አቤቱ ሙሉ አርገኝ እኔም ሙሉ እሆናለሁ። አቤቱ አንተ አዋቂ ባለይቅርታ ሐኪም ሆይ፣ ቸርነትህን ባርያህ እሻለሁ፡፡ የነፍሴን ቁስል ፈውስ። በዘለዓለማዊው እቅድህ ያለኝን ቦታ አውቅ ዘንድ የልቡናዬን ዐይን አብራ። ምንም ልቤ እና አእምሮዬ ቢታመሙም ጸጋህ ትፈውሳቸው ዘንድ ፍቀድ።
የሰውን የልቡን ሐሳብ ውስጡንም የምትመረምር ላንተ አቤቱ እኔ ምን እላለሁ? አንተ ነፍሴ ውሃን እንዳጣ ምድረ በዳ አንተን እንደተጠማች ልቤም አንተን እንደምትሻ ታውቃለህ። የአንተ ጸጋ የሚወዱህን ሁል ጊዜ ታድናለች፡፡
ሁልጊዜ ትሰማኛለህና አቤቱ አሁን ከጸሎቴ ፊትህን አታዙር። ልቡናዬ አንተን አዳኟን ከእስራቷ አርነትን ትሰጣት ዘንድ ፍጹም እንደምትፈልግህ ታውቃለህና ፊትህን ከእኔ አታዙር።
አቤቱ መራቤን ታጠግብ ዘንድ መጠማቴንም ታረካ ዘንድ ጸጋህን ወደኔ ላክ፥ ባንተ ያለች መረጋጋትን ፍጹም እሻለሁና።
አቤቱ ጌታዬ ሆይ አንተን የሚወድ እውነትህንም የተጠማ ከቶ መች ጠግቦ ይጠግብሃል? አቤቱ ብርሃንን የምትሰጥ ሆይ ልመናዬን ስማ፥ እንደጸሎቴ ጸጋህን ስጠኝ፥ የፍቅርህ ነበልባል በልቤ ይነድ ዘንድ ከጸጋህ አንዲት ጠብታን በልቤ አኑር። እሳት እሾህና ኮሸሽላን እንደሚያነድ እንዲሁ በልቤ ያለውን ክፉ ሐሳብ የጸጋህ እሳት አቃጥሎ ያጥፋልኝ።
አቤቱ የለመንኩህን ሁሉ አትረፍርፈህ ስጠኝ፥ አምላኬ ነህና ለእኔ ለፍጥረትህ፣ ንጉሴም ነህና ለእኔ ለባርያህ ጸጋህን ፍቀድልኝ። እንደ ቸር አባትነትህም አብዝተህ በጸጋህ ባርከኝ።
ማር ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
የሰውን የልቡን ሐሳብ ውስጡንም የምትመረምር ላንተ አቤቱ እኔ ምን እላለሁ? አንተ ነፍሴ ውሃን እንዳጣ ምድረ በዳ አንተን እንደተጠማች ልቤም አንተን እንደምትሻ ታውቃለህ። የአንተ ጸጋ የሚወዱህን ሁል ጊዜ ታድናለች፡፡
ሁልጊዜ ትሰማኛለህና አቤቱ አሁን ከጸሎቴ ፊትህን አታዙር። ልቡናዬ አንተን አዳኟን ከእስራቷ አርነትን ትሰጣት ዘንድ ፍጹም እንደምትፈልግህ ታውቃለህና ፊትህን ከእኔ አታዙር።
አቤቱ መራቤን ታጠግብ ዘንድ መጠማቴንም ታረካ ዘንድ ጸጋህን ወደኔ ላክ፥ ባንተ ያለች መረጋጋትን ፍጹም እሻለሁና።
አቤቱ ጌታዬ ሆይ አንተን የሚወድ እውነትህንም የተጠማ ከቶ መች ጠግቦ ይጠግብሃል? አቤቱ ብርሃንን የምትሰጥ ሆይ ልመናዬን ስማ፥ እንደጸሎቴ ጸጋህን ስጠኝ፥ የፍቅርህ ነበልባል በልቤ ይነድ ዘንድ ከጸጋህ አንዲት ጠብታን በልቤ አኑር። እሳት እሾህና ኮሸሽላን እንደሚያነድ እንዲሁ በልቤ ያለውን ክፉ ሐሳብ የጸጋህ እሳት አቃጥሎ ያጥፋልኝ።
አቤቱ የለመንኩህን ሁሉ አትረፍርፈህ ስጠኝ፥ አምላኬ ነህና ለእኔ ለፍጥረትህ፣ ንጉሴም ነህና ለእኔ ለባርያህ ጸጋህን ፍቀድልኝ። እንደ ቸር አባትነትህም አብዝተህ በጸጋህ ባርከኝ።
ማር ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
ጥሩ ነገር ከሆነልህ እግዚአብሔርን አመስግን፥ ያን ጥሩ ነገር ያጸናልሃል፤ መጥፎ ነገር ከሆነብህም እግዚአብሔርን አመስግን፥ ያን ክፉ ነገር ለመልካም ያደርግልሃል፤ ስለ ሁሉም ነገር ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን!
— ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
— ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Forwarded from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
ማኅበራዊ ሚድያን እንደ ቋሚ ዕውቀት መጠቀም ብዙ በሽታዎችን ወደ ውስጣችን ማስተጋባት ነው።
ለአእምሯችን እድገት ሊሆኑ የሚችሉ መጻሕፍትን በማንበብ ግን ከደዌው መላቀቅ ይቻላል።
ፍጡራዊ ሰው ሙሉ የሚሆነው በትምህርት እና በንባብ ነው።
ከትምህርት እና ከንባብ የተገታ ሰው ግን የወሬ ጋን ነው የሚሆነው።
ማህበራዊ ሚድያ ሀሳብን ለመሸጥ መረጃን ለማየት ነው እንጂ ቋሚ የዕውቀት ቦታ አይደለም።
በረጂም አንቀጽ የተጻፉትን ለማየት ዓይኑን የሚያመው አፉን የሚያዛጋው ሰው በወሬ ሱስ የተሞላ ስለሆነ ነው።
ይሄ ደዌ ደግሞ በደንብ ተንፍሶ መፈወስ የሚችለው በመጻሕፍት ምርመራ ነው።
ለአእምሯችን እድገት ሊሆኑ የሚችሉ መጻሕፍትን በማንበብ ግን ከደዌው መላቀቅ ይቻላል።
ፍጡራዊ ሰው ሙሉ የሚሆነው በትምህርት እና በንባብ ነው።
ከትምህርት እና ከንባብ የተገታ ሰው ግን የወሬ ጋን ነው የሚሆነው።
ማህበራዊ ሚድያ ሀሳብን ለመሸጥ መረጃን ለማየት ነው እንጂ ቋሚ የዕውቀት ቦታ አይደለም።
በረጂም አንቀጽ የተጻፉትን ለማየት ዓይኑን የሚያመው አፉን የሚያዛጋው ሰው በወሬ ሱስ የተሞላ ስለሆነ ነው።
ይሄ ደዌ ደግሞ በደንብ ተንፍሶ መፈወስ የሚችለው በመጻሕፍት ምርመራ ነው።
Forwarded from የግቢ ጉባኤያት ምሩቃን ዓለም አቀፍ ኅብረት
ጭንቀት ምንድነው?
ክፍል አንድ
ጭንቀት ከአስጨናቂ ነገሮች የሚመነጭና የሚመጣ፣ የልቦናን በር ሰብሮ፣ የኅሊናን መስኮት ሰርስሮ፣ የሒሳብን መስመር ተቆጣጥሮ፣ አጥንትን ቦርቡሮ በመግባት የደም ዝውውርን አስጨንቆና አፍኖ በመያዝ ለአደጋ ሊያጋልጥ የሚችል ነው፡፡ በአንድ ነገር ላይ ትኩረት በማድረግ ደግሞ መውጫ ቀዳዳ የሌለው አስመስሎና አግዝፎ በማሰብ ኅሊናን የሚያስጨንቅ ነው። በዚህም መሠረት ሥጋዊና መንፈሳዊ ጭንቀቶች ይኖራሉ።
፩ኛ. ሥጋዊ ጭንቀት፦ የተለያዩ ነገሮች በማሰብ በማውጣትና በማውረድ፣ በማሰላሰል መጨነቅ፣ መጠበብ፣ መሠቃየት፣ መቸገር፣ “እንዴት እሆናለው” ማለት ነው፡፡ ከልብ የሚመነጭ፣ በኅሊና የሚወጣና የሚወርድ፣ በረቂቁ አእምሯችን የሚመላስ፣ በኅሊና ቦይ የሚፈስ ሲሆንም ለጉዳት ያጋልጣል።
ጭንቀት ክብደቱና ቅለቱ ይለይ እንጂ በሁሉም ሰው ላይ የሚታይና የሚገለጽ በመሆኑ የጭንቀት መጠን ከሚገባው በላይ እየጨመረ ከሄደ ሰውነትን የሚያዛባ፣ አእምሮን የሚያቃውስ፣ ኅሊና የሚያቃውስ፣ ከቤተ ሰብ፣ ከትዳር፣ ከጓደኛ፣ ከጎረቤት እንዲሁም ከማኅበራዊ ኑሮ የሚለይ እና በብቸኝነት መኖርን የሚያላምድ አደገኛ ነገር ነው።
ታዲያ ይህ ጭንቀት በተከታታይ ለሳምንታትም ሆነ ለወራት፣ ያለማቋረጥ ከፍ ባለ ቁጥር ውስጣችን በኀዘን እንዲዝል፣ ስሜታችን ዝቅ እንዲል፣ ለነገሮች ፍላጎት እንዳይኖረን፣ የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን፣ በሕይወታችን ምንም የደስታ ስሜት እንዳይኖረን፣ ነገሮችን አስበን እንዳናከናውን፣ ራሳችንን እንድንጠላ፣ በትንሿ ነገር እንድንበሳጭና በራሳችን እንዳንተማመን በማድረግ ተስፋ እስከ መቁረጥ ሊያደርስ ይችላል።
የጭንቀት መንሥኤዎች ፦
* የጤና ችግር
* የቤተ ሰብ ሞት
* ሥራ ማጣት
* ከቤተ ሰብ መለየት
* ትዳር አለመያዝ
* ልጅ አለመውለድ
* የሀገር ሰላም መደፍረስ
* ገደብ የሌለው ፍላጎት ተጠቃሽ ናቸው።
ለሰው ልጅ ሦስት መሠረታዊ ነገሮች (ምግብ፣ ልብስና መጠለያ) የሚያስፈልጉት ቢሆንም እነዚህ ነገሮች ቢሟሉም ርካታ የማግኘት ዕድሉ በመሆኑ “ለእናንተ ሰማያዊ አባታቹ ይህን ሁሉ እንድትሹ ያውቃል” ተብሎ እንደተጻፈው (ማቴ.፮፥፴፪) ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ በአርያውና በአምሳሉ የፈጠረው አምላክ እንደማይነሣ የታመነ መሆኑን ማወቅ ግን ተገቢ ነው።
፪ኛ መንፈሳዊ ጭንቀት፦ ይህ ስለ መንፈሳዊውና ዘለዓለማዊው ሕይወት መጨነቅና ማሰብ ነው። በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰው ከሞት በኋላ ሕይወት፣ ከመቃብር በኋላ ትንሣኤ ያለው ሲሆን ኅልፈት በሌለበት መንግሥተ ሰማያት ከቅዱሳን መላእክት ጋር “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ” እያለ እያመሰገነ ይኖራል። ታዲያ የሰው ልጅ ይህንን የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ ፍቅር እያሰበ፣ እርሱን ደስ የሚያሰኝበትን መልካም ሥራ እየሠራ፣ በኋላ ጌታ ለፍርድ ሲመጣ በቀኙ ለመቆምና ክብሩን ለመውረስ መንፈሳዊ ጭንቀት ሊጨነቅ ይገባል።
“ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ፣ ነፍሱንም ቢያጣ፣ ለሰው ምን ይረባዋል? ሰውስ ለነፍሱ ቤዛ ምን በሰጠ ነበር?” እንዲል፡፡ (ማቴ.፲፮፥፳፮) ሰው አብዝቶ መጨነቅ ያለበት በነፍሱ እንዳይጎዳና ከእግዚአብሔር እንዳይለይ በመሆኑ ሰይጣን የሚያመጣብንን ልዩ ልዩ መከራ በትዕግሥት በመቀበል በሃይማኖት ጸንቶ፣ በመንፈሳዊ ምግባር በርትቶ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት ተግቶ ውጣ ውረድ የበዛበትንን ዓለም ለማሸነፍ ልንጨነቅ ይገባል።
መንፈሳዊ ጭንቀቶች የሚባሉት፦
እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት መጨነቅ
ሕጉን በመጠበቅ
ንስሓ መግባት
መንግሥቱን መውረስ
ይቆየን !
ክፍል አንድ
ጭንቀት ከአስጨናቂ ነገሮች የሚመነጭና የሚመጣ፣ የልቦናን በር ሰብሮ፣ የኅሊናን መስኮት ሰርስሮ፣ የሒሳብን መስመር ተቆጣጥሮ፣ አጥንትን ቦርቡሮ በመግባት የደም ዝውውርን አስጨንቆና አፍኖ በመያዝ ለአደጋ ሊያጋልጥ የሚችል ነው፡፡ በአንድ ነገር ላይ ትኩረት በማድረግ ደግሞ መውጫ ቀዳዳ የሌለው አስመስሎና አግዝፎ በማሰብ ኅሊናን የሚያስጨንቅ ነው። በዚህም መሠረት ሥጋዊና መንፈሳዊ ጭንቀቶች ይኖራሉ።
፩ኛ. ሥጋዊ ጭንቀት፦ የተለያዩ ነገሮች በማሰብ በማውጣትና በማውረድ፣ በማሰላሰል መጨነቅ፣ መጠበብ፣ መሠቃየት፣ መቸገር፣ “እንዴት እሆናለው” ማለት ነው፡፡ ከልብ የሚመነጭ፣ በኅሊና የሚወጣና የሚወርድ፣ በረቂቁ አእምሯችን የሚመላስ፣ በኅሊና ቦይ የሚፈስ ሲሆንም ለጉዳት ያጋልጣል።
ጭንቀት ክብደቱና ቅለቱ ይለይ እንጂ በሁሉም ሰው ላይ የሚታይና የሚገለጽ በመሆኑ የጭንቀት መጠን ከሚገባው በላይ እየጨመረ ከሄደ ሰውነትን የሚያዛባ፣ አእምሮን የሚያቃውስ፣ ኅሊና የሚያቃውስ፣ ከቤተ ሰብ፣ ከትዳር፣ ከጓደኛ፣ ከጎረቤት እንዲሁም ከማኅበራዊ ኑሮ የሚለይ እና በብቸኝነት መኖርን የሚያላምድ አደገኛ ነገር ነው።
ታዲያ ይህ ጭንቀት በተከታታይ ለሳምንታትም ሆነ ለወራት፣ ያለማቋረጥ ከፍ ባለ ቁጥር ውስጣችን በኀዘን እንዲዝል፣ ስሜታችን ዝቅ እንዲል፣ ለነገሮች ፍላጎት እንዳይኖረን፣ የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን፣ በሕይወታችን ምንም የደስታ ስሜት እንዳይኖረን፣ ነገሮችን አስበን እንዳናከናውን፣ ራሳችንን እንድንጠላ፣ በትንሿ ነገር እንድንበሳጭና በራሳችን እንዳንተማመን በማድረግ ተስፋ እስከ መቁረጥ ሊያደርስ ይችላል።
የጭንቀት መንሥኤዎች ፦
* የጤና ችግር
* የቤተ ሰብ ሞት
* ሥራ ማጣት
* ከቤተ ሰብ መለየት
* ትዳር አለመያዝ
* ልጅ አለመውለድ
* የሀገር ሰላም መደፍረስ
* ገደብ የሌለው ፍላጎት ተጠቃሽ ናቸው።
ለሰው ልጅ ሦስት መሠረታዊ ነገሮች (ምግብ፣ ልብስና መጠለያ) የሚያስፈልጉት ቢሆንም እነዚህ ነገሮች ቢሟሉም ርካታ የማግኘት ዕድሉ በመሆኑ “ለእናንተ ሰማያዊ አባታቹ ይህን ሁሉ እንድትሹ ያውቃል” ተብሎ እንደተጻፈው (ማቴ.፮፥፴፪) ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ በአርያውና በአምሳሉ የፈጠረው አምላክ እንደማይነሣ የታመነ መሆኑን ማወቅ ግን ተገቢ ነው።
፪ኛ መንፈሳዊ ጭንቀት፦ ይህ ስለ መንፈሳዊውና ዘለዓለማዊው ሕይወት መጨነቅና ማሰብ ነው። በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰው ከሞት በኋላ ሕይወት፣ ከመቃብር በኋላ ትንሣኤ ያለው ሲሆን ኅልፈት በሌለበት መንግሥተ ሰማያት ከቅዱሳን መላእክት ጋር “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ” እያለ እያመሰገነ ይኖራል። ታዲያ የሰው ልጅ ይህንን የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ ፍቅር እያሰበ፣ እርሱን ደስ የሚያሰኝበትን መልካም ሥራ እየሠራ፣ በኋላ ጌታ ለፍርድ ሲመጣ በቀኙ ለመቆምና ክብሩን ለመውረስ መንፈሳዊ ጭንቀት ሊጨነቅ ይገባል።
“ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ፣ ነፍሱንም ቢያጣ፣ ለሰው ምን ይረባዋል? ሰውስ ለነፍሱ ቤዛ ምን በሰጠ ነበር?” እንዲል፡፡ (ማቴ.፲፮፥፳፮) ሰው አብዝቶ መጨነቅ ያለበት በነፍሱ እንዳይጎዳና ከእግዚአብሔር እንዳይለይ በመሆኑ ሰይጣን የሚያመጣብንን ልዩ ልዩ መከራ በትዕግሥት በመቀበል በሃይማኖት ጸንቶ፣ በመንፈሳዊ ምግባር በርትቶ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት ተግቶ ውጣ ውረድ የበዛበትንን ዓለም ለማሸነፍ ልንጨነቅ ይገባል።
መንፈሳዊ ጭንቀቶች የሚባሉት፦
እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት መጨነቅ
ሕጉን በመጠበቅ
ንስሓ መግባት
መንግሥቱን መውረስ
ይቆየን !
ማረፍያ Tube
@marefiatube
ይህ ቻናል የተለያዩ ድንቅ እውነታዊ ታሪኮች እና ከተለያዩ መፅሐፍት አስተማሪ የሆኑ ርዕሶች በማንሳት እንዲሁም ከደጋግ አንደበቶች የወጡ እውቀት መንፈሳዊ እና እውቀት ስጋዊን የምያስጨብጥ እና የምያስተምር ነው።
ሰብስክርያብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ😊
https://youtube.com/channel/UCKYptOUbNTlr1JLLpofTHcw?si=Ghw3Q3hq0ZkYrPhQ
@marefiatube
ይህ ቻናል የተለያዩ ድንቅ እውነታዊ ታሪኮች እና ከተለያዩ መፅሐፍት አስተማሪ የሆኑ ርዕሶች በማንሳት እንዲሁም ከደጋግ አንደበቶች የወጡ እውቀት መንፈሳዊ እና እውቀት ስጋዊን የምያስጨብጥ እና የምያስተምር ነው።
ሰብስክርያብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ😊
https://youtube.com/channel/UCKYptOUbNTlr1JLLpofTHcw?si=Ghw3Q3hq0ZkYrPhQ
YouTube
ማረፍያ Tube
Welcome to **Marefia Tube**, a channel dedicated to bringing you thought-provoking ideas, fascinating facts, and diverse perspectives drawn from a wide range of texts and human experiences. Our mission is to create a space where truth and wisdom are shared…
"ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያምን እንዲህ አላት ' ባንቺ ያመነውን አድን ዘንድ የምሕረት ኪዳንን ካንቺ ጋር አደረኹ፡ በራሴም ማልኹልሽ። ለባርያዬ ለኖኅ ለወዳጄ ለአብርሃምም የማልኹ እኔ፤ የታመነ እንደልቤም ለሚሆን ለመረጥኹት ለዳዊት የማልኹ እኔ፤ በቅዱስ ሥጋዬ በክቡር ደሜም መሐላየን አላፈርስ ዘንድ በራሴ ማልኩልሽ'"
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ፤ ዝማሬ ዘኪዳነ ምሕረት)
"ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምዕመን ዘከመ ልብየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይኄሱ ማእኰትየ"
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ፤ ዝማሬ ዘኪዳነ ምሕረት)
* እንኳን አደረሰን!
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ፤ ዝማሬ ዘኪዳነ ምሕረት)
"ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምዕመን ዘከመ ልብየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይኄሱ ማእኰትየ"
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ፤ ዝማሬ ዘኪዳነ ምሕረት)
* እንኳን አደረሰን!
Forwarded from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
ዘወረደ ዕምላዕሉ፦
[፦ወረደ ለማለት በቅድምና ነበረ ማለት ይቀድማል።
[፦ ተፀነሰ ለማትም በነቢያት አድሮ ትንቢት አናገረ ማለት ይቀድማል።
[፦ተወለደ ለማለትም ተፀነሰ ማለት ይቀድማል።
[፦ ወንጌልን ዙሮ አስተማረ ለማለትም ተወለደ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ ማለት ይቀድማል።
[፦ተሰቀለ ለማለትም ሰው ሁኖ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን ዙሮ አስተማረ ማለት ይቀድማል።
[፦ተነሣ ለማለትም ተቀበረ ማለት ይቀድማል።
[፦ዓረገ ለማለትም ፵ ቀን ሐዋርያትን ለማስተማር ተመላለሰ ማለት ይቀድማል።
[፦ዳግም ይመጣል ለማለትም ወደ ሰማያት ዓረገ ማለት ይቀድማል።
ከዘወረደ የሚቀድመው በቅድምና ነበረ ማለት ነው።
መነሻ ከሌለው ህላዌው ተነስቶ መረዳት ጥሩ ነው።
ዘወረደ ብሎ ጾሙ መጀመሩ ግን ፵ መዓልት ፵ ሌሊት ጾመ ከማለት ወረደ ተወለደ ማለት ስለሚቀድም ነው።
[፦ወረደ ለማለት በቅድምና ነበረ ማለት ይቀድማል።
[፦ ተፀነሰ ለማትም በነቢያት አድሮ ትንቢት አናገረ ማለት ይቀድማል።
[፦ተወለደ ለማለትም ተፀነሰ ማለት ይቀድማል።
[፦ ወንጌልን ዙሮ አስተማረ ለማለትም ተወለደ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ ማለት ይቀድማል።
[፦ተሰቀለ ለማለትም ሰው ሁኖ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን ዙሮ አስተማረ ማለት ይቀድማል።
[፦ተነሣ ለማለትም ተቀበረ ማለት ይቀድማል።
[፦ዓረገ ለማለትም ፵ ቀን ሐዋርያትን ለማስተማር ተመላለሰ ማለት ይቀድማል።
[፦ዳግም ይመጣል ለማለትም ወደ ሰማያት ዓረገ ማለት ይቀድማል።
ከዘወረደ የሚቀድመው በቅድምና ነበረ ማለት ነው።
መነሻ ከሌለው ህላዌው ተነስቶ መረዳት ጥሩ ነው።
ዘወረደ ብሎ ጾሙ መጀመሩ ግን ፵ መዓልት ፵ ሌሊት ጾመ ከማለት ወረደ ተወለደ ማለት ስለሚቀድም ነው።
ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
Photo
በቤተክርስቲያን የአገልግሎት ሰዓት አገልጋዮች የእጅ ስልካቸውን ይዘው እንዳይገቡ ተከለከለ፡፡
(MK TV የካቲት 19/2017 ዓ.ም)
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እንዳስታወቀው በቤተክርስቲያን የአገልግሎት ሰዓት አገልጋዮች የእጅ ስልካቸውን ይዘው እንዳይገቡ ተከልክሏል ብሏል፡፡
የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ መከናነው በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ጸሐፍትና ሰባክያነ ወንጌልና ቄሰ ገበዞች ጋር ውይይት በተካሄደበት ወቅት የተለያዩ መመሪያዎች ተላልፈዋል።
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ጊዜ የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ከተላለፈው መመሪያዎች ውስጥ አንድ ነው፡፡
በዚህም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም በረከትን ከሚያሳጡ እንዲሁም ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ ተከልክሏል ተብሏል፡፡
መመሪያው ለየገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ ተእዛዝ ተላልፏል፡፡
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ማኅበራዊ የሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ
ፌስቡክ:- https://www.facebook.com/eotcmkidusan
ዩትዩብ:- https://www.youtube.com/@EOTCMK
ቴሌ ግራም:- https://www.tgoop.com/+1fuTLjgAW882MjI8
ቲክቶክ:-https://www.tiktok.com/@eotcmktv?_t=8shN97IVQlp
(MK TV የካቲት 19/2017 ዓ.ም)
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እንዳስታወቀው በቤተክርስቲያን የአገልግሎት ሰዓት አገልጋዮች የእጅ ስልካቸውን ይዘው እንዳይገቡ ተከልክሏል ብሏል፡፡
የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ መከናነው በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ጸሐፍትና ሰባክያነ ወንጌልና ቄሰ ገበዞች ጋር ውይይት በተካሄደበት ወቅት የተለያዩ መመሪያዎች ተላልፈዋል።
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ጊዜ የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ከተላለፈው መመሪያዎች ውስጥ አንድ ነው፡፡
በዚህም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም በረከትን ከሚያሳጡ እንዲሁም ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ ተከልክሏል ተብሏል፡፡
መመሪያው ለየገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ ተእዛዝ ተላልፏል፡፡
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ማኅበራዊ የሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ
ፌስቡክ:- https://www.facebook.com/eotcmkidusan
ዩትዩብ:- https://www.youtube.com/@EOTCMK
ቴሌ ግራም:- https://www.tgoop.com/+1fuTLjgAW882MjI8
ቲክቶክ:-https://www.tiktok.com/@eotcmktv?_t=8shN97IVQlp
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
"ፈተናዎች [ሕማማት] አንዳንድ ሰዎችን ከቀደሙ ኀጢአቶቻቸው ለማንጻት ይመጣሉ። ለአንዳንዶች ደግሞ አሁን ያገኙትን ፍጽምና (የበለጠ) ለማስዋብ ይመጣሉ። ለሌሎች ደግሞ ወደፊት ለሚገጥሟቸው ነገሮች ቀድሞ ለማዘጋጀት የሚመጡም አሉ። እንደ ኢዮብም፤ ሰው እምነትና ምግባርን እንዲጨምር የሚመጡም አሉ"
መክሲሞስ ተአማኒ
መክሲሞስ ተአማኒ
"ደመና ሳይኖር ዝናብ ሊዘንብ እንደማይችል ሁሉ በጎ ኅሊና ሳይኖረን እግዚአብሔርን ማስደሰት አንችልም።"
(ቅዱስ ማርቆስ መናኙ - 5ኛ ክ/ዘመን)
(ቅዱስ ማርቆስ መናኙ - 5ኛ ክ/ዘመን)
ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን የአበውን ልብ ገንዘብ ማድረግ ይገባናል፡፡ ይህም ማለት ሐሳባቸውን ማሰብ አለብን ማለት ነው፡፡ የእኛም ልብ ወደ አበው ልብ ይመለስ ዘንድ አስፈላጊ ነው፡፡ ከአበው የተለየ ልብ ክርስቶሳዊውን የእውነት አስተሳሰብ መቀበልና ማቀበል አይችልም፡፡ የሰው ሠራሽ ሥጋዊና ደማዊ አስተሳሰብ ማከማቻ ጎተራ ይሆናል እንጅ፡፡ በሀገር ታሪክ ብንመጣም ወደ አበው ልብ ብንመለስ ታሪክ ሠሪነትን፣ ታሪክ ጸሐፊነትን፣ ለሀገር፣ ለወገን መታመንን፣ እየታረዙ፣ እየተራቡና እየተጠሙ ቅርስ መጠበቅን፣ እየሞቱ ነጻነትን ማውረስን እናገኛለን፡፡ በክርስትናው ዓለም ውስጥ በአበው ልብ ውስጥ የክርስቶስን ልብ እናገኘዋለን፡፡ እንደ ክርስቶስ ሲያስቡ፣ ሲሠሩ . . . በሁሉ ነገር ሲመስሉት እናያለን፡፡ ወደ ዚያ ልብ መመለስ ይጠይቀናል፡፡ ከዚያ ልብ ስንለይ ከግንዱ የተለየ ቅርንጫፍ እንሆናለን፡፡ ከግንዱ የተለየ ቅርንጫፍ ይደርቃል፤ ለእሳት ይጣላል፡፡ ከክርስቶሳዊው የአበው ልብ መነጠልም እንዲሁ በኀጢአት መድረቅ ያመጣል፤ በሱታፌ መተባበርን ያሳጣል፡፡
" መጥቼም ምድርን በእርግማን እንዳልመታ እርሱ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች፥ የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ይመልሳል።" (ሚል 4፥6)
@ምሥራቀ ጸሐይ ጉባኤ ቤት
" መጥቼም ምድርን በእርግማን እንዳልመታ እርሱ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች፥ የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ይመልሳል።" (ሚል 4፥6)
@ምሥራቀ ጸሐይ ጉባኤ ቤት
Forwarded from ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
"የተባረከ ሰው ማለት የራሱን ድክመት የሚያውቅ ሰው ነው። ምክንያቱም ይሄ የእውቀቱ መሠረትና የሁሉም መልካም ነገሮች መጀመሪያ ይሆንለታልና፡፡"
ማር ይስሐቅ
ማር ይስሐቅ
“በዚያም ጊዜ ትምረን ይቅርም ትለን ዘንድ በበላነው ሥጋህ በጠጣነውም ደምህ ተማጽነናል አንተ ሥጋዬን ለበላ ደሜንም ለጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ብለሃልና ። ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማጽነናል ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት አንተ መታሰቢያሽን ያደረገ ስምሽንም የጠራ የዘላለም ድኅነትነ ይድናል ብለሃታል”
ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ