BEMALEDANEK Telegram 2372
    "ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።"

                                      (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5፥19
)

አትብሉ የሚል ትእዛዝ ያሰመረው እግዚአብሔር፤ መስመሩ ተጥሶበታል፡፡ አዳም ሕግ በማፍረስ በደል ፈጽሞአል፡፡ ስለዛ ካሳ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ ለንጉሥ እግዚአብሔር የሚሆን እጅ መንሻ መስጠት ይገባዋል፡፡ ሆኖም ይህንን አምኃ ችሎ ሊከፍል አልተቻለውም፡፡ ሞትን የሚክስ ሕይወት፣ ውድቀትን የሚሽር ትንሣኤ፣ የተዘጋውን ማኅተም የሚከፍት ቁልፍ ከፍጥረት ዘንድ አልተገኘም፡፡ ዮሐንስ ፦

     "በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም። መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ። "ከሽማግሌዎቹም አንዱ። አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ።"

                                             (የዮሐንስ ራእይ 5፥3-5)

አበው በሰባት ማኅተሞች የተዘጋው መጽሐፍ አንድም ሰው ((ሰ)ብእ-(ሰ)ባት) ነው ይላሉ፡፡ ከነዚህ ማኅተሞች አንዱ ሞት ነው፡፡ "አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ" የሚለውን ድምፅ ያደመጠ ባሕሪያችን ሞትን መሻገር ቢፈልግም አልሆነለትም፡፡ አለመሞት የሚባለውን ገጽ ሊዘረጋና ገልጦ ሊያነበው ማንም አልቻለም፡፡

ይህንን ያወቀቺው የባለ ራእዩ ነፍስ፤ ስለ ሁሉ የሰው ልጅ ሕይወት ተወክላ ስለተዘጉባት ማኅተሞችና ሊከፈቱም ስላለመቻላቸው አስባ አምርራ አለቀሰች፡፡ በዚህን ጊዜ አንድ የሚያጽናና ድምፅ "ከይሁዳ ወገን የሆነ አንበሳ እርሱም የዳዊት ልጅ" የተባለ ማኅተሞቹን ሊተረትራቸውና መጽሐፉን ሊገልጠው እንደቻለ ተናገረ፡፡ ይሄ ድል ነሺ መድኃኒቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!

ለእጅ መንሻ የሚቀርብ ንጹሕ በግ፣ እጅ መንሻውን የሚያቀርብ ሊቀ ካህን፣ እጅ መንሻውን የሚቀበል ንጉሥ ራሱ ሆኖ፤ መድኃኒቱ በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ እንከፍለው ዘንድ የሚገባውን ዕዳ በእኛ ቦታ ሆኖ ከፈለልን፡፡ ሞት የማይገባውን ሥጋውን ለሞት አሳልፎ በመስጠት፣ መፍሰስ የሌለበት ቅዱስ ደሙን ስለ ኃጢአታችን ቤዛ በማፍሰስ፤ ለመተላለፋችን ካሳ የሚሆን ንጹሕ አምኃን ሰጠ፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ሥጋና ደሙን ቅዱስ ቁርባን እየተባለ እንዲጠራ ያደረገው ቀዳሚ ምክንያት፡፡

ሌላውና ዋነኛው ደግሞ ቁርባን በግእዙ አቻ ፍቺ መቀራረቢያ፣ መገናኛ ማለት ነው ተባብለናል፡፡ ይህም ትርጉም እንዲሁ ለመድኃኒቱ ሥጋና ደም የሚስማማ ነው፡፡ በወደፊት ክፍሎች ላይ በሰፊው ስለምንመለስበት ለመግቢያ ያህል በሚሆን እናብራራው፡፡

ባሳለፍነው የንስሐ ምዕራፍ ላይ ከአምላክ ፈቃድ ከተለየን በኋላ ፊታችን ወደ ዓለም ጀርባችን ወደ እግዚአብሔር ዞሮ እንደምንኖር አይተናል፡፡ ይሄን በሌላ አገላለጽ ከእግዚአብሔር ርቀን ለዲያቢሎስ ቀርበን በምድር መመላለስ ጀመርን ልንለው እንችላለን፡፡

በዚህ አኗኗር ውስጥ ሳለን፤ ዘመን ምሕረትን ባመጣልን የመዳን ጊዜ ላይ "አማኑኤል" በተባለ ስሙ ከእኛ ጋር ሊሆን ያፈቀረ ክርስቶስ፤ መለኮት የተዋሐደውን ሥጋና ደሙን ለእኛ በመስጠት ከእግዚአብሔር ለያይቶን የነበረውን የመራራቅ ግድግዳ አፍርሶ አንድነትን አምጥቶአል፡፡

    "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ (አንድነት!)።"

                                                 (የዮሐንስ ወንጌል 6፥56)


እግዚአብሔር በእኛ ከሚኖርበት እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር ከምንኖርበት ክሂል ወጥተን ለዘላለሙ እንዳንጠፋ፤ መድኃኒቱ ሥጋውን መብል ደሙን መጠጥ በማድረግ ራሱን በውስጣችን እኛን ደግሞ በውስጡ በማኖር፤ ከራሱ ጋር አቀራረበን፣ አገናኘን፡፡ ይህን የእውነት መሠረት ስናውቅም፤ የጌታችን ሥጋውና ደሙ ቁርባን መባሉ ትክክለኛ ሃይማኖታዊ አተረጓገም ስለመሆኑ ግንዛቤ እንወስዳለን፡፡

ሦስተኛ ቁርባን ማለት መሥዋዕት ማለት እንደሆነ አይተናል፡፡ በተስፋና በቃል ስለ እግዚአብሔር ልጅ መወለድ ሲናገር የቆየው ብሉዩ ዘመን፤ ቁርባንን በመሥዋዕትነቱ ሲገለገልበት ቆይቷል፡፡ በሐዲስ ኪዳኑ ጊዜ ላይ አማናዊ መሥዋዕት ሆኖ ስለሚቀርበው የክርስቶስ ሥጋና ደም ምሳሌ ያደረጉ፤ በትንቢትነት የተገለጡ፤ የተለያዩ የእንስሳትና የዕፅዋት መሥዋዕቶች ለእግዚአብሔር ሲቀርቡ ነበር፡፡ ለምሳሌ ያህል ፦

የልዑል እግዚአብሔር ካህንና የሳሌም ንጉሥ ያቀረበው የኅብስትና የወይን መሥዋዕት ለክርስቶስ ዘላለማዊ ሊቀ ካህናትነትና ለሥጋው ወደሙ ዓይነተኛ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል (ዘፍ 14፤18 ዕብ 5፣6 እና 10፣7፥17)። ሁለተኛ፤ ከቀሳፊ የሞት መልአክ አድኖ ከግብጽ ባርነት ነፃ ያወጣቸው የፋሲካ በግ ደም መረጨትና ሥጋውም ተጠብሶ መበላቱ የእግዚአብሔር በግ ለተባለው ለመድኃኒቱ አዳኝነትና ለምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ ሆኗል (ዘፀ 12፤1:51 1ኛ ቆሮ 4፣7)። ሦስተኛ፤ እሥራኤላውያን በምድረ በዳ ይመገቡት የነበረው ከሰማይ የወረደው መና ዛሬ ምእመናን ለነፍሳቸው ምግብ የሚቀበሉት የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ነው (ዘፀ 16፣16፥23 ዮሐ 6፣49፥51)። አራተኛ፤ ጥበብ ያዘጋጀችው ማዕድ፣ ያረደችው ፍሪዳ፣ የጠመቀችው የወይን ጠጅ፣ የላከቻቸው አገልጋዮቿ የተጠሩት ሰዎች ሁሉ ምሳሌነት እንዳላቸው ይነገራል። ጥበብ የክርስቶስ፣ ማዕድ የሥጋው የደሙ፣ አገልጋዮች የካህናት፣ ተጋባዦች የምእመናን ምሳሌ ናቸው ተብሎ ይተረጎማል (ምሳ 9፤1፥5)። ይህን የመሳሰሉ ሌሎች ምሳሌዎችም አሉ (ዘሌዋ 2፤ 23፣13፥14 ሲራክ 24፣19፥21)።

ለአካሉ ጥላ ሆኖ የነበረው ዘመን ሲያበቃ፤ የብሉይ ዓመታትን መሥዋዕት የሚጠቀልል አንድ የመሥዋዕት ሥርዓት በመድኃኒቱ አማካኝነት ከስቅለት ቀን በፊት በነበረው የመጨረሻው እራት በሚሰኘው ዕለተ ሐሙስ ላይ ተመሠረተ፡፡

   "ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።"

                                               (የማቴዎስ ወንጌል 26፥28)

ከጠፋንበት ፈልጎ ያገኘን መድኃኒታችን ወደኛ ሥጋን ለብሶ የመጣበት ትልቁ፣ መሠረታዊና መጨረሻ ምክንያት ስለዚህ ኃጢአትን የሚያስተሠረይ ዘላለማዊ መሥዋዕት ሲል ነው፡፡ የአርብ ሥጋውን በሐሙስ ኅብስት፥ የአርብ ደሙን በሐሙስ ወይን አድርጎ ባርኮ እንበላው እንጠጣው ዘንድ ራሱን መሥዋዕት ያደረገ ቅዱስ በግ፤ ለበጎቹ ራሱን የሚመግብ ቅዱስ እረኛ!

እናስታውስ! ከእግዚአብሔር የተለየነው በመብል ምክንያት ነው ብለናል፡፡ እህሳ ወደ እግዚአብሔር የመመለሻው መንገድም የተዘረጋልን እንዲሁ በመብል በኩል ነው፡፡ በልተን ትተነው እንደወጣን፤ እንደገና በልተን ደግሞ ወደተውነው አምላክ እንመለሳለን፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን . . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2372
Create:
Last Update:

    "ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።"

                                      (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5፥19
)

አትብሉ የሚል ትእዛዝ ያሰመረው እግዚአብሔር፤ መስመሩ ተጥሶበታል፡፡ አዳም ሕግ በማፍረስ በደል ፈጽሞአል፡፡ ስለዛ ካሳ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ ለንጉሥ እግዚአብሔር የሚሆን እጅ መንሻ መስጠት ይገባዋል፡፡ ሆኖም ይህንን አምኃ ችሎ ሊከፍል አልተቻለውም፡፡ ሞትን የሚክስ ሕይወት፣ ውድቀትን የሚሽር ትንሣኤ፣ የተዘጋውን ማኅተም የሚከፍት ቁልፍ ከፍጥረት ዘንድ አልተገኘም፡፡ ዮሐንስ ፦

     "በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም። መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ። "ከሽማግሌዎቹም አንዱ። አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ።"

                                             (የዮሐንስ ራእይ 5፥3-5)

አበው በሰባት ማኅተሞች የተዘጋው መጽሐፍ አንድም ሰው ((ሰ)ብእ-(ሰ)ባት) ነው ይላሉ፡፡ ከነዚህ ማኅተሞች አንዱ ሞት ነው፡፡ "አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ" የሚለውን ድምፅ ያደመጠ ባሕሪያችን ሞትን መሻገር ቢፈልግም አልሆነለትም፡፡ አለመሞት የሚባለውን ገጽ ሊዘረጋና ገልጦ ሊያነበው ማንም አልቻለም፡፡

ይህንን ያወቀቺው የባለ ራእዩ ነፍስ፤ ስለ ሁሉ የሰው ልጅ ሕይወት ተወክላ ስለተዘጉባት ማኅተሞችና ሊከፈቱም ስላለመቻላቸው አስባ አምርራ አለቀሰች፡፡ በዚህን ጊዜ አንድ የሚያጽናና ድምፅ "ከይሁዳ ወገን የሆነ አንበሳ እርሱም የዳዊት ልጅ" የተባለ ማኅተሞቹን ሊተረትራቸውና መጽሐፉን ሊገልጠው እንደቻለ ተናገረ፡፡ ይሄ ድል ነሺ መድኃኒቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!

ለእጅ መንሻ የሚቀርብ ንጹሕ በግ፣ እጅ መንሻውን የሚያቀርብ ሊቀ ካህን፣ እጅ መንሻውን የሚቀበል ንጉሥ ራሱ ሆኖ፤ መድኃኒቱ በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ እንከፍለው ዘንድ የሚገባውን ዕዳ በእኛ ቦታ ሆኖ ከፈለልን፡፡ ሞት የማይገባውን ሥጋውን ለሞት አሳልፎ በመስጠት፣ መፍሰስ የሌለበት ቅዱስ ደሙን ስለ ኃጢአታችን ቤዛ በማፍሰስ፤ ለመተላለፋችን ካሳ የሚሆን ንጹሕ አምኃን ሰጠ፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ሥጋና ደሙን ቅዱስ ቁርባን እየተባለ እንዲጠራ ያደረገው ቀዳሚ ምክንያት፡፡

ሌላውና ዋነኛው ደግሞ ቁርባን በግእዙ አቻ ፍቺ መቀራረቢያ፣ መገናኛ ማለት ነው ተባብለናል፡፡ ይህም ትርጉም እንዲሁ ለመድኃኒቱ ሥጋና ደም የሚስማማ ነው፡፡ በወደፊት ክፍሎች ላይ በሰፊው ስለምንመለስበት ለመግቢያ ያህል በሚሆን እናብራራው፡፡

ባሳለፍነው የንስሐ ምዕራፍ ላይ ከአምላክ ፈቃድ ከተለየን በኋላ ፊታችን ወደ ዓለም ጀርባችን ወደ እግዚአብሔር ዞሮ እንደምንኖር አይተናል፡፡ ይሄን በሌላ አገላለጽ ከእግዚአብሔር ርቀን ለዲያቢሎስ ቀርበን በምድር መመላለስ ጀመርን ልንለው እንችላለን፡፡

በዚህ አኗኗር ውስጥ ሳለን፤ ዘመን ምሕረትን ባመጣልን የመዳን ጊዜ ላይ "አማኑኤል" በተባለ ስሙ ከእኛ ጋር ሊሆን ያፈቀረ ክርስቶስ፤ መለኮት የተዋሐደውን ሥጋና ደሙን ለእኛ በመስጠት ከእግዚአብሔር ለያይቶን የነበረውን የመራራቅ ግድግዳ አፍርሶ አንድነትን አምጥቶአል፡፡

    "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ (አንድነት!)።"

                                                 (የዮሐንስ ወንጌል 6፥56)


እግዚአብሔር በእኛ ከሚኖርበት እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር ከምንኖርበት ክሂል ወጥተን ለዘላለሙ እንዳንጠፋ፤ መድኃኒቱ ሥጋውን መብል ደሙን መጠጥ በማድረግ ራሱን በውስጣችን እኛን ደግሞ በውስጡ በማኖር፤ ከራሱ ጋር አቀራረበን፣ አገናኘን፡፡ ይህን የእውነት መሠረት ስናውቅም፤ የጌታችን ሥጋውና ደሙ ቁርባን መባሉ ትክክለኛ ሃይማኖታዊ አተረጓገም ስለመሆኑ ግንዛቤ እንወስዳለን፡፡

ሦስተኛ ቁርባን ማለት መሥዋዕት ማለት እንደሆነ አይተናል፡፡ በተስፋና በቃል ስለ እግዚአብሔር ልጅ መወለድ ሲናገር የቆየው ብሉዩ ዘመን፤ ቁርባንን በመሥዋዕትነቱ ሲገለገልበት ቆይቷል፡፡ በሐዲስ ኪዳኑ ጊዜ ላይ አማናዊ መሥዋዕት ሆኖ ስለሚቀርበው የክርስቶስ ሥጋና ደም ምሳሌ ያደረጉ፤ በትንቢትነት የተገለጡ፤ የተለያዩ የእንስሳትና የዕፅዋት መሥዋዕቶች ለእግዚአብሔር ሲቀርቡ ነበር፡፡ ለምሳሌ ያህል ፦

የልዑል እግዚአብሔር ካህንና የሳሌም ንጉሥ ያቀረበው የኅብስትና የወይን መሥዋዕት ለክርስቶስ ዘላለማዊ ሊቀ ካህናትነትና ለሥጋው ወደሙ ዓይነተኛ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል (ዘፍ 14፤18 ዕብ 5፣6 እና 10፣7፥17)። ሁለተኛ፤ ከቀሳፊ የሞት መልአክ አድኖ ከግብጽ ባርነት ነፃ ያወጣቸው የፋሲካ በግ ደም መረጨትና ሥጋውም ተጠብሶ መበላቱ የእግዚአብሔር በግ ለተባለው ለመድኃኒቱ አዳኝነትና ለምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ ሆኗል (ዘፀ 12፤1:51 1ኛ ቆሮ 4፣7)። ሦስተኛ፤ እሥራኤላውያን በምድረ በዳ ይመገቡት የነበረው ከሰማይ የወረደው መና ዛሬ ምእመናን ለነፍሳቸው ምግብ የሚቀበሉት የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ነው (ዘፀ 16፣16፥23 ዮሐ 6፣49፥51)። አራተኛ፤ ጥበብ ያዘጋጀችው ማዕድ፣ ያረደችው ፍሪዳ፣ የጠመቀችው የወይን ጠጅ፣ የላከቻቸው አገልጋዮቿ የተጠሩት ሰዎች ሁሉ ምሳሌነት እንዳላቸው ይነገራል። ጥበብ የክርስቶስ፣ ማዕድ የሥጋው የደሙ፣ አገልጋዮች የካህናት፣ ተጋባዦች የምእመናን ምሳሌ ናቸው ተብሎ ይተረጎማል (ምሳ 9፤1፥5)። ይህን የመሳሰሉ ሌሎች ምሳሌዎችም አሉ (ዘሌዋ 2፤ 23፣13፥14 ሲራክ 24፣19፥21)።

ለአካሉ ጥላ ሆኖ የነበረው ዘመን ሲያበቃ፤ የብሉይ ዓመታትን መሥዋዕት የሚጠቀልል አንድ የመሥዋዕት ሥርዓት በመድኃኒቱ አማካኝነት ከስቅለት ቀን በፊት በነበረው የመጨረሻው እራት በሚሰኘው ዕለተ ሐሙስ ላይ ተመሠረተ፡፡

   "ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።"

                                               (የማቴዎስ ወንጌል 26፥28)

ከጠፋንበት ፈልጎ ያገኘን መድኃኒታችን ወደኛ ሥጋን ለብሶ የመጣበት ትልቁ፣ መሠረታዊና መጨረሻ ምክንያት ስለዚህ ኃጢአትን የሚያስተሠረይ ዘላለማዊ መሥዋዕት ሲል ነው፡፡ የአርብ ሥጋውን በሐሙስ ኅብስት፥ የአርብ ደሙን በሐሙስ ወይን አድርጎ ባርኮ እንበላው እንጠጣው ዘንድ ራሱን መሥዋዕት ያደረገ ቅዱስ በግ፤ ለበጎቹ ራሱን የሚመግብ ቅዱስ እረኛ!

እናስታውስ! ከእግዚአብሔር የተለየነው በመብል ምክንያት ነው ብለናል፡፡ እህሳ ወደ እግዚአብሔር የመመለሻው መንገድም የተዘረጋልን እንዲሁ በመብል በኩል ነው፡፡ በልተን ትተነው እንደወጣን፤ እንደገና በልተን ደግሞ ወደተውነው አምላክ እንመለሳለን፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን . . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2372

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Matt Hussey, editorial director at NEAR Protocol also responded to this news with “#meIRL”. Just as you search “Bear Market Screaming” in Telegram, you will see a Pepe frog yelling as the group’s featured image. To delete a channel with over 1,000 subscribers, you need to contact user support Click “Save” ; Telegram channels fall into two types: The public channel had more than 109,000 subscribers, Judge Hui said. Ng had the power to remove or amend the messages in the channel, but he “allowed them to exist.”
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American