡ ὥρα θερίσαι, ὅτι ἐξηράνθη ὁ θερισμὸς τῆς γῆς.

እዚህ አንቀጽ "ሌላ" የሚለው የገባው ቃል "አሎስ" ἄλλος ሲሆን "ሌላ ተመሳሳይ ዓይነት"Another the same kind" ማለት ነው፥ ስለዚህ ታዛዡ መልአክ እና አዛዡ መልአክ ሁለቱም ተመሳሳይ ተፈጥሮ ያላቸው ፍጡራን መላእክት ናቸው። "ሄቴሮስ" ἕτερος እራሱ ተመሳሳይ ተፈጥሮ ላላቸው ይገባል፦
ማቴዎስ 8፥21 ከደቀ መዛሙርቱም "ሌላው"፦ “ጌታ ሆይ፥ አስቀድሜ እንድሄድ አባቴን እንድቀብር ፍቀድልኝ፡” አለው። ἕτερος δὲ τῶν μαθητῶν εἶπεν αὐτῷ Κύριε, ἐπίτρεψόν μοι πρῶτον ἀπελθεῖν καὶ θάψαι τὸν πατέρα μου.

"ሄቴሮስ" ἕτερος በብሉይ ኪዳን ግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ ተመሳሳይ ተፈጥሮ ላላቸው ውሏል፥ ዘፍጥረት 29፥10 ዘፍጥረት 30፥24 ተመልከት!
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ዘካሪያስ ጋር የመጡት ሁለት መላእክት ተመሳሳይ ተፈጥሮ ያላቸው ፍጡራን መላእክት ናቸው፦
ዘካርያስ 2፥3 እነሆም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው "መልአክ" ወጣ፥ "ሌላም" መልአክ ሊገናኘው ወጣ። וְהִנֵּ֗ה הַמַּלְאָ֛ךְ הַדֹּבֵ֥ר בִּ֖י יֹצֵ֑א וּמַלְאָ֣ךְ אַחֵ֔ר יֹצֵ֖א לִקְרָאתֹֽו׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሌላ" ለሚለው ገላጭ ቅጽል የገባው ቃል "አኼር" אַחֵ֔ר ሲሆን ሁለቱም ተመሳሳይ ተፈጥሮ ያላቸው ፍጡራን መላእክት መሆናቸውን አመላካች ነው፥ "ሌላ ሰው ይመጣል" ብል ፊተኛው ሰው እና ሌላው ሰው ተመሳሳይ ተፈጥሮ ያላቸው ፍጡራን ሰዎች አመላካች እንደሆነው ማለት ነው። ሌላይኛው መልአክ ፊተኛውን መልአክ፦ "ሩጥ" "በለው" በማለት በትእዛዛዊ ግሥ ያዘዋል፦
ዘካርያስ 2፥4 እንዲህም አለው፦ “ሩጥ፥ ይህንም ጕልማሳ እንዲህ በለው፦ ኢየሩሳሌም በውስጥዋ ካሉት ሰዎች እና እንስሶች ብዛት የተነሣ ቅጥር እንደሌላቸው መንደሮች ሆና ትኖራለች"።

"እኔ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ" ባዩ ያህዌህ ስለሆነ ሁለተኛው መልአክ፦ "እኔ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ፥ በውስጥዋም ክብርን እሆናለሁ" ይላል ያህዌህ" በማለት ይናገራል፦
ዘካርያስ 2፥5 "እኔ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ፥ በውስጥዋም ክብርን እሆናለሁ" ይላል ያህዌህ።

ሁለተኛው መልአክ "ይላል ያህዌህ" ማለቱ በራሱ ያህዌህ ሲናገር የሚያስተላልፍ ፍጡር መልአክ መሆኑ ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል፥ መልአኩም፦ "አንቺ ከባቢሎን ሴት ልጅ ጋር የምትኖሪ ጽዮን ሆይ! ኰብልዪ" ያህዌህ እንዳለ ይነግረናል፦
ዘካርያስ 2፥7 “አንቺ ከባቢሎን ሴት ልጅ ጋር የምትኖሪ ጽዮን ሆይ! ኰብልዪ” እንዲህ ይላልና ጸባዖት ያህዌህ። הֹ֥וי צִיֹּ֖ון הִמָּלְטִ֑י יֹושֶׁ֖בֶת בַּת־בָּבֶֽל׃ ס כִּ֣י כֹ֣ה אָמַר֮ יְהוָ֣ה צְבָאֹות֒

"እንዲህ ይላልና ጸባዖት ያህዌህ" ቁጥር 8 ላይ ቢኖርም ቁጥር 7 ላይ ያለውን መልአኩ "ይላልና" በማለት እየተናገረ ነው፥ መልአኩ በመቀጠል፦ "ልኮኛል" በማለት የያህዌህ መልእክተኛ መሆኑን ይናገራል፦
ዘካርያስ 2፥8 ከክብሩ በኋላ ወደ በዘበዙአችሁ አሕዛብ "ልኮኛል"፤ የሚነካችሁ የዓይኑን ብሌን የሚነካ ነውና።
ዘካርያስ 2፥9 እነሆ እጄን በላያቸው አወዛውዛለሁ፥ ተገዝተው ለነበሩት ብዝበዛ ይሆናሉ፤ ጸባዖት ያህዌም እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ።

"ጸባዖት" የሚለው የግዕዝ ቃል "ሰባኡት" צְבָא֖וֹת ከሚል የዕብራይስጥ የተገኘ ሲሆን "ሠራዊት" ማለት ነው፥ ያህዌህ የሠራዊቱ የመላእክት ጌታ መሆኑን ለማሳየት የገባ ነው። መልአኩም "ይላል ያህዌህ" በማለት ንግግሩን ይቀጥላል፦
ዘካርያስ 2፥10 "የጽዮን ልጅ ሆይ! እነሆ መጥቼ በመካከልሽ እኖራለሁና ዘምሪ ደስም ይበልሽ" ይላል ያህዌህ።

"በመካከልሽ እኖራለሁ" የሚለው ያህዌህ ነው፥ በቀጣይ "በመካከልሽም እኖራለሁ" የሚለው ሁለተኛው ፍጡር መልአክ ነው፦
ዘካርያስ 2፥11 በዚያም ቀን ብዙ አሕዛብ ወደ ያህዌህ ይጠጋሉ፥ ሕዝብም ይሆኑኛል፤ በመካከልሽም እኖራለሁ፥ ጸባዖት ያህዌህም ወደ አንቺ እንደ ላከኝ ታውቂአለሽ።
ይህ የሚያሳየው መልአኩ ያህዌህ መሆኑን ሳይሆን የያህዌህ መልአክ የያህዌህ ወኪል፣ ልኡክ፣ እንደራሴ መሆኑን ነው። ለምሳሌ፦ የያህዌህ ታቦት የሰው እጅ ሥራ ፍጡር ነው፥ ግን ታቦቱ የያህዌህ መገኘት እንደ ራሴ ነው፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥2 ንጉሡ ነቢዩን ናታንን፦ እኔ ከዝግባ በተሠራ ቤት ተቀምጬአለሁ፥ የያህዌህ ታቦት ግን በመጋረጆች ውስጥ እንደ "ተቀመጠ" እይ" አለው።

በመጋረጃ ድንኳን የተቀመጠው የያህዌህ ታቦት ሆኖ ሳለ ያህዌህ ግን "በድንኳን እና በማደሪያ እሄድ ነበር እንጂ በቤት "አልተቀመጥሁምና" ብሎአል፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥5 ሂድ፥ ለባሪያዬ ለዳዊት ንገረው፦ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ የእስራኤልን ልጆች ከግብፅ ምድር ካወጣሁበት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በድንኳን እና በማደሪያ እሄድ ነበር እንጂ በቤት "አልተቀመጥሁምና" አንተ የምኖርበትን ቤት አትሠራልኝም"።

የያህዌህ ታቦት የያህዌህ መገኘት እንጂ ታቦቱ ያህዌህ እንዳልሆነ ሁሉ የያህዌህ መልአክም የያህዌህ መገኘት እንጂ ያህዌህ በፍጹም አይደለም። የያህዌህ ታቦት ወደ ሰፈሩ በገባ ጊዜ ፍልስጥኤማውያን፦ "አምላክ ወደ ሰፈሩ ገብቷል" አሉ፦
1 ሳሙኤል 4፥6 የያህዌህም ታቦት ወደ ሰፈሩ እንደገባ አስተዋሉ። וַיֵּ֣דְע֔וּ כִּ֚י אֲרֹ֣ון יְהוָ֔ה בָּ֖א אֶל־הַֽמַּחֲנֶֽה׃
1 ሳሙኤል 4፥7 ፍልስጥኤማውያንም ፈርተው፦ "አምላክ ወደ ሰፈሩ ገብቷል" አሉ። וַיִּֽרְאוּ֙ הַפְּלִשְׁתִּ֔ים כִּ֣י אָמְר֔וּ בָּ֥א אֱלֹהִ֖ים אֶל־הַֽמַּחֲנֶ֑ה

ሁለቱም ጥቅስ ላይ "ገባ" ለሚለው የገባው ቃል "ባ" בָּ֖א ሲሆን "መጣ" ማለት ነው፥ ወደ ሰፈሩ የመጣው ማን ነው? ታቦት ወይስ አምላክ? የታቦቱ መምጣት የአምላክ መምጣት እንጂ ታቦቱ አምላክ ካልሆነ የመልአኩ መኖር የአምላክ መኖር እንጂ መልአኩ አምላክ አይደለም። ሙሴ በታቦቱ መጓዝ እና ማረፍ ጊዜ ያህዌህን ያነጋግር ነበር፦
ዘኍልቍ 10፥35 ሙሴም ታቦቱ በተጓዘ ጊዜ፦ ያህዌህ ሆይ! ተነሣ፥ ጠላቶችህም ይበተኑ፥ የሚጠሉህም ከፊትህ ይሽሹ" ይል ነበር። ባረፈም ጊዜ፦ ያህዌህ ሆይ! ወደ እስራኤል እልፍ አእላፋት ተመለስ" ይል ነበር።

ሙሴ "ተነሳ" "ተመለስ" እያለ በሁለተኛ መደብ ታቦቱን አላኮ እና አስታኮ መናገሩ ታቦቱ ያህዌህ ነው ወይስ የያህዌህ ነው? ታቦቱ እኮ የሙሴ የእጅ ሥራ ነው፦
ዘዳግም 10፥3 ከግራርም እንጨት ታቦትን ሠራሁ።

"መልአክ" በዕብራይስጥ "ማላህ" מֲלְאָךְ ሲሆን "መልእክተኛ" ማለት ነው፥ "መላሆት" מַלְאֲכוּת ማለት "መልእክት" ማለት ሲሆን መልእክተኛው ከላኪው ተቀብሎ የሚናገረው መልእክት የላኪው እስከሆነ ድረስ "በመካከልሽ እኖራለሁ" የሚለውን መልእክት መልአኩ ቢናገርም እንኳን የሚያስረዳው መልአኩ ላኪው ያህዌን መሆኑን ሳይሆን መልአኩ መልእክት አድራሽ መሆኑን ብቻ ነው እንጂ ፍጡር መልአክ ፈጣሪ አይሆንም። ፈጣሪ ፈጣሪ ከላከ ሁለት ፈጣሪ ይሆናልና አያስኬድም፥ ፈጣሪ ግን አንደ ነው። አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፦
22፥75 አሏህ ከመላእክት ውስጥ መልእክተኞችን ይመርጣል፥ ከሰዎችም እንደዚሁ ይመርጣል። አሏህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ اللَّهُ يَصْطَفِي مِنَ الْمَلَائِكَةِ رُسُلًا وَمِنَ النَّاسِ ۚ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِيرٌ

"ለዘካሪያስ የተገለጠው ሁለተኛው መልአክ ኢየሱስ ነው" የሚለው ትምህርት እንዲህ ድባቅ ይገባል፥ ኢየሱስን ብሉይ ኪዳን ላይ አስገብቶ መልአክ የማድረግ አባዜ የተጠናወታቸው ሰዎች ለአሁኑ አልተሳካላቸውም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tgoop.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ለመጪው ትውልድ የሚሆን መተግበሪያ"Application" እና ድረ ገጽ"Website" ሁለት ወንድሞች ሠርተው አበርክተዋል። በዱዓችሁ አትርሷቸው!

ለአንድሮይድ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details?id=net.wahidcom&pli=1

ለiOS ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/wahid-islamic-apologist/id6743720489?platform=iphone
2025/05/29 21:00:35
Back to Top
HTML Embed Code: