Telegram Web
🔴 ትዳር ክቡር ነው || አትፋቱ || ...
Enqo silassie
ትዳር ክቡር ነው አትፋቱ
             
Size:-64.2MB
Length:-1:09:17

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
አሐቲ ድንግል
ማርያም ማለት ምን ማለት ነው?

ማርያም ማለት፦
እግዝእት:-
እመቤት ማለት ነው የዓለሙን ንጉስ በመውለዷ ከፈጣሪ በታች የፍጥረት ንግስት ሆናለችና፤

ጸጋ ዘተውኅበት ለኩሉ ዓለም፦ ለዓለሙ ሁሉ የተሰጠች ጸጋ ማለት ነው። ለአበው በተስፋ የሰጣቸው ሲሆን ለእኛ ደግሞ ከመስቀሉ ሥር እናት ትሁናችሁ ብሎ ሰጥቶናልና። (ዮሐ ፲፱፤፳፮) ለዚህም ነው ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ ንግሲቲቱ በቀኝህ ትቆማለች የሚለውን የዳዊት መዝሙር ሲተረጉም In becoming the mother of creator she become the Mistress of all creation (የፈጣሪ እናት በሆነች ጊዜ የፍጥረታት ሁሉ ንግስት እመቤት ሆናለችና በማለት ተርጉሞታል። (መዝ 44፤9)

ተስፋ ማለት ነው፦ ለአዳም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ካለው ጀምሮ መድኃኒቴን የምትወልጅልኝ ልጄ እያለ ተስፋ አድርጓት በልቦናው መዝገብነት ይዟት የኖረ ስንቁ ናት። አበውም ድንግል ማርያምን መቼ ፀሐይ ክርስቶስን ወልዳልን ከቁረ መርገም ድነን አይተነው እያሉ ተስፋ አድርገዋት ነበር። ተስፋቸው ክርስቶስም ከእርስዋ ተወልዶ ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን ገብተዋል። ለዚህ ምስክር የሚሆነን አረጋዊ ስምዖን "ጌታ ሆይ አገልጋይህን ዛሬ ታሰናብተዋለህ፥ አቤቱ በሰላም እንዳዘዝክ አይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና በህዝብ ፊት ሁሉ ያዘጋጀኸውን ለአሕዛብ ብርሃንን ትገልጽ ዘንድ፥ ለእስራኤልም ክብርን" በማለት ተስፋውን አይቶ አርፏል። (ሉቃ 2፥29)

የባሕር ከርቤ (Myrrh of the sea) ማለት ነው። ይህ ከርቤ እጅግ ውድ ዋጋ ያለው ከዘይት ጋር ተጨምሮ በጠበብተ ኦሪት ተቀምሞ ለንዋያተ ቅድሳት ማክበሪያ የታዘዘ ሽቱ ነው። ሙሴ ደብተራ ኦሪቱን በኦሪት መቅደሱ ያሉትን ሁሉ በዚህ ሽቱ እንዲቀባ ታዟል። ሽቱ ያረፈባቸውን የነካ ሁሉ እንደሚቀደስ እግዚአብሔር ለሙሴ ነግሮታል። ባሕር የተባለ ይህ ዓለም ሲሆን እመቤታችንም ከእርስዋ ስጋን ነስቶ ክርስቶስ ተብሎ ስሙ እንደ ዘይት ተዋህዶን ክርስቲያን ተብለን እንድንጣፍጥ የድኅነት መሳሪያ የመዓዛ መንፈሳዊ ምንጭ ናትና የባህር ሽቱ ትባላለች።

ሽቱ ያረፈበትን የነካ ሁሉ እንደሚቀደስ በልጇ ስም አምነው ተጠምቀው በእምነት የሚቀርብ ሁሉ ይጣፍጣልና ይላሉ አበው!

የባሕር ኮከብ (Star of the seas) ማለት ነው። ባሕር የተባለ ይህ ዓለም ነው፥ በባሕር የሚበላም የማይበላም ደግሞ ክፉም ፍጥረት እንዳለ በዚህ ዓለምም አማኒም ከሓዲም መናፍቅም ጻድቅም ኃጥእም ይኖራልና፥ ዳግመኛም ባሕር ከሁከት አይርቅም ይች ዓለምም ከሁከት አትርቅምና፥ በባህር ላይ ሲጓዙ በመርከብ ላይ ሆነው የንጋት ኮከብን አብነት አድርገው ከተጓዙ ካሰቡት ይደረሳል። ሰብአ ሰገልን ኮከብ እየመራ ቤተልሔም እንዳደረሳቸው ማለት ነው። እንዲሁም ሁሉ እመቤታችን በዚህ ዓለም የክህደት የኃጢአት ሞገድ እንዳያጠፋን የተረፍንባት መርከባችን ናት።

ብርህት (Illuminated) ማለት ነው። ብርሃኗ ከፀሐይ ይበልጣል፤ መለወጥ የሌለባት የድኅነት በር ናት ውበቷም በፍፁም ክብርና ሞገስ የተሸለመ ነው፤ እውነት በእውነት የመና መሶብ ነች። ጽድልት መባሏ ነውርና ነቀፋ የሌለበት የእግዚአብሔር እናት በመሆኗ ነው።

አሐቲ ፍቅርት፦ ብቻዋን የምትወደድ (Beloved One) ማለት ነው። ንጉስ ውበትሽን ወዷልና ተብሎ የተዘመረላት እግዚአብሔር መዓዛ ድንግልናዋን ወዶ ከእርሷ ሰው እስኪሆን ድረስ፥ ፍጥረትን ሁሉ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብቅሎ የሚመግብ ጌታ ጡቶቿን ጠብቶ እስከማደግ ድረስ ደርሶ ብቻዋን በእግዚአብሔር የተወደደች ናትና።

የባሕር ምንጭ (Drop of the sea) ማለት ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም በሦስት ዋና ዋና የድኅነት ምንጭ ሆናለችና። የጥምቀት፥ የቁርባን፥ የቅዳሴ ናቸው። ይህም ማለት ከጎኑ የፈሰሰው ውሃ፥ ከጎኑ የፈሰሰው ደም ከእርሷ ባህሪ የተገኘ ነውና ጌታ የተጠመቀውም ከእርሷ በነሳው ስጋ ነው የምንበላው ቅዱስ ስጋው የምንጠጣው ክቡር ደሙ ከእርሷ የነሳው ነውና የቁርባን ምንጭ ትባላለች።

ዳግመኛም ማርያም ማለት ልዕልት ማለት ነው።.... (ቀጣዩን መጽሐፉን ገዝተው አንብቡ)


አሐቲ ድንግል በአባ ገብረኪዳን ግርማ ገጽ 257 የተወሰደ
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ...
ማኅበረ ጽዮን
የጸናውን አስቡ
             
Size:-63.4MB
Length:-1:08:26

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
Audio
ሰማንያ አራት ዓመት
ሉቃ 2÷37
Size:-29.4MB
Length:-2:08:31
አዲስ አበባ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ የካቲት 8/2014ዓ.ም የተሰጠ

በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
http://www.tgoop.com/abagebrekidan
የእመቤታችን መከራዋን ማሰብ
መስቀል ተሸክሞ ወደሞት ሲሄድ ያየችው ጊዜ

በፍጡራን መካከል ካለ ፍቅር በጥልቅ የምትወድ እንደ እናት ማንም የለም። እጅጉን የጠበቀ ነው የሚባለው የባልና ሚስት ፍቅር እንኳ እናት ለልጇ ካላት ፍቅር አይተካከልም ለምን ቢሉ ባል ከሚስቱ የሚፈልገው የሚስት ፍቅር ስላለ ነው የወደዳት ሚስትም ከባሏ የምትሻው ፍቅር ስላለ ነው የወደደችው። እናት ግን የምትወደው ልጇ ስለሆነ ብቻ ነው። ማንም ሰው እናቴ የምትወደኝ ከዚህ ተነስታ (on account of this....) ብሎ መናገር አይችልም።

እናት ደስታዋ ከልጇ በምታገኘው ነገር ሳይሆን ለልጇ በምትሰጠው ነገር ነው። ደስታዋም የልጇ መሆንና አለመሆን ነው። እናት ልጇ ራሷ ለእናትነት ደርሳም ቢሆን ዛሬም እንደታናሽነቷ ታስብላታለች። እናት የምትኖረው ለልጇ ነው። ደስታዋም ልጇ ነው። የልጇ ስብራት የእርሷን ያህል እኩል ይሰማታል። የእናት ምጥ የወለደች ልት ብቻ የሚያበቃ አይደለም። ልጆቿ በተጎዱ ቁጥር ልቧ በኀዘን ሰይፍ ይወጋል። አንድ ደራሲ እናት ስለልጇ የምታዝነውን ኀዘን "All mother feel the suffering of their children as their own. ሁሉም እናቶች የልጆቻቸውን መከራ እንደራሳቸው ይሰማቸዋል" ሲል የገለጸው እርግጥ ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈ አንዲት ሴት ልጇን ጋኔን አሞብባት ነበርና ወደ ጌታ መጥታ እየጮኸች "ልጄን አሞብኛልና እባክህ እርዳኝ" ብላ ነበር የለመነችው። ማቴ15÷22

ልብ በሉ ይህች ሰው ጌታን "እባክህ ልጄን እርዳት" አላለችም ይልቁንም የልጇን ኀዘን እንደራስዋ ቆጥራ ይሰማት ነበርና "እባክህ እርዳኝ" አለችው እንጂ። እናስተውል ይህች ሴት ልጇ ታማለች እንጂ የሚደበድባት የለም፣ እናቷም የማስታመም እድል አላት፣ የሞት ፍርድ አልተፈረደባትም ግን የታመመች ብቻ እናቷ እስክትጮህ ድረስ አለቀሰች እንጂ።

እስኪ የእመቤታችንን ኀዘን እናስብ
ጌታ ከጲላጦስ አደባባይ እስከ ጎልጎታ አስራ አራት ምዕራፎች ያሉት የመስቀል ጉዞ አድርጓል። አራተኛው ከእናቱ ጋር የተያዩበት ቦታ ነው። ወዮ ያቺ ሰአት ምን ያህል አስጨናቂ ናት። እናት ልጇ ሲነግስላት፣ ዘውዱ ሲደፋላት ደስ ይላታል ድንግል ግን አንዱን የድንግልናዋን ፍሬ ራሱን የሚበሱ የእሾህ ጉንጉኖች በራሱ ላይ ደፍቶ አየችው። ከእነዚያ አንዱን እሾህ እንኳን ለልጇ መንቀል አለመቻሏ ለድንግሊቱ እናት ምን ያህል መራራ ነው።

እሾሁን ልትነቅልለት ይቅርና እየወደቀ እየተነሳ ሲገረፍ ሲዳፋ ያደረ በደም የተሸፈነ ፊቱን ለማየትስ እንኳን እድል አላገኘችም። የልጇን ደስታ ለምትሻ እናት የመከራ ፊቱን አቅፋ እንዳታለቅስ እንኳን ስትከለከል እንደምን ያለ የተሳለ የኀዘን ሰይፍ ወግቷት ይሆን። ወየው እመቤቴ አዕላፈ እስራኤል በልጅሽ ላይ እየደነፉ ላንቺ አንድስ እንኳን የሚያረጋጋ አልነበረሽም። ስቃዩ ገርፈው ይለቁታል እንዳይባል ደግሞ እንደዚያ እያደረጉ የሚወስዱት ሊገድሉት መሆኑ ሰይፉ ይበልጡን ልብዋን እንደምን ይወጋው።
የእናት ሀዘን ለታመመች ልጅ የሚያስጨንቅ ከሆነ አጥንቱ እስኪቆጠር ተገርፎ ሊሞት የሚወስደን ልጇን ለምታይ ድንግልማ ምን ያህል የሀዘን ሰይፍ ይሆን? ነብዩ ኤርምያስ የሚያጽናናኝ የነፍሴን የሚያበረታታት ከእኔ ርቋልና ስለዚህ አለቅሳለሁ። አይኔ ውሃ ያፈሳል ፣ ጠላት በርትቷል ፣ ልጄም ጠፍቷል ብሎ እተናገረው ያላጽናኝ እየተገፋፋሽ ባለቀሰሰሽ በድንግል ተፈጸመ። ሰቆ 1÷15 እመቤታችንን የምንወዳት ይህንን የመሰለው መከራዋ ሲረዳን ነው።

አሐቲ ድንግል ገጽ 553 - 554
በአባ ገብረ ኪዳን ግርማ

https://www.tgoop.com/abagebrekidan
https://www.tgoop.com/abagebrekidan
2025/02/23 01:58:18
Back to Top
HTML Embed Code: