የይሁዳ መሳም ውጤቱ ጌታን አሳልፎ መስጠት ነው። የለንጊኖስ መውጋት ውጤቱ ልጅነት የምናገኝበትን ማየ ገቦ ማስገኘት ነው። እንዲህ ከሆነ ከይሁዳ ሰላምታ የለንጊኖስ መውጋት ይሻላል።
ማርያም ጽዮን ታቦተ ቃለ ጽድቅ መንፈቀ ዕሥራ፣ ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ፣ አፍቀርኩኪ አፍቅርኒ እምይእዜ ለግሙራ
➥|እውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል (ዐሠርቱ ቃላት) የተጻፉብሽ የሙሴ ታቦት (ጽላት) ነሽ፡፡ (ጊደሮች) ርግቦች ከልጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደወደዱ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ፈጽሜ አፈቅርሻለሁና ረድኤትሽ አይለየኝ፡፡
➥|እውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል (ዐሠርቱ ቃላት) የተጻፉብሽ የሙሴ ታቦት (ጽላት) ነሽ፡፡ (ጊደሮች) ርግቦች ከልጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደወደዱ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ፈጽሜ አፈቅርሻለሁና ረድኤትሽ አይለየኝ፡፡
ባዘንኩም በተቆረቆርሁ ጊዜ የኃዘኔ መፅናኛ ነሽ። ባለቀስኩም ጊዜ የለቅሶዬ መተዊያ ነሽ። በዘመርሁ ጊዜ ለእጄ እንደ መሰንቆ ለጣቶቼም እንደበገና ነሽ። በተራብሁ ጊዜ ለሆዴ ትመግቢኛለሽ በተጠማሁ ጊዜ እኔን ለማርካት የሕይወት ውሃን የተመላሽ ነሽ። በተጨነቅሁ ጊዜ ጭንቀቴን ታርቂያለሽ። በቆሰልኩም ጊዜ ቁስሌን ታጠጊያለሽ። በበደልኩም ጊዜ ኃጢያቴን ታቀልያለሽ። በርኩሰቴም ጊዜ ንጹሕ ታደርጊኛለሽ። የደኸየሁም ጊዜ ለድህነቴ ባለጸግነት ሀብቴ ነሽ።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
“ጸቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍርኪ፤ ሀሊበ ወመዓር እምታሕተ ልሳንኪ፤ወይቤላ ንዒ ንሑር ኀበ ደብረ ከርቤ ውስተ አውግረ ስሂን"
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን አደረሳችሁ
በዓታ ለማርያም
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን አደረሳችሁ
በዓታ ለማርያም
“የክርስቶስ ፍቅር እንደምናውቀው እና እንደምንጠብቀው “እንደሆነው የሚቀበል(accept as who they are)” አይነት ሳይሆን የክርስቶስ ፍቅር ሰዎችን እንደሆኑት የሚቀበል እና ‘አዲስ፣ዋጋ የሚታጣለት፣ታላቅ’ አድርጎ የሚለውጥ ነው።”
አበምኔት አይሪኒ
አበምኔት አይሪኒ
"ድንግል ማርያም የሽቱ መኖሪያና የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት የማኅፀንዋ ፍሬ ሰውን ሁሉ አድንዋልና። ከእኛም እርግማንን አጠፋልን። "
ቅዱስ ኤፍሬም
ቅዱስ ኤፍሬም
“በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰዉ ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፣ ስለተገለጠልን ምስጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋህዷልና ቅድምና የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት”
ቅዱስ ኤፍሬም
ቅዱስ ኤፍሬም
"ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤
እርሱም እናቱን ፈጠረ፤
የፈጠረውንም ሥጋ መልሶ ተዋሐደው።"
ቅዱስ ኤፍሬም
እርሱም እናቱን ፈጠረ፤
የፈጠረውንም ሥጋ መልሶ ተዋሐደው።"
ቅዱስ ኤፍሬም
"በቀዳማዊት ሔዋን አለመታዘዝ ምክንያት ሞት በሰው ላይ ሰለጠነ፤ በዳግማዊት ሔዋን (ድንግል ማርያም) መታዘዝ ምክንያት ሕይወት ወደ ዓለም መጣ፡፡ ሞት ኃይሉን አጣ፡፡"
ቅዱስ ሄሬንዮስ
ቅዱስ ሄሬንዮስ
ከአብ የተወለደ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ በመለኮቱ መዋረድ ሳይኖርበት በፈቃዱ ተዋርዶ የተገዥ ባሕርይን ተዋሐደ።
ሰው ሆይ ሥጋ ያልነበረው እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው ሆይ በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ፤ በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ።
አይታይ የነበረው የሚታይ ሥጋን ተዋሐደ፤ የማይለወጥ እርሱ በሚለወጥ ሥጋ ተዳሠሠ፤ የማይለወጥም አደረገው።
ባዕል እርሱ ከሌዊ ወገን በተወለደች በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ።
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አጢፎስ
ምዕራፍ ፰
👉 @behlateabew 👈
ሰው ሆይ ሥጋ ያልነበረው እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው ሆይ በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ፤ በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ።
አይታይ የነበረው የሚታይ ሥጋን ተዋሐደ፤ የማይለወጥ እርሱ በሚለወጥ ሥጋ ተዳሠሠ፤ የማይለወጥም አደረገው።
ባዕል እርሱ ከሌዊ ወገን በተወለደች በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ።
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አጢፎስ
ምዕራፍ ፰
👉 @behlateabew 👈