BEMALEDANEK Telegram 2390
ዘላለማዊነትን ከፊደል ትምህርት ሰነዶቿና ፍኖተ ካርታዎቿ፣ ከሥራ መዋቅሯና የመሥሪያ ደንቦቿ፣ ከዜጎች የሕይወት መርህና የአኗኗር ሥርዓት፣ ከቴክሎኖጂ ውጤቶቿና ከምርምር ግኝቶቿ፣ ከፖለቲካዊ መርሆቿና ሕጓቿ አርቃ ያወጣቺው ይህቺ ዓለም፤ የሕያውነትን ኃይል ከብዙ ሰዎች ግንዛቤ ውስጥ አሽሽታዋለች፡፡

ለዘላለም ተፈጥረን ለጊዜዎች እንድንኖር የሚሸብበን የዓለም ወጥመድ ላይ ንቃተ ሕሊና የሌለን አማኞችም፤ በደረስንባቸው የኑሮ ሁኔታዎችና ቆይታዎች ላይ የሚያጋጥሙን ነገሮች ሁሉ ጊዜያዊ ሆነው አረፉ፡፡ አልሆኑም? .. ከደስታም ጊዜያዊ፣ ከእፎይታም ጊዜያዊ፣ ከዕረፍትም ጊዜያዊ፣ ከተስፋም ጊዜያዊ፣ ከጸጋና ከበረከትም ጊዜያዊ፣ ከሞገስና ከማስተዋልም ጊዜያዊ፣ ከጥበብና ከችሎታም ጊዜያዊ ቆይታ ያለን ታይቶ ጠፊዎች አልሆንም?

አዳማዊያን ስንፈጠር ጊዜዎች ወደ ሕይወታችን የሚያመጧቸውን ነገራት ወደ ራሳችን የመኖር ውህደትና የመስመር ስምምነት ከማምጣታችን በፊት 'ምን መጣ?' የሚለውን ለማጥለል እንድንችል፤ ከመጣው ጉዳይ አሊያ አጋጣሚ መካከል ክፋትን ለይተን፥ መልካሙን አስቀርተን፤ አንጥረን፤ እንጠቀም ዘንድ አእምሮ ከግራ ቀኝ የማጤኛ ልቦና ጋራ ታድለን የነበረን ቢሆንም፤ ሰዎች ዛሬ ከተሰጣቸው በታች የሚኖሩ ሲሆን፤ ጊዜ እንዳመጣው የሚመጡ፣ ጊዜ እንደሚወስደው የሚሄዱ እየሆኑ፤ ወደ ዓለም በጊዜ እንደመጡ ከዓለምም ተለይተው በጊዜያቸው ይሄዳሉ፡፡ የዘላለም ሕይወት ከውስጣችን የሚጀምርበት የእምነት ጥበብ ስለጠፋን፤ ጊዜ ጀምሮ፤ ጊዜ እንዳደረገን አድርጎ፤ ጊዜ ይጨርስናል፡፡ በዕድሜያችን ጊዜዎች መካከል ልዩ ማንነታችንን ሳንፈልገውና አግኘተን ሳንጠቀምበት፤ ጊዜው ለኛ የሚስማማውን እንዲያቆይልን፥ የማይጠቅምንን እንዲወስድልን በመንፈሳዊ ኃይል ሳንቆጣጠረው፤ ሳንሞት በጊዜዎች ውስጥ በኑሮ ሞተን ደግሞ እንደገና በአካል የምንሞትበት ጊዜ ሲደርስ ወደ መቃብር እንሸኛለን፡፡

ዮሐንስ 6፥27 ላይ "ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና" ይላል፡፡ ለሚጠፋ መብል አትሥሩ ተብለን ግን ለዕለት እንጀራ ብቻ ስንባዝን ዕድሜያችን ሄደ፡፡ እንጀራ ብቻ ስናሳድድ፥ ሥጋችንም በዛው እንደ ባሕሪዩ ከነፍሳችን ርቆ ተሰደደ፡፡ በየቀኑ ለእንጀራ ኑሮ ብቻ የምንወጣ የምንገባ ፍጡሮች ሆነን፤ ሌሎች መንፈሳዊ እውነታዎችና ሰማያዊ ሚስጢሮች ከጉያችንም ሆነው እየተሸሸጉብን፤ የሕይወትን በረከት ያዝነው ስንል እያመለጠን፣ ልናድግ ነው ስል እየደከምን፣ ልናርፍ ነው ስንል ተጨማሪ እየሮጥን፣ ተረጋጋን ስንል አዲስ ችግር እያስጨነቀን፤ አልባረክ ባለ ጊዜ ውስጥ አልበረክት ያለ ዘመንን ተሸክመን ተቸገርን፡፡ አልፎም ተርፎ የመኖር ወዝ ተሟጥጦ እስከሚደበዝዝብን ድረስ ተፈተንን፡፡ አየህ? ለምድር እንጀራ ብቻ የመሮጥን ውጤት? የምድርን እንጀራ፣ የምድርን መብል፣ የምድርን ምቾት ፍለጋ ስትሮጥ መንገዱ ማለቂያ አይኖረውም፡፡ አጋመስኩት ብትል ዞረህ ከተነሣህበት ጅማሮ ላይ ትመለሳለህ፡፡ ደረስኩበት ብትል የሚቀርህን አስበህ በአእምሮም በአካልም አንድ ጊዜ ትዝላለህ፡፡ እንደዚህ ነው የሚለው በቃ "ለሚጠፋ መብል አትሥሩ!"

እሺ ታዲያ ለምን እንሥራ? ቃሉን መለስ ስናነበው እንደዚህ የሚል ምላሽ ይሰጠናል፤ "ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፡፡" ለዘላለም የሚኖር፡፡ ዛሬ ተበልቶ ነገ የሚርብ መብል አይደለም፡፡ ወሩን ሙሉ ተደክሞበት፣ ከክፉዎች ጋር በመታገል፣ ብዙ በመውጣትና በመድከም የሚመጣ መብል አይደለም፡፡ ይሄ የዘላለም መብል ነው፡፡ እርሱም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደሙ ነው፡፡ ቅዱስ ቁርባን፡፡

የዘላለም ሕይወትን አጥተው የጊዜዎች ሕይወትን ይመሩ ዘንድ ሰዎች እንዳይገደዱ አምላክ ሰው ሆኖ የዘላለም ቃሉን አሰማን፡፡ "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው" አለን፡፡

የክርስቶስን ሥጋና ደም መውሰድ ስንጀምር፤ ሥጋችን ከነፍስ ፈቃዳችን ጋር ተናብቦ ጉዞውን ወደ ሰባተኛው የዕረፍት ቀን ስለሚያቀናው፤ የእኛ እና የዓለም ጊዜዎች ቅርጻቸውን ወደ ዘላለማዊነት እየቀየሩ እየቀየሩ ይመጣሉ፡፡ የዕድሜ ሰዓቶቻችንና የምንኖርበት ዘመን ሰዓቶች ቅጽበታዊ የሆነ ኲነታቸውን እየለቀቁ ሊቆይ የሚችለውን፥ ሊጸና የሚችለውን ለማምጣት ሲሉ መሄድ ይጀምራሉ፡፡ ቅዱስ ቁርባን ስንወስድ ዘላለማዊነትን መኖር የምንጀምረው በሚከተሉት ሁለት ውስጣዊና ውጪያዊ መንገዶች ነው፡፡

በአንደኛው፥ እግዚአብሔር አምላክ ከምድር አፈር አበጅቶን ሰው ሊያደረገን ሕያው እስትንፋሱን ነፍስ አድርጎ በውስጣችን ሲያኖራት፤ ከውጪ የምንቀበለው የእግዚአብሔር አምላክ ሕያው ሥጋውና ሕያው ደሙ ለነፍሳችን ምግብና መጠጥ ይሆንላታል፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን የሕይወትህ ክፍል በሚሆንበት ጊዜ ዘላለማዊነት ከነፍስህ ውስጥ ስለሚጀምርና እየገዘፈ እየገዘፈ ስለሚመጣ ውስጣዊ ሕይወትህ ዝም ይላል፡፡

ዝምታው የሐዘን፣ የመቆዘም፣ የመባዘንና የመቆራመድ ሳይሆን የመረጋጋት ዝምታ ነው፡፡ የእፎይታ ዝምታ ከውስጥ በኩል በጥልቀት ይሰማሃል፡፡ ቢሆንም ባይሆንም ላንተ ምንም የማይሞቅ የማይበርድ አይነት ሆኖ ማዕበል ቢመታው የማይናወጽ እንደ ሐይቅ ጠለል በዝግታ የሚንሸዋሸው ዝምታ ከውስጥ ይሰማሃል፡፡ ከውስጥህ ያለው በሥጋና ደሙ መቀደስ በኩል የመጣው የዘላለማዊነትን መንፈስ ያዘለ ዝምታ፤ ብትታመም የማይደነግጥ፣ ብታጣ የማይሰጋ፣ ብትራብ የማይጨነቅ፣ ቢሞላልህ የማይፈነጥዝ፣ ቢተረፈረፍህ የማይኮፍስ፣ ብትጠግብ የማይወጣጠር ሰው አድርጎ ይቀርጽሃል፡፡ ቢመችህም ባይመችህም ዘወትር የውስጥ መደላደልና የማይሸበር ጸጥታ ያለው ሰው ትሆናለህ፡፡

ሁለተኛው፤ ሥጋና ደሙን በተደጋጋሚ በመቀበል የሕይወት ልምድ ውስጥ ሰውነትህን ስትቀድሰው ተፈጥሮ ወዳንተ እያዘነበለ፤ ላንተ እየታዘዘ፣ አንተን እያገዘ፣ የምትለውን እየሰማህ የምትኖርበትን ዘላለማዊነት ከውጪ ባለው ገጽታ በሚታይ እውነት ውስጥ ይገልጥልሃል፡፡

እግዚአብሔር ተፈጥሮን አንጾና አስተካክሎ ከፍጥረታት ጋር ሲያኖራት፤ የሰው ልጆችን እንደ አባትነቱ በፍጹም ፍቅሩ ለይቶ ሲፈጥር በነፍስ ሥልጣንነት በኩል እግዚአብሔርነት አካፍሎናልና ተፈጥሮ እንድታገለግለን ፍጥረታትን እንድንገዛ አክብሮ ቀረጸን፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 1፥28)
   
ይሄ ድንቅ ነገር ነው፡፡ የምድር ፍጥረታትን ሁሉ በየወገን ወገናቸውና በየነገድ ነገዳቸው ካበጃቸው በኋላ ስም የማውጣት ኃላፊነት ለሰው ልጅ ተሰጠው፡፡ አዳምም ለእንስሳትና ፍጡራኑ ሁሉ ስም ሲሰጣቸው፤ ስማቸውም ጸድቆላቸው እንዲታዘዙትና እንዲያገልግሉት ሆኑ፡፡ በፍጥረታቱም ሳያበቃ ተፈጥሮን አዳም እንዳሻው እንዲያበጃትና እንዲጠብቃት ተሰጠቺው፡፡

     "እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው።"

                                                         (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥15)

ዛሬ ይሄ ታላቅ ስጦታ ከሰብአዊነታችን ውስጥ ከነአካቴው ርቆ፤ እንኳንስ ተፈጥሮን ልናበጃትና ልንጠብቃት ይቅርና የራሳችንን የግል ሕይወት ማስተካከልና መጠበቅ ተስኖን ከተፈጠርንበት ኃያል ጸጋ ሸሽተን የምንኖር ድኩማኖች በመሆን ዝምብለን እንገላወዳለን፡፡



tgoop.com/bemaledanek/2390
Create:
Last Update:

ዘላለማዊነትን ከፊደል ትምህርት ሰነዶቿና ፍኖተ ካርታዎቿ፣ ከሥራ መዋቅሯና የመሥሪያ ደንቦቿ፣ ከዜጎች የሕይወት መርህና የአኗኗር ሥርዓት፣ ከቴክሎኖጂ ውጤቶቿና ከምርምር ግኝቶቿ፣ ከፖለቲካዊ መርሆቿና ሕጓቿ አርቃ ያወጣቺው ይህቺ ዓለም፤ የሕያውነትን ኃይል ከብዙ ሰዎች ግንዛቤ ውስጥ አሽሽታዋለች፡፡

ለዘላለም ተፈጥረን ለጊዜዎች እንድንኖር የሚሸብበን የዓለም ወጥመድ ላይ ንቃተ ሕሊና የሌለን አማኞችም፤ በደረስንባቸው የኑሮ ሁኔታዎችና ቆይታዎች ላይ የሚያጋጥሙን ነገሮች ሁሉ ጊዜያዊ ሆነው አረፉ፡፡ አልሆኑም? .. ከደስታም ጊዜያዊ፣ ከእፎይታም ጊዜያዊ፣ ከዕረፍትም ጊዜያዊ፣ ከተስፋም ጊዜያዊ፣ ከጸጋና ከበረከትም ጊዜያዊ፣ ከሞገስና ከማስተዋልም ጊዜያዊ፣ ከጥበብና ከችሎታም ጊዜያዊ ቆይታ ያለን ታይቶ ጠፊዎች አልሆንም?

አዳማዊያን ስንፈጠር ጊዜዎች ወደ ሕይወታችን የሚያመጧቸውን ነገራት ወደ ራሳችን የመኖር ውህደትና የመስመር ስምምነት ከማምጣታችን በፊት 'ምን መጣ?' የሚለውን ለማጥለል እንድንችል፤ ከመጣው ጉዳይ አሊያ አጋጣሚ መካከል ክፋትን ለይተን፥ መልካሙን አስቀርተን፤ አንጥረን፤ እንጠቀም ዘንድ አእምሮ ከግራ ቀኝ የማጤኛ ልቦና ጋራ ታድለን የነበረን ቢሆንም፤ ሰዎች ዛሬ ከተሰጣቸው በታች የሚኖሩ ሲሆን፤ ጊዜ እንዳመጣው የሚመጡ፣ ጊዜ እንደሚወስደው የሚሄዱ እየሆኑ፤ ወደ ዓለም በጊዜ እንደመጡ ከዓለምም ተለይተው በጊዜያቸው ይሄዳሉ፡፡ የዘላለም ሕይወት ከውስጣችን የሚጀምርበት የእምነት ጥበብ ስለጠፋን፤ ጊዜ ጀምሮ፤ ጊዜ እንዳደረገን አድርጎ፤ ጊዜ ይጨርስናል፡፡ በዕድሜያችን ጊዜዎች መካከል ልዩ ማንነታችንን ሳንፈልገውና አግኘተን ሳንጠቀምበት፤ ጊዜው ለኛ የሚስማማውን እንዲያቆይልን፥ የማይጠቅምንን እንዲወስድልን በመንፈሳዊ ኃይል ሳንቆጣጠረው፤ ሳንሞት በጊዜዎች ውስጥ በኑሮ ሞተን ደግሞ እንደገና በአካል የምንሞትበት ጊዜ ሲደርስ ወደ መቃብር እንሸኛለን፡፡

ዮሐንስ 6፥27 ላይ "ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና" ይላል፡፡ ለሚጠፋ መብል አትሥሩ ተብለን ግን ለዕለት እንጀራ ብቻ ስንባዝን ዕድሜያችን ሄደ፡፡ እንጀራ ብቻ ስናሳድድ፥ ሥጋችንም በዛው እንደ ባሕሪዩ ከነፍሳችን ርቆ ተሰደደ፡፡ በየቀኑ ለእንጀራ ኑሮ ብቻ የምንወጣ የምንገባ ፍጡሮች ሆነን፤ ሌሎች መንፈሳዊ እውነታዎችና ሰማያዊ ሚስጢሮች ከጉያችንም ሆነው እየተሸሸጉብን፤ የሕይወትን በረከት ያዝነው ስንል እያመለጠን፣ ልናድግ ነው ስል እየደከምን፣ ልናርፍ ነው ስንል ተጨማሪ እየሮጥን፣ ተረጋጋን ስንል አዲስ ችግር እያስጨነቀን፤ አልባረክ ባለ ጊዜ ውስጥ አልበረክት ያለ ዘመንን ተሸክመን ተቸገርን፡፡ አልፎም ተርፎ የመኖር ወዝ ተሟጥጦ እስከሚደበዝዝብን ድረስ ተፈተንን፡፡ አየህ? ለምድር እንጀራ ብቻ የመሮጥን ውጤት? የምድርን እንጀራ፣ የምድርን መብል፣ የምድርን ምቾት ፍለጋ ስትሮጥ መንገዱ ማለቂያ አይኖረውም፡፡ አጋመስኩት ብትል ዞረህ ከተነሣህበት ጅማሮ ላይ ትመለሳለህ፡፡ ደረስኩበት ብትል የሚቀርህን አስበህ በአእምሮም በአካልም አንድ ጊዜ ትዝላለህ፡፡ እንደዚህ ነው የሚለው በቃ "ለሚጠፋ መብል አትሥሩ!"

እሺ ታዲያ ለምን እንሥራ? ቃሉን መለስ ስናነበው እንደዚህ የሚል ምላሽ ይሰጠናል፤ "ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፡፡" ለዘላለም የሚኖር፡፡ ዛሬ ተበልቶ ነገ የሚርብ መብል አይደለም፡፡ ወሩን ሙሉ ተደክሞበት፣ ከክፉዎች ጋር በመታገል፣ ብዙ በመውጣትና በመድከም የሚመጣ መብል አይደለም፡፡ ይሄ የዘላለም መብል ነው፡፡ እርሱም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደሙ ነው፡፡ ቅዱስ ቁርባን፡፡

የዘላለም ሕይወትን አጥተው የጊዜዎች ሕይወትን ይመሩ ዘንድ ሰዎች እንዳይገደዱ አምላክ ሰው ሆኖ የዘላለም ቃሉን አሰማን፡፡ "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው" አለን፡፡

የክርስቶስን ሥጋና ደም መውሰድ ስንጀምር፤ ሥጋችን ከነፍስ ፈቃዳችን ጋር ተናብቦ ጉዞውን ወደ ሰባተኛው የዕረፍት ቀን ስለሚያቀናው፤ የእኛ እና የዓለም ጊዜዎች ቅርጻቸውን ወደ ዘላለማዊነት እየቀየሩ እየቀየሩ ይመጣሉ፡፡ የዕድሜ ሰዓቶቻችንና የምንኖርበት ዘመን ሰዓቶች ቅጽበታዊ የሆነ ኲነታቸውን እየለቀቁ ሊቆይ የሚችለውን፥ ሊጸና የሚችለውን ለማምጣት ሲሉ መሄድ ይጀምራሉ፡፡ ቅዱስ ቁርባን ስንወስድ ዘላለማዊነትን መኖር የምንጀምረው በሚከተሉት ሁለት ውስጣዊና ውጪያዊ መንገዶች ነው፡፡

በአንደኛው፥ እግዚአብሔር አምላክ ከምድር አፈር አበጅቶን ሰው ሊያደረገን ሕያው እስትንፋሱን ነፍስ አድርጎ በውስጣችን ሲያኖራት፤ ከውጪ የምንቀበለው የእግዚአብሔር አምላክ ሕያው ሥጋውና ሕያው ደሙ ለነፍሳችን ምግብና መጠጥ ይሆንላታል፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን የሕይወትህ ክፍል በሚሆንበት ጊዜ ዘላለማዊነት ከነፍስህ ውስጥ ስለሚጀምርና እየገዘፈ እየገዘፈ ስለሚመጣ ውስጣዊ ሕይወትህ ዝም ይላል፡፡

ዝምታው የሐዘን፣ የመቆዘም፣ የመባዘንና የመቆራመድ ሳይሆን የመረጋጋት ዝምታ ነው፡፡ የእፎይታ ዝምታ ከውስጥ በኩል በጥልቀት ይሰማሃል፡፡ ቢሆንም ባይሆንም ላንተ ምንም የማይሞቅ የማይበርድ አይነት ሆኖ ማዕበል ቢመታው የማይናወጽ እንደ ሐይቅ ጠለል በዝግታ የሚንሸዋሸው ዝምታ ከውስጥ ይሰማሃል፡፡ ከውስጥህ ያለው በሥጋና ደሙ መቀደስ በኩል የመጣው የዘላለማዊነትን መንፈስ ያዘለ ዝምታ፤ ብትታመም የማይደነግጥ፣ ብታጣ የማይሰጋ፣ ብትራብ የማይጨነቅ፣ ቢሞላልህ የማይፈነጥዝ፣ ቢተረፈረፍህ የማይኮፍስ፣ ብትጠግብ የማይወጣጠር ሰው አድርጎ ይቀርጽሃል፡፡ ቢመችህም ባይመችህም ዘወትር የውስጥ መደላደልና የማይሸበር ጸጥታ ያለው ሰው ትሆናለህ፡፡

ሁለተኛው፤ ሥጋና ደሙን በተደጋጋሚ በመቀበል የሕይወት ልምድ ውስጥ ሰውነትህን ስትቀድሰው ተፈጥሮ ወዳንተ እያዘነበለ፤ ላንተ እየታዘዘ፣ አንተን እያገዘ፣ የምትለውን እየሰማህ የምትኖርበትን ዘላለማዊነት ከውጪ ባለው ገጽታ በሚታይ እውነት ውስጥ ይገልጥልሃል፡፡

እግዚአብሔር ተፈጥሮን አንጾና አስተካክሎ ከፍጥረታት ጋር ሲያኖራት፤ የሰው ልጆችን እንደ አባትነቱ በፍጹም ፍቅሩ ለይቶ ሲፈጥር በነፍስ ሥልጣንነት በኩል እግዚአብሔርነት አካፍሎናልና ተፈጥሮ እንድታገለግለን ፍጥረታትን እንድንገዛ አክብሮ ቀረጸን፡፡ (ኦሪት ዘፍጥረት 1፥28)
   
ይሄ ድንቅ ነገር ነው፡፡ የምድር ፍጥረታትን ሁሉ በየወገን ወገናቸውና በየነገድ ነገዳቸው ካበጃቸው በኋላ ስም የማውጣት ኃላፊነት ለሰው ልጅ ተሰጠው፡፡ አዳምም ለእንስሳትና ፍጡራኑ ሁሉ ስም ሲሰጣቸው፤ ስማቸውም ጸድቆላቸው እንዲታዘዙትና እንዲያገልግሉት ሆኑ፡፡ በፍጥረታቱም ሳያበቃ ተፈጥሮን አዳም እንዳሻው እንዲያበጃትና እንዲጠብቃት ተሰጠቺው፡፡

     "እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው።"

                                                         (ኦሪት ዘፍጥረት 2፥15)

ዛሬ ይሄ ታላቅ ስጦታ ከሰብአዊነታችን ውስጥ ከነአካቴው ርቆ፤ እንኳንስ ተፈጥሮን ልናበጃትና ልንጠብቃት ይቅርና የራሳችንን የግል ሕይወት ማስተካከልና መጠበቅ ተስኖን ከተፈጠርንበት ኃያል ጸጋ ሸሽተን የምንኖር ድኩማኖች በመሆን ዝምብለን እንገላወዳለን፡፡

BY በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪


Share with your friend now:
tgoop.com/bemaledanek/2390

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to build a private or public channel on Telegram? Those being doxxed include outgoing Chief Executive Carrie Lam Cheng Yuet-ngor, Chung and police assistant commissioner Joe Chan Tung, who heads police's cyber security and technology crime bureau. Telegram offers a powerful toolset that allows businesses to create and manage channels, groups, and bots to broadcast messages, engage in conversations, and offer reliable customer support via bots. So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. Write your hashtags in the language of your target audience.
from us


Telegram በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
FROM American