Telegram Web
ኢስራእ ወልሚዕራጅ የመጨረሻ ክፍል
"የመካ ሠዎች ዜናውን ሰሙ"

ጧት ነቢዩ [ﷺ] ከአቡ ጀህል ጋር ተገናኙ ፣ አቡ ጀህልም በሹፈት መልክ " እህሳ ሙሐመድ ዛሬስ ምን አዲስ የገር አለክ ? " በማለት ጠየቀ ፣ ነቢዩም [ﷺ] " አዎን ! በዛሬዋ ሌሊት በይተል መቅዲስ ሄጄ ነበር " አሉት ፣ አቡ ጀህልም በመገረም  " ከዛን ደም በእኛው መሀል ሆነህ አነጋህ ማለት ነው ? " አላቸው  "አዎን" አሉት የአሏህ መልዕክተኛ ፣ አቡጀህልም " እና ሠዎችን ብሰበስብ የነገርከኝን ትነግራቸዋለህ ? "  አለ ፣ አዎን አሉት ፣
አቡጀህልም " እናንተ የከዕብ እብኑ ሉአይ ልጆች ሆይ ! " በማለት ጮሆ ተጣራ ፣ ሠዎች ሲሰበሰቡም ነቢዩ [ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም] ስለ ጉዞው ነገሯቸው ፣ ጣኦታዊያኑ በዜናው በመገረም እጃቸውን በጭንቅላታቸው ላይ ጫኑ ፣ ሌሎች ተዐምራቶችን እንዳስተባበሉት ሁሉ ይህንንም አስተባበሉ ፣ ስለ በይተል መቅዲስ ገፅታና በጉዞአቸው ላይ ስለተመለከቷቸው የንግድ ቅፍለቶቻቸው ግልፅ ያለ መረጃ ቢሰጧቸውም ከሀዲያኑ ግን በክህደታቸው ላይ ተማምለው ነበርና አምነው ሊቀበሉ አልቻሉም ።
ከፊል ሠዎች ወደ ሰይዱና አቡበክር ረዐ ዘንድ በመሄድ " ጓደኛህ በዚህች ሌሊት ወደ በይተል መቅዲስ ሄጄ መጣሁ እያለ ነው " በማለት ወሬውን አደረሷቸው ፣ ሰይዱና አቡበክርም ረዐ " እርሱ ይህን ካለ ትክክል ነው ማለት ነው " እኔ ከዚህ ሩቅ በሆነ በጧትና ማታ የሚመጣለት የሰማይ ወሬ እያመንኩት በዚህች እንዴት አላምነውም ? " በማለት መለሱ ፣ በዚህም «አስ-ሲዲቅ» በጣም ዕውነተኛው በሚል የክብር ቅጥያ ስም ለመሠየም በቁ ።
2👍2
إِنَّا لِلّهِ وَإِنَّـا إِلَيْهِ رَاجِعونَ

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን😭😭😭

ማዲሁ ሙሀመድ ሰዒድ ወደ አኼራ ተሻግሯል።
ሀሪማ ቲቪ ለዘመድ ወዳጅ በሙሉ ሰብሩን አላህ ይስጣቹህ ይላል!!🤲

بسم الله الرحمن الرحيم
ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ٱلرَّحۡمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ مَٰلِكِ يَوۡمِ ٱلدِّينِ
إِيَّاكَ نَعۡبُدُ وَإِيَّاكَ نَسۡتَعِينُ ٱهۡدِنَا
ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنۡعَمۡتَ
عَلَيۡهِمۡ غَيۡرِ ٱلۡمَغۡضُوبِ عَلَيۡهِمۡ
وَلَا ٱلضَّآلِّينَ
አሚን🤲🤲🤲
2025/07/14 04:36:14
Back to Top
HTML Embed Code: