BEMALEDANEK Telegram 2384
አንድን በግ በሕይወት ወይንም በተለምዶ አገላለጽ ከነነፍሱ እያለ ልንበላው አንችልም፡፡ ሊታረድና ሥጋው በአግባቡ ለመብልነት እንዲሆን ተዘጋጅቶ ሊወጣ ግድ ይላል፡፡ እንዲሁ የእግዚአብሔር በግ ክርስቶስም በሐሙስ ማታ ሥጋዬን ብሉ፥ ደሜንም ጠጡ በሚልበት ሰዓት በመስቀል ላይ ገና አልታረደም ነበር፡፡ በሌላ አባባል አልሞተም ነበር፡፡ ስለዚህ ሥጋውን በመለኮት ጥበብ የተቀደሰ ሕብስት፥ ደሙንም ወይን አድርጎ ሲሰጣቸው፤ የሥጋና ደሙ ኃጢአትን የማስተሠረይ ኃይል የሚፈጸመው በአርብ መሰቀሉ እንዲሆን መንክር ሥርዓት አበጅቶ ነው፡፡ "ስለ ብዙዎች የሚፈስ ደሜ" ያለውም ለዚህ ነው፡፡ ደሙ የፈሰሰው አርብ ነው፡፡ እንኪያስ የዳንነው (ኃጢአታችን የተፈወሰው) በቁስሉ (በፈሰሰ ደሙ) ነው መባሉ እውነት ነው፡፡

በክርስቲያኖች ዘንድ ዝነኛ የሆነውና የተወደደው "በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን" የሚለው የጥቅስ ቃል ሲነበብ አሊያ በአንደበት ሲነገር ደስ ይላል፡፡ በእምነት ተቀብለን በሕይወት የሚገለጥ "ኑሮ" የምናደርገው ግን፤ በመበላቱ ይፈውሰን ዘንድ ለቁስል ተላልፎ የተሰጠ ሥጋውን ስንወስድ የተገኘን እንደሆነ ነው፡፡

በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ምእመን፤ "በእርሱ ቁስሉ እኔ ተፈወስኩ" የሚል ንግግር ሲያሰማ፤ ለቁስል የተዳረገን የጌታን ሥጋ ስለመቀበሉ እርግጠኛ መሆን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም ቁስሉ እኛን ሊፈውስ የቻለው፤ "ሥጋዬን ብሉ፥ ደሜንም ጠጡ" ሲል፤ መድኃኒት እርሱነቱን ከውስጣችን እንዲኖር የሚያደርግ አማናዊ ኪዳን ስለተሠራልን ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፤ ጌታ አርብ ላይ በመስቀል ሥጋውን የቆረሰው፥ ደሙን ያፈሰሰው፤ የሐሙሱ የሥርየት ቃልኪዳን ወደ ፍጻሜ እንዲመጣ ነውና፤ ቅዱስ ቁርባንን ትቶ እንዲሁ በደፈናው በጌታ ተፈውስኩ ማለት፤ የታዘዘ መድኃኒትን ሳይውጡ ከሕመሜ ዳንኩ እንደማለት ነው፡፡

ቅዱስ ቁርባን ስለ ሰዎች ልጆች ኃጢአት ሥርየት ተብሎ የተሰናዳ ሰማያዊ ሥርዓት ነው፡፡ በእግዚአብሔር ልጅ አምነን በስሙ የሚዘጋጀውን ማዕድ ስንካፈል፤ በመጀመሪያው ከአንዱ የአዳም ዘር በመሆናችን ምክንያትነት በመወለድ የሚከተለንን የእርግማን ገመድ እንበጥሳለን፡፡ በመቀጠል ከአዳም ኃጢአት ብቻ ሳይሆን፤ ከእውቀት ዛፍ በመብላታችን ክፉና ደጉን በጊዜያችን ውስጥ ስለምንሠራ፤ በክፉ እውቀት (በመንፈስ ርኩስ) የሚመራውን ኃጢአት እንድንደመስስ፤ በመልካም እውቀት (በመንፈስ ቅዱስ) የሚመራውን ጽድቅ ደግሞ እንድናጠነክር ኃይል እናገኛለን፡፡

የክርስቶስን ሥጋና ደም እየተቀበልን ስንኖር በሚከተሉት መንገዶች የኃጢአት ሥርየት ይከሰታል ፦

፩•  በሥጋ ከአዳም ቤተሰብ ሁላችን ተወልደናልና በባሕርየ ሰብ ውስጥ ከሚከተለን ከገነቱ ጥፋት ነጻ እንወጣለን (ይሄን በ40 እና በ80 ቀን የጥምቀት ቁርባን ላይ ብዙዎቻችን አግኝተነዋል)
፪•  በትውልዳችን የዘር ሐረግ ውስጥ የነበሩ የዓመፃ መዝገቦችና የበደል ሥራዎች ሁሉ ከነታሪካቸው ይፋቃሉ
፫•  በየጊዜው ኑሮአችን ውስጥ ስፍራ ይዘው ለመቆየት የሚታገሉ የአሳብ (ሐልዮ)፣ የቃል (ነቢር) እና የድርጊት (ገቢር) ኃጢአቶች ሥርየት ያገኛሉ

ስምዖን የሚባል አንድ ፈሪሳዊ በመድኃኒቱ ዘመን ነበረ አሉ፡፡ ይህም ሰው ጌታ ወደርሱ ቤት መጥቶ እንዲጋበዝ አጥብቆ ይወተውታል፡፡ ጥያቄውም ተቀባይነት ያገኝና መድኃኒቱ በጠሪው ቤት ለማዕድ ይሰየማል፡፡ ይህንን ሁሉ በርቀት ትከታተል የነበረች በከተማው ውስጥ የምትኖር አንዲት በኃጢአት አሽክላ የተያዘች ሴት፤ መድኃኒቱ የገባበትን ቤት ለይታ ካወቀች በኋላ ሽቱ የሞላበት ውድ የሆነ የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ ወደ ፈሪሳዊው መኖሪያ ዘለቀች፡፡ ከገባችም በኋላ ከመድኃኒቱ "በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች።" (የሉቃስ ወንጌል 7፥38) ይህንን ያየው ጋባዡ ባለቤትም፤ የሴትየዋ ኃጢአት በጌታ ፊት ሳይገለጥ በመቅረቱ እየታዘበ በልቡ ነገር ያመላልሳል፡፡ መድኃኒቱም የውስጡን አውቆ ለሰውየው የሚሆን ምላሽ ሰጠና ከበታቹ ወድቃ የምታለቅሰውን ሴት ደግፎ አነሣት፡፡ በስተመጨረሻም እንዲህ አላት "ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል"፡፡ (የሉቃስ ወንጌል 7፥48)

እንግዲህ ክርስቲያኖች እንዲህ ነው የምናምነው፡፡ ተወዳጁ ወደ ሕይወታችን ይመጣ ዘንድ የወደደው ስለ ኃጢአታችን እንደሆነ እናምናለን፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከኃጢአት ፍዳ ሊያድነንም ከመካከላችን እንደገባ እናምናለን፡፡ ግን እጅግ ብዙዎቻችን ያመንነውን የምንኖር አይመስልም፡፡ ከሁለት ሺሕ ዓመታት በፊት ምስኪኒቱን ሴት "ከኃጢአት ማሠሪያ ተፈትተሻልና በሰላም ሂጂ" ሲል የተናገረ ጌታ፤ ዛሬም ይህንኑ የምሕረት ድምፅ በሥጋውና በደሙ ውስጥ አኑሮልን ወደ አባቱ እንደተመለሰ አልገባንም፤ ወይንም የገባንን በሕይወት መተርጎም አልፈለግንም፡፡

ስለዚህ የኃጢአት ሥርየትን ያላገኘ ሰውነታችን፤ ተገልጾ በማይወጣ የነፍስ ጭንቀት መተንፈሻ እያጣ፤ ይህንንም ያልተገለጸ ጭንቀት በሌሎች የተገለጹ ሥጋዊ ጭንቀቶች ለመርሳት እየዳከረ፤ አሁን ታይቶ አሁን የሚጠፋ ቅጽበታዊ ደስታን ለማቆየት ብዙ እየደከመ ቀናቱን ይገፋል፡፡ በመድኃኒቱ ትእዛዝ ዝም እንዲል ያልታዘዘው፥ ከውስጣችን የሚናወጠው፥ የኃጢአት ማዕበል፤ የሰከነ እፎይታንና አስተማማኝ እረፍትን ነስቶን፤ ስሜትና ትርጉም በሌለው የመኖር ጉዞ እንድንባዝን አስገድዶናል፡፡ የኃጢአትን ሰንሰለት ከበጠሰ በኋላ፤ እውነተኛ ሰላሙን ከሚታይ አካላችን ሥር ላለ የማይታይ ሕይወታችን ሊያካፍለን እጁን ወደኛ የዘረጋውን ጌታ፤ እንዴት ወደ ውስጣችን እንደምንይዘው ስላላወቅን፤ ብናውቅም እንኳ የተለያየ ሰበብ እየሰጠን መዳፉን ከመጨበጥ ሰለዘገየን፤ በክፉ እውቀት የሚገለጸው ዲያቢሎስ በሁሉም መንገድ አኗኗራችንን ከንቱ ሊያደርግ እርሱ አስቀድሞ እኛን ጨበጠን፡፡ በመሆኑም "በሰላም ሂዱ!" የሚለው የአምላክ ቃል ለሕልውናችን ስላልተደመጠ፤ በትንሹም መረበሽ፥ በትልቁም መረበሽ ዕጣችን ሆኖ፤ በየደረስንበት ቦታ ተጠራጣሪና ድንጉጥ ሆነን ችግርን በሰቀቀን እንጠባበቃለን፡፡

በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች በክርስቶስ ቁስል አልተፈወስንም፡፡ ለምን፤ ከኃጢአት ደዌ የሚያድነው የመድኃኒቱ ሥጋና ደም በብዙ ምክንያቶች ወደ ሥጋና ደማችን አልገባም፡፡ ይልቁኑ ወደ ውስጥ ሰውነታችን እንዲገባ የፈቀድነው የሚፈርሰውን እህልና ውኃ ብቻ ስለሆነ፤ ውጨኛው ኑሮአችንም እንዲሁ ይህንን የመፈረስ ገጽታ ይዞ፤ ተምረን ተምረን ባዶ፣ ሠርተን ሠርተን ባዶ፣ አቅደን አቅደን ባዶ በሆነብን ጊዜ ላይ በዘወትር ምሬት እንመላለሳለን፡፡

እናም፤ እንዲፈወስ ዕድል ያልተሰጠው ቁስላችን፤ ከዓመት ወደ ዓመት እያመረቀዘና እየሰፋ ሄዶ፤ አሁን በነኩን አካል ላይ ሁሉ ሕመም እየተሰማን፤ ውኃ ሲቀጥን ሲወፍር እየከፋን፣ በሆነ ባልሆነው ቶሎ ሆድ እየባሰን፣ በመጣ ባልመጣው እየተደናገርን፣ በሚሳካ በማይሳካው እየተብሰከሰክን፤ በውድ ዋጋ ተሠርቶ በነጻ የተሰጠ መድኃኒት እያለን፤ በርካሽ ዋጋ ተሠርቶ በውድ ዋጋ የሚገዛ ክኒን ለጭንቀት ማቅለያ እንውጣለን፡፡ ኸረ እስከ ዘላለም የታመነው፥ ታምኖም በሕልውና የሚነበበው፥ መጽሐፍ እንዲህ ነው የሚለው፤ "በእርሱም ቍስል (በተቆረሰ ክቡር ሥጋና በፈሰሰ ቅዱስ ደም) እኛ ተፈወስን (የኃጢአት ሥርየት አገኘን)።"

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek



tgoop.com/bemaledanek/2384
Create:
Last Update:

አንድን በግ በሕይወት ወይንም በተለምዶ አገላለጽ ከነነፍሱ እያለ ልንበላው አንችልም፡፡ ሊታረድና ሥጋው በአግባቡ ለመብልነት እንዲሆን ተዘጋጅቶ ሊወጣ ግድ ይላል፡፡ እንዲሁ የእግዚአብሔር በግ ክርስቶስም በሐሙስ ማታ ሥጋዬን ብሉ፥ ደሜንም ጠጡ በሚልበት ሰዓት በመስቀል ላይ ገና አልታረደም ነበር፡፡ በሌላ አባባል አልሞተም ነበር፡፡ ስለዚህ ሥጋውን በመለኮት ጥበብ የተቀደሰ ሕብስት፥ ደሙንም ወይን አድርጎ ሲሰጣቸው፤ የሥጋና ደሙ ኃጢአትን የማስተሠረይ ኃይል የሚፈጸመው በአርብ መሰቀሉ እንዲሆን መንክር ሥርዓት አበጅቶ ነው፡፡ "ስለ ብዙዎች የሚፈስ ደሜ" ያለውም ለዚህ ነው፡፡ ደሙ የፈሰሰው አርብ ነው፡፡ እንኪያስ የዳንነው (ኃጢአታችን የተፈወሰው) በቁስሉ (በፈሰሰ ደሙ) ነው መባሉ እውነት ነው፡፡

በክርስቲያኖች ዘንድ ዝነኛ የሆነውና የተወደደው "በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን" የሚለው የጥቅስ ቃል ሲነበብ አሊያ በአንደበት ሲነገር ደስ ይላል፡፡ በእምነት ተቀብለን በሕይወት የሚገለጥ "ኑሮ" የምናደርገው ግን፤ በመበላቱ ይፈውሰን ዘንድ ለቁስል ተላልፎ የተሰጠ ሥጋውን ስንወስድ የተገኘን እንደሆነ ነው፡፡

በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ምእመን፤ "በእርሱ ቁስሉ እኔ ተፈወስኩ" የሚል ንግግር ሲያሰማ፤ ለቁስል የተዳረገን የጌታን ሥጋ ስለመቀበሉ እርግጠኛ መሆን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም ቁስሉ እኛን ሊፈውስ የቻለው፤ "ሥጋዬን ብሉ፥ ደሜንም ጠጡ" ሲል፤ መድኃኒት እርሱነቱን ከውስጣችን እንዲኖር የሚያደርግ አማናዊ ኪዳን ስለተሠራልን ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፤ ጌታ አርብ ላይ በመስቀል ሥጋውን የቆረሰው፥ ደሙን ያፈሰሰው፤ የሐሙሱ የሥርየት ቃልኪዳን ወደ ፍጻሜ እንዲመጣ ነውና፤ ቅዱስ ቁርባንን ትቶ እንዲሁ በደፈናው በጌታ ተፈውስኩ ማለት፤ የታዘዘ መድኃኒትን ሳይውጡ ከሕመሜ ዳንኩ እንደማለት ነው፡፡

ቅዱስ ቁርባን ስለ ሰዎች ልጆች ኃጢአት ሥርየት ተብሎ የተሰናዳ ሰማያዊ ሥርዓት ነው፡፡ በእግዚአብሔር ልጅ አምነን በስሙ የሚዘጋጀውን ማዕድ ስንካፈል፤ በመጀመሪያው ከአንዱ የአዳም ዘር በመሆናችን ምክንያትነት በመወለድ የሚከተለንን የእርግማን ገመድ እንበጥሳለን፡፡ በመቀጠል ከአዳም ኃጢአት ብቻ ሳይሆን፤ ከእውቀት ዛፍ በመብላታችን ክፉና ደጉን በጊዜያችን ውስጥ ስለምንሠራ፤ በክፉ እውቀት (በመንፈስ ርኩስ) የሚመራውን ኃጢአት እንድንደመስስ፤ በመልካም እውቀት (በመንፈስ ቅዱስ) የሚመራውን ጽድቅ ደግሞ እንድናጠነክር ኃይል እናገኛለን፡፡

የክርስቶስን ሥጋና ደም እየተቀበልን ስንኖር በሚከተሉት መንገዶች የኃጢአት ሥርየት ይከሰታል ፦

፩•  በሥጋ ከአዳም ቤተሰብ ሁላችን ተወልደናልና በባሕርየ ሰብ ውስጥ ከሚከተለን ከገነቱ ጥፋት ነጻ እንወጣለን (ይሄን በ40 እና በ80 ቀን የጥምቀት ቁርባን ላይ ብዙዎቻችን አግኝተነዋል)
፪•  በትውልዳችን የዘር ሐረግ ውስጥ የነበሩ የዓመፃ መዝገቦችና የበደል ሥራዎች ሁሉ ከነታሪካቸው ይፋቃሉ
፫•  በየጊዜው ኑሮአችን ውስጥ ስፍራ ይዘው ለመቆየት የሚታገሉ የአሳብ (ሐልዮ)፣ የቃል (ነቢር) እና የድርጊት (ገቢር) ኃጢአቶች ሥርየት ያገኛሉ

ስምዖን የሚባል አንድ ፈሪሳዊ በመድኃኒቱ ዘመን ነበረ አሉ፡፡ ይህም ሰው ጌታ ወደርሱ ቤት መጥቶ እንዲጋበዝ አጥብቆ ይወተውታል፡፡ ጥያቄውም ተቀባይነት ያገኝና መድኃኒቱ በጠሪው ቤት ለማዕድ ይሰየማል፡፡ ይህንን ሁሉ በርቀት ትከታተል የነበረች በከተማው ውስጥ የምትኖር አንዲት በኃጢአት አሽክላ የተያዘች ሴት፤ መድኃኒቱ የገባበትን ቤት ለይታ ካወቀች በኋላ ሽቱ የሞላበት ውድ የሆነ የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ ወደ ፈሪሳዊው መኖሪያ ዘለቀች፡፡ ከገባችም በኋላ ከመድኃኒቱ "በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች።" (የሉቃስ ወንጌል 7፥38) ይህንን ያየው ጋባዡ ባለቤትም፤ የሴትየዋ ኃጢአት በጌታ ፊት ሳይገለጥ በመቅረቱ እየታዘበ በልቡ ነገር ያመላልሳል፡፡ መድኃኒቱም የውስጡን አውቆ ለሰውየው የሚሆን ምላሽ ሰጠና ከበታቹ ወድቃ የምታለቅሰውን ሴት ደግፎ አነሣት፡፡ በስተመጨረሻም እንዲህ አላት "ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል"፡፡ (የሉቃስ ወንጌል 7፥48)

እንግዲህ ክርስቲያኖች እንዲህ ነው የምናምነው፡፡ ተወዳጁ ወደ ሕይወታችን ይመጣ ዘንድ የወደደው ስለ ኃጢአታችን እንደሆነ እናምናለን፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከኃጢአት ፍዳ ሊያድነንም ከመካከላችን እንደገባ እናምናለን፡፡ ግን እጅግ ብዙዎቻችን ያመንነውን የምንኖር አይመስልም፡፡ ከሁለት ሺሕ ዓመታት በፊት ምስኪኒቱን ሴት "ከኃጢአት ማሠሪያ ተፈትተሻልና በሰላም ሂጂ" ሲል የተናገረ ጌታ፤ ዛሬም ይህንኑ የምሕረት ድምፅ በሥጋውና በደሙ ውስጥ አኑሮልን ወደ አባቱ እንደተመለሰ አልገባንም፤ ወይንም የገባንን በሕይወት መተርጎም አልፈለግንም፡፡

ስለዚህ የኃጢአት ሥርየትን ያላገኘ ሰውነታችን፤ ተገልጾ በማይወጣ የነፍስ ጭንቀት መተንፈሻ እያጣ፤ ይህንንም ያልተገለጸ ጭንቀት በሌሎች የተገለጹ ሥጋዊ ጭንቀቶች ለመርሳት እየዳከረ፤ አሁን ታይቶ አሁን የሚጠፋ ቅጽበታዊ ደስታን ለማቆየት ብዙ እየደከመ ቀናቱን ይገፋል፡፡ በመድኃኒቱ ትእዛዝ ዝም እንዲል ያልታዘዘው፥ ከውስጣችን የሚናወጠው፥ የኃጢአት ማዕበል፤ የሰከነ እፎይታንና አስተማማኝ እረፍትን ነስቶን፤ ስሜትና ትርጉም በሌለው የመኖር ጉዞ እንድንባዝን አስገድዶናል፡፡ የኃጢአትን ሰንሰለት ከበጠሰ በኋላ፤ እውነተኛ ሰላሙን ከሚታይ አካላችን ሥር ላለ የማይታይ ሕይወታችን ሊያካፍለን እጁን ወደኛ የዘረጋውን ጌታ፤ እንዴት ወደ ውስጣችን እንደምንይዘው ስላላወቅን፤ ብናውቅም እንኳ የተለያየ ሰበብ እየሰጠን መዳፉን ከመጨበጥ ሰለዘገየን፤ በክፉ እውቀት የሚገለጸው ዲያቢሎስ በሁሉም መንገድ አኗኗራችንን ከንቱ ሊያደርግ እርሱ አስቀድሞ እኛን ጨበጠን፡፡ በመሆኑም "በሰላም ሂዱ!" የሚለው የአምላክ ቃል ለሕልውናችን ስላልተደመጠ፤ በትንሹም መረበሽ፥ በትልቁም መረበሽ ዕጣችን ሆኖ፤ በየደረስንበት ቦታ ተጠራጣሪና ድንጉጥ ሆነን ችግርን በሰቀቀን እንጠባበቃለን፡፡

በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች በክርስቶስ ቁስል አልተፈወስንም፡፡ ለምን፤ ከኃጢአት ደዌ የሚያድነው የመድኃኒቱ ሥጋና ደም በብዙ ምክንያቶች ወደ ሥጋና ደማችን አልገባም፡፡ ይልቁኑ ወደ ውስጥ ሰውነታችን እንዲገባ የፈቀድነው የሚፈርሰውን እህልና ውኃ ብቻ ስለሆነ፤ ውጨኛው ኑሮአችንም እንዲሁ ይህንን የመፈረስ ገጽታ ይዞ፤ ተምረን ተምረን ባዶ፣ ሠርተን ሠርተን ባዶ፣ አቅደን አቅደን ባዶ በሆነብን ጊዜ ላይ በዘወትር ምሬት እንመላለሳለን፡፡

እናም፤ እንዲፈወስ ዕድል ያልተሰጠው ቁስላችን፤ ከዓመት ወደ ዓመት እያመረቀዘና እየሰፋ ሄዶ፤ አሁን በነኩን አካል ላይ ሁሉ ሕመም እየተሰማን፤ ውኃ ሲቀጥን ሲወፍር እየከፋን፣ በሆነ ባልሆነው ቶሎ ሆድ እየባሰን፣ በመጣ ባልመጣው እየተደናገርን፣ በሚሳካ በማይሳካው እየተብሰከሰክን፤ በውድ ዋጋ ተሠርቶ በነጻ የተሰጠ መድኃኒት እያለን፤ በርካሽ ዋጋ ተሠርቶ በውድ ዋጋ የሚገዛ ክኒን ለጭንቀት ማቅለያ እንውጣለን፡፡ ኸረ እስከ ዘላለም የታመነው፥ ታምኖም በሕልውና የሚነበበው፥ መጽሐፍ እንዲህ ነው የሚለው፤ "በእርሱም ቍስል (በተቆረሰ ክቡር ሥጋና በፈሰሰ ቅዱስ ደም) እኛ ተፈወስን (የኃጢአት ሥርየት አገኘን)።"

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2384

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

5Telegram Channel avatar size/dimensions Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. The optimal dimension of the avatar on Telegram is 512px by 512px, and it’s recommended to use PNG format to deliver an unpixelated avatar. Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American