“ጸቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍርኪ፤ ሀሊበ ወመዓር እምታሕተ ልሳንኪ፤ወይቤላ ንዒ ንሑር ኀበ ደብረ ከርቤ ውስተ አውግረ ስሂን"
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን አደረሳችሁ
በዓታ ለማርያም
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን አደረሳችሁ
በዓታ ለማርያም
“የክርስቶስ ፍቅር እንደምናውቀው እና እንደምንጠብቀው “እንደሆነው የሚቀበል(accept as who they are)” አይነት ሳይሆን የክርስቶስ ፍቅር ሰዎችን እንደሆኑት የሚቀበል እና ‘አዲስ፣ዋጋ የሚታጣለት፣ታላቅ’ አድርጎ የሚለውጥ ነው።”
አበምኔት አይሪኒ
አበምኔት አይሪኒ
"ድንግል ማርያም የሽቱ መኖሪያና የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት የማኅፀንዋ ፍሬ ሰውን ሁሉ አድንዋልና። ከእኛም እርግማንን አጠፋልን። "
ቅዱስ ኤፍሬም
ቅዱስ ኤፍሬም
“በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰዉ ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፣ ስለተገለጠልን ምስጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋህዷልና ቅድምና የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት”
ቅዱስ ኤፍሬም
ቅዱስ ኤፍሬም
"ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤
እርሱም እናቱን ፈጠረ፤
የፈጠረውንም ሥጋ መልሶ ተዋሐደው።"
ቅዱስ ኤፍሬም
እርሱም እናቱን ፈጠረ፤
የፈጠረውንም ሥጋ መልሶ ተዋሐደው።"
ቅዱስ ኤፍሬም
"በቀዳማዊት ሔዋን አለመታዘዝ ምክንያት ሞት በሰው ላይ ሰለጠነ፤ በዳግማዊት ሔዋን (ድንግል ማርያም) መታዘዝ ምክንያት ሕይወት ወደ ዓለም መጣ፡፡ ሞት ኃይሉን አጣ፡፡"
ቅዱስ ሄሬንዮስ
ቅዱስ ሄሬንዮስ
ከአብ የተወለደ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ በመለኮቱ መዋረድ ሳይኖርበት በፈቃዱ ተዋርዶ የተገዥ ባሕርይን ተዋሐደ።
ሰው ሆይ ሥጋ ያልነበረው እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው ሆይ በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ፤ በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ።
አይታይ የነበረው የሚታይ ሥጋን ተዋሐደ፤ የማይለወጥ እርሱ በሚለወጥ ሥጋ ተዳሠሠ፤ የማይለወጥም አደረገው።
ባዕል እርሱ ከሌዊ ወገን በተወለደች በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ።
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አጢፎስ
ምዕራፍ ፰
👉 @behlateabew 👈
ሰው ሆይ ሥጋ ያልነበረው እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው ሆይ በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ፤ በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ።
አይታይ የነበረው የሚታይ ሥጋን ተዋሐደ፤ የማይለወጥ እርሱ በሚለወጥ ሥጋ ተዳሠሠ፤ የማይለወጥም አደረገው።
ባዕል እርሱ ከሌዊ ወገን በተወለደች በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ።
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አጢፎስ
ምዕራፍ ፰
👉 @behlateabew 👈
"ለመወለዱ ጥንት በሌለዉ አስቀድሞ ዓለም ሳይፈጠር በመለኮቱ ከአብ በተወለደ ዳግመኛም እኛን ለማዳን ቡሃላ ዘመን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በእግዚአብሔር ልጅ እናምናለን ።የቀኑ ቀጠሮ ሲደርስ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከድንግልም ተወለደ።"
ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
እሰይ ነጋ!ቀኑን ሙሉ ክፋትን በመስራት አንተን ስናሳዝን እንዳንውል ጠብቀን::
ከራሳችን ጠብቀን
ከክፉ ሐሳቦቻችን ጠብቀን
ከጠላት ወጥመድ ጠብቀን
እረኛችን ሆይ ጠብቀን
መልካም ቀን
ከራሳችን ጠብቀን
ከክፉ ሐሳቦቻችን ጠብቀን
ከጠላት ወጥመድ ጠብቀን
እረኛችን ሆይ ጠብቀን
መልካም ቀን
ጌታችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወደው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ በሁለት ወገን ድንግል ከምትሆን ከቅድስት ማርያም መወለዱንም የማያምን ሰው ሁሉ እንግዳ እስከሚሆን ምጽአቱ ድርስ ጳውሎስ እንደ ተናገረ የተለየ ይሁን፡፡
ሥርዓተ ቅዳሴ
@behlateabew
ሥርዓተ ቅዳሴ
@behlateabew