Telegram Web
(በላይ በቀለ ወያ)
@ethio_poem


እኔ ላንቺ ብዬ
ባልሽን ገድዬ ፣
አብሬሽ ስተኛ
እኔን ሊያስወነጅል ፣ ባልሸ ሞቶ ቀረ
እሱ ላንቺ ብሎ...
እኔ እየገደልኩት ፣ ባይሞት ምን ነበረ
ባይወድሽ ነው እንጂ...
ሲገድሉት አይሞትም ፣ የእውነት ያፈቀረ፡፡

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
አልወዳትም እንጂ አልጠላትም .....#3

(ሜሪ ፈለቀ)

.
.
እንድትሞት በጭራሽ አልፈልግም ነበር:: ስለምወዳት አይደለም !!!.... በቁሟ ልበልጣት .... ላሸንፋት ነበር ትግሌ ..... ሞቷማ ኪሳራዬ ነው::

የሞቷ ቀን ማታ በሬን አንኳኳች ........ ደፈራርሰው ያበጡ ዓይኖቿ .... የተንጨባረረው ፀጉሯ ....የሚንቀጠቀጡ እግሮቿ ... የሆነ ነገር እንደተፈጠረ ገባኝ::

"ትዳሬን? ኤዱዬ ፍቅሬን? እንዴት እንደምወደው እያወቅሽ? ምን ብበድልሽ ነው እንዲህ የከፋሽብኝ? እስኪ ንገሪኝ እኔ ምንድነው ያደረግኩሽ?" ከንፈሯ ይንቀጠቀጣል..... እንባዋ ይከታተላል ..... አሳዘነችኝ .... ማታ አልጋቸው ላይ ሲዋደቁ የእኔን ስም እንደጠራባት ነገረችኝ ... ፈገግታዬ አመለጠኝ::

"ይሄን ነው prove ማድረግ የፈለግሽው? ከኔ የተሻልሽ መሆንሽን ከባሌ ጋር ተኝተሽ ነው ማረጋገጥ የምትፈልጊው?" እየተናደደች መጣች ..." .... ጤነኛ አይደለሽም ..... ይሄ በሽታ ነው!..... " ደሞ ምልስ ትልና አሳዛኝ ትሆናለች ... "እንዴት ክፉ ነሽ ግን በማሪያም?...." ኩርምት ብላ ትንሰቀሰቃለች ........

ዝም ብዬ እሰማታለሁ:: .... ስታለቅስ... ምን ያህል ክፉ ሴት እንደሆንኩ ቃላት እየቀያየረች ስትነግረኝ... ስትናደድ ... አንድ ሰዓት ያህል ዝም ብዬ ሰማኃት ...

ለምንድነው የመሸነፍ እንጂ የድል ስሜት የማይሰማኝ ታዲያ? ..... በክፋት መብለጥ የለም ይሆናል....

"ታውቂያለሽ ወንድምሽ ከደፈረኝ በኃላ አብሬው የተኛሁት ወንድ ባልሽ ነው!!" አልኳት .... (አታውቅም... እንደማታውቅም አውቃለሁ:: .... ፊቷ የሆነ ነገር የፈነዳበት ይመስል ተመሰቃቀለ::)

"ቤተሰቦችሽ እኔ ለተደፈርኩት ... እህትሽ ከሰማች ትጎዳለች ... እንዳትሰማ ብለው ተጠነቀቁልሽ:: ... አስበሽዋል? እኔ እሳት ውስጥ ሆኜ እየነደድኩ .... ሙቀቱ አንቺን እንዳይነካሽ እየከሰልኩ ዝምም ጭጭጭጭ ብዬ ስነድ?"

ዝም አለች:: ክው ብላ ደርቃ ከአፌ የሚወጡት ቃላት የሆኑ የሞት ፍላፃዎች ይመስሉ እየተንቀጠቀጠች ትጠብቃቸዋለች .....

ሁሌም እንደዛ ነበር ... የሆነ የተረገመ ቀን እቤታችን የመጣች እንግዳ

"በስመአብ ቁልጭ እናትሽ አይደል እንዴ? ነፍሷን ይማረው ፀጉሯን እንዲህ ማስያዝ ትወድ ነበር እሷም!" ብላ የማውቅ የመሰላትን ቦንብ ከማፈንዳቷ ቀን በፊት

'ውይ ልጄ ደረቅ ዳቦ አትወድምኮ' ተብሎ እኔ ደረቅ ዳቦ ስበላ ለእህቴ እንቁላል መሰራቱን በክፉ ተርጉሜው አላውቅም ነበር::

'እሷ ጎበዝ ተማሪ ስለሆነች' ተብሎ እሷ የግል ትምህርት ቤት ስትማር እኔ የመንግስት መማሬን ጉብዝናዋ የሰጣት ሽልማት ነው ብዬ ከማሰብ ዘልዬ አላውቅም....

'እሷ ቆንጆ ስለሆነች ጎረምሳ አያስኬዳትም' በሚል የሚያመላልሳት መኪና ሲከራዩላት ... እኔ ጥፍጥፍ መሆኔን አምኜ ከሷ ትምህርት ቤት የሚርቅ ትምህርት ቤቴን መንገድ በእግሬ እየፈጨሁ ለእህቴ ጥበቃ ከመደሰት ያለፈ የተሰማኝ አልነበረም::

እህቴ ናታ.... በመልክም በባህሪም በጭራሽ የማንመሳሰል መንታ እህቴ ....

"እናቴ ማናት?" ብዬ ጎፈላሁ እንግዳዋ ከሄደች በኃላ ..... 13 ዓመቴ ነው:: እናቴ(አሳዳጊዬ) እህቴ እንዳትሰማ እሽሽሽሽ አስብላኝ

"ይሄን ነገር ግን በፍፁም እህትሽ እንዳትሰማ... እንዴት እንደምትወድሽ ታውቂያለሽ አይደል? ቃል ግቢልኝ በፍፁም ለእህትሽ እንዳትነግርያት .... " ብላ መርዶዬን ነገረችኝ .... እናቴ የኛን ቤት ተከራይታ የምትኖር የቡና ቤት ሴት እንደነበረችና እኔን ስትወልድ እንደሞተች ነገረችኝ .....

አሳዳጊዎቼ ልጅ የመውለድ ተስፋቸው ባዶ መሆኑን በዶክተርም በጥበቃ ብዛትም ባረጋገጡበት ወቅት የእኔ እናት እንደ ተዓምር ከማን እንዳረገዘች የማታውቀውን ልጅ ልታስወርድ ዱብ ዱብ ስትል ነው አሳዳጊዎቼ በደስታ እኔን ሊያሳድጉኝ ቃል ገብተውላት እናቴ የወለደችኝ .... ቆይ ....!!!! እህቴ ከእኔ ጋር ግብ ግብ የጀመረችው ገና ሳላውቃት
ሳታውቀኝ ... በእናቴ ሆድ ሆኜ ነው...

ለዓመታት ልጅ አልሸከም ያለው የአሳዳጊዬ ማህፀን ልክ እናቴ ሆድ እኔ መደላደል ስጀምር እህቴን ቋጠረ:: .... ውድድሩ ተጀመረ....

"በቃ አሁን የራሳችንን ልጅ ስላገኘን ልጅሽን የማሳደግ ፍላጎታችንን ትተነዋል" ብለዋት እንደነበር አድጌ ያቺ እንግዳ ናት የምትነግረኝ ... እናቴ በማላውቀው ምክንያት ልትወልደኝ ወሰነች.... ስትወልደኝ ሞተች:: አሳዝኛቸው.... ወይም ልውሰዳት ያለ ዘመድ ስለጠፋ... አልያም እግዜሩን ፈርተው ለፅድቅ ትሆነናለች ብለው ... አላውቅም:: ወሰዱኝ...... በወሩ እህቴ .... መንታዬ ተወለደች::

ቤተሰብ ያጣሁት እኔ .... የኖርኩት ህይወት ሁሉ እንክትክት ብሎ የውሸት ካብ ሆኖ የተናደብኝ እኔ .... የተዋሸሁት እኔ .... "እሷ ከሰማች ይከፋታል..." ተብሎ የምትጠበቀው እሷ ....

"ለምን አልነገርሽኝም? እንዲህ ሁሉ ስትሆኚ ምናለ ብትነግሪኝ? ይሄ ጅብ እንዴት እህቱ ላይ እንዲህ ያደርጋል?" አለችኝ መልሳ ወንድሜ የምትለው የአጎቷ ልጅ ከጏደኞቹጋ ያደረገኝን ስነግራት ... ባሏን እንዳባለግኩባት ረስታው አቅፋኝ ለእኔ መንገብገብ ጀመረች .....

"ቤተሰቦችሽ ሁሉም ነገር በደም ካልተገመደ ዋጋው አይታያቸውም ..... በደም ስለማንገናኝ እህቱ አልነበርኩም ..... ደም ስላልፈሰሰኝ ደፈረኝ እንዳልል ዝም አስባሉኝ .... ስህተት ነው ተባለለት .... ድሮም የጀመረችው ነው ተባለና የሱን አውሬነት በእኔ ጥፋት ከደኑለት ..... እሽሽሽሽሽሽ ዝም በይ ተባልኩ::"

አሁንም ልክ እንደ ቅድሙ መንሰቅሰቅ ጀመረች .....

"በህይወቴ አንድ ነገር ይሁንልሽ ብሎ ፈጣሪ ቢጠይቀኝ ምን እንደምሻ ታውቂያለሽ?" አልኳት ....

"ምንድነው?" አለችኝ ማድረግ የምትችለው ነገር ቢሆን አሁኑኑ የምታሳካልኝ በሚመስል ጉጉት

"አንቺን እንዲያደርገኝ .... አንቺን መሆን"

ዝምምምምም አለች::..... አሳዘንኳት .... ዝምምምም አለች .....

"እሺ እኔ ምን ላድርግ? እነአባቢን ልጣላቸው? ያ ደስ ይልሻል? ወይም እኔን እንደሚወዱኝ እንዲወዱሽ ልንገራቸው? ስራ ልተው? ስራ ባይኖረኝ ደስ ይልሻል? አብርሽን ብቻ ተይልኝ አትበይኝ .... እሱን አልችልም.... ኤዱዬ እሱን ከራሴ በላይ እወደዋለሁ:: ሌላ የፈለግሽውን ላድርግልሽ እንዳሸነፍሽኝ ከተሰማሽ..." አለችኝ ..........

አዎ በክፋት አይበለጥም ......... ይኸው አሁንም በዝረራ አሸነፈችኝ ....

"ውጪልኝ!!" አልኳት በቀስታ ..... "ውጪልኝ .... ከህይወቴም ከቤቴም ውጪልኝ ... " እያልኳት ለራሴ 'በቃኝ' እላለሁ ..... ርቄ እሄዳለሁ ... ሁላቸውንም የማላይበት .... ሁሉንም ከኃላዬ ጥዬ ብንንንንንን ብዬ እሄዳለሁ ....

......... አልጨረስንም ..........

(ሜሪ ፈለቀ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
አልወዳትም እንጂ አልጠላትም.....#4

(ሜሪ ፈለቀ)
@ethio_poem
.
.
'ከቤቴ ውጪልኝ' የሚለውን ዘላ 'ከህይወቴ ውጪልኝ' ያልኳትን ሰምታኝ መሰለኝ....... የሞተችው......

"ኤዱዬ የኔ ከህይወትሽም ከቤትሽም መውጣት አንቺን አያስተካክልሽም!! Let us make this right!! ላግዝሽ?" አለችኝ ....

"የቱን? የቱን ነው የምናስተካክለው?" አልኳት "ያንቺ እህት አለመሆኔን? ንገሪኝ ከየት እንጀምር? ገና ሳልወለድ ቤተሰቦችሽ ከከዱኝ? ወይስ ለ13 ዓመት እማ አባ ያልኳቸው ቤተሰቦቼ ሳይሆኑ የወለደችኝ ሌላ ሴት መሆኗን እንዴት ነው የምናርመው? ከየት እንጀምር ንገሪኝ? .... ጥፋት ሳጠፋ 'ዘር ከግንዱ ይመዘዛል' እየተባልኩ .... በራሴ መንገድ ስጏዝ 'እንደእህትሽ ብትሆኚ ምናለ?' እየተባልኩ ማደጌን ምኑጋ እናቅናው ?" ......

እንዲህ ለማንም አውርቼ አላውቅም.... የተሰማኝን ህመም ሁሉ መዋጥ እንዳለብኝ ተነግሮኝ ነው ያደግኩት.... ጭጭ... እሽሽሽሽሽ ተብዬ ... እየታመሙ መሳቅ ለምጄ ነው ያደግኩት ....

"ወንድሜ ስለው ያደግኩት ወንድ ከጏደኞቹ ጋር የደፈረኝን ምኑጋ እናቅናው እህቴ? ንገሪኝ ?.... እኔ .... እኔ መቃናት አልችልም!! .... የእኔ ህይወት የቱምጋ አይቃናም!! .. "

"ወደኃላ ተመልሶ ቢቃና .... ሀ ብዬ ሌላ ሰው ሆኜ መፈጠር ነው የምፈልገው.... ያንቺ እህት ሳልባል... አንቺ በምታገኚው ፍቅር ሳልቀና ... ባንቺ ጉብዝና ራሴን ሳልለካ.... እንዳንቺ ቆንጆ ለመሆን ሳልመኝ.... ባጠቃላይ ካንቺ ሳያወዳድሩኝ 'እኔን' የሚወዱኝ ቤተሰቦች ልጅ ሆኜ መፈጠር ነው የምፈልገው ..... ክፉ ... ቀናተኛ ... ሳልሆን ...."

ከተቀመጠችበት ሳትነሳ ብዙ ቆየች.... እኔ ህመሜን ብዙ አወራሁ .... ከቤቴ ስትወጣ ....

የኔን ሸክም ሲደመር የጥፋተኝነት ስሜት ሲደመር ባሏ ከእህቷጋ የባለገባት ሚስት የልብ ስብራት ... ይሄን ሁሉ ተሸክማ ከአንገቷ አቀርቅራ .... የጎበጠች መሰለኝ ...

"ኤድዬ ህመምሽን ስላልታመምኩልሽ ይቅርታ!!" ብላኝ ወጣች .... እኔ 30 ዓመት ቀስ በቀስ የጠጣሁትን ጎምዛዛ ክፋትና በደል ... በአንድ ቀን ጋትኳት .... ከበዳት!!
....
.....
...

የቀብር ቦታው ላይ ሬሳዋን ወደ ጉድጏዱ ሲነዱት እያየሁ ...ምናለ አቅፌያት ቢሆን? 'ያንቺ ጥፋት አይደለም' ብያት ቢሆን? ምናለ ዝም ብዬስ ቢሆን? .... ምናለ..... ምናለ.... እያልኩ እንሰቀሰቃለሁ:: .....
.....
.....

ከቤቴ ከወጣች በኃላ ለሰዓታት ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ስልኬ ጠራ!!

"እህትሽ አርፋለች!"

ምንም አልጠየቅኩም:: እስከአሁንም ድረስ የደወለልኝ ማን እንደሆነ አላውቅም:: ... ስልኩንም ከዘጋሁ በኃላ ለሰዓታት እዛው ተቀመጥኩ:: ድጋሚ ስልኬ ጠራ:: ጏደኛዋ ናት::

"ኤዱ የት ነሽ?" አለችኝ በማልቀስ በሻከረ ድምፅ .... 'እንዴት እህትሽ ሞታ ለቅሶ ቦታ የለሽም' የሚል ድምፀት ባለው ቃና

"ምን ሆና ነው?" የሚል ጥያቄ ነው ከአፌ የወጣው....

"ወየው ጉዴ አልሰማሽም? (ለቅሶ አስከትላ) ምን እንዳጋጠማት ምን አውቄ? ራሷን ነው ያጠፋችው::" አለችኝ ...... ስልኩን ዘጋሁት .... እስኪነጋ ከተቀመጥኩበት አልተነሳሁም:: ..... ፀሀይዋ ብቅ ስትል ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ለቅሶዋ ላይ ተገኘሁ:: ስገባ ነጠላ ትከሻዬ ላይ አደረጉልኝ.... ምፅ ምፅ እያሉ ደግፈው ወንበር ላይ አስቀመጡኝ ...... ግራ ገባኝ ....

ሲያፈጡብኝ አለቅሳለሁ .... እንባዬ ይተባበረኛል ..... እስከቀብሯ ቀን ድረስ ሲያለቅሱ ከማልቀስ .... ሲያፈጡብኝ 'ጨካኝ' ላለመባል አይኔን ከማስጨነቅ ያለፈ የሚሰማኝንም ስሜት ለይቼ አላወቅኩትም::

አፈሩን ሲያለብሷት ልቤን ሞት ተጫነው:: ዝም ጭጭ .... ያለ ስሜት ተሰማኝ:: አብሬያት ጉድጏድ ውስጥ የገባሁ ስሜት .... አፈሩ እኔ ላይ የሚጫን ስሜት .... ራሴን ልስት አይነት ስሜት ይሰማኝና ተስተካክዬ ለመቆም እሞክራለሁ .. .... የሚሰማኝ ዝምታ ብቻ ሆነ ... ከዛ .... ጨለማ!!!!

እንደሞት ያለ ጨለማ ........

"ምን ሆኜ ነው?" አልኩኝ አይኖቼን ስገልጥ ሆስፒታል እንዳለሁ ገብቶኝ:: ...... አጠገቤ የእህቴ ጏደኛ እና እናቴ (አሳዳጊዬ) ነበሩ:;

"ቀብር ቦታ ራስሽን ስተሽ ነው" አለችኝ ጏደኛዋ .... ፊታቸው ላይ የሆነ የጉጉት ስሜት አየሁ..... ስለነቃሁ የመደሰት ግን ያስደሰታቸው መንቃቴ ብቻ ሳይሆን ሌላ ነገር እንዳለ ገባኝ

"ምንድነው?" አልኩኝ ወደ እናቴ ዞሬ ..... ከአፌ
እስኪወጣ ስትጠብቀው የቆየ ቃል ይመስል ቅብል አድርጋ

"ምን ማለቷ ነው? ምንድነው?" ብላ የሆነ ፖስታ ሰጠችኝ

"ምንድነው?" አልኩ እየተቀበልኩኝ

"እህትሽ ከመሞቷ በፊት ያስቀመጠችልሽ ደብዳቤ ነው! ምን ማለቷ ነው? ከሁላችን መርጣ ለምንድነው ላንቺ የፃፈችው? የፃፈችው ምኑን አልገባኝም!" አለችኝ

"ለእኔ ከሆነ የተፃፈው ለምን አነበባችሁት?" አልኩኝ ፖስታው ላይ ለኤደን ብቻ የሚል ፅሁፍ እያየሁ .,,......

.......... አልጨረስንም............

(ሜሪ ፈለቀ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
እስከዛሬ ድረስ...
@ethio_poem

(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
.
ስኳር ስኳር ለሚል ፣ እድሜ ላንቺ ከንፈር
ስኳር ጠፋ ብዬ ፣ አልጮሁም እንዳገር፡፡
አንዴ ስትስሚኝ..
አንድሺ ቶን ስኳር ፣ ትለግሺኝ ነበር፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ዛሬ ግን ስትስሚኝ...
ስኳር ስኳር የሚል ፣
የከንፈርሽ ጠአም ፣ ጠፍቶብኛል ውዴ
እስቲ ልጠይቅሽ...
አንቺም ለኬንያ ፣ ተሽጠሻል እንዴ?
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
(በላይ በቀለ ወያ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
……ህልሜን አደራ!
(በውቀቱ ስዩም)

@ethio_poem
.
.
ባይመረመሬ ፥ ጥበብ ተሽከርክሮ
ከወርቃማ ብርሃን ፥ ከብርማ ፀዳል
የተሰራ ሸማ ፥ ማግኘት ብችል ኖሮ
ከውብ እግሮችሽ ስር ፥ እዘረጋው ነበር
ግና ምንም የለኝ ፥ ከህልሞቼ በቀር፤
:
የኔ ውድ እንግዲህ
ህልሜን እግሮችሽ ስር ፥ ከዘረጋሁ ወዲህ
ዝግ ብለሽ እርገጪ ፥ ዝግ ብለሽ ሂጂ
ህልሜ ላይ ነውና ፥ የምትራመጂ።

የማለዳ ድባብ

(በእውቀቱ ስዩም)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
አልወዳትም እንጂ አልጠላትም ....#5
(የመጨረሻ ክፍል)

(ሜሪ ፈለቀ)

@ethio_poem
.
.
"ኤደን ምን ይሰማሻል?"

"ምንም"
(ዝም ተባብለን ሰዓቴ አልቆ እመለሳለሁ::)

በሌላኛው ቀንም ........

"ኤደን ዛሬስ ለማውራት ዝግጁ ነሽ?"

"አይደለሁም!! ማውራት አልፈልግም!"
(ዝምምምምም..... ሰዓቱ ያልቃል)

ደግሞ በሌላኛውም ቀን

"ኤደን ዛሬስ ለመጀመር ዝግጁ ነሽ?"

"ምኑን?"

" ማውራት ትፈልጊያለሽ?"

"እኔ ምንም የማድረግ ፍላጎት የለኝም!!"

(የምፈልገው አንድና አንድ ነገር .... የቀብሯ ቀን ጭልጥ አድርጎ የወሰደኝ ጨለማ ለዘለዓለሙ እንዲወስደኝ ነው)

በሌላኛው ቀን አልጠየቀኝም:: ገብቼ ስቀመጥ ሰላምታ ሰጥቶኝ ዝም አለ::

"ዛሬ አትጠይቀኝም እንዴ?"

"ምኑን?"

"ዝግጁ መሆን አለመሆኔን?"

"ነሽ?"

"አይደለሁም!"

"ጥሩ!! ዝግጁ እስክትሆኚ ድረስ የሚሰማሽ እዚህ መጥቶ መቀመጡ ከሆነ ዝም በይ... ማውራት ሲሰማሽ አውሪ.... ማልቀስ ሲሰማሽ አልቅሺ.... መጮህ ሲሰማሽ ጩሂ ..... ሰዎች ሀዘናቸውን በተለያያየ መንገድ ነው የሚያስተናግዱት.... የተለያየ ጊዜ ይወስድባቸዋል::"

"ሀዘን አይደለም የሚሰማኝ!!"

"እሺ!! ምንድነው የሚሰማሽ?"

"ምንም!!! ዝም ... ፀጥ .... ያለ ስሜት!!"

ለብዙ ቀናት ተመላለስኩ .... እሄዳለሁ:: እቀመጣለሁ:: ሰዓቴ ያልቃል:: እመለሳለሁ::

"ዛሬ አሻንጉሊትሽን የት ትተሻት መጣሽ?" አለኝ

"ሰጥቻት መጣሁ:: ..... 'ያውልሽ' ብዬ መቃብሯ ላይ ወርውሬላት መጣሁ:: ትውሰደው .... " እንባዬ ከወራት በኃላ ላስቆመው እንዳልችል ሆኖ ይንጠኝ ገባ ...... ማልቀስ ማቆም እፈልጋለሁ:: .. አቃተኝ.... የቀብሯ ቀን እንደሆነው ራሴን የምስት መሰለኝ .... ጨለማው ናፈቀኝ... ግን አልመጣም... አልወሰደኝም.... ደብዳቤዋን ከኪሴ አውጥቼ ሰጠሁት::

"አየህ በዝህች ሁለት መስመር ደብዳቤ እንዳልሞትም እንዳልኖርም አስራኝ ሞተች:: አንብበውማ! ጮክ ብለህ አንብበው!!"

" አንቺ ደግሞ በተራሽ የእኔንም ደርበሽ ኑሪልኝ:: የከፈልኩትን ዋጋ እንዳታከስሪኝ .... ደስ ተሰኝተሽ ኑሪና ዋጋዬን ክፈዪ!! .... ፖኒን ትቼልሻለሁ::" ጮክ ብሎ አነበበው .... ቤተሰቦቻችን እንዳልገባቸው ሁሉ እሱም አልገባውም..... የሆነው ሳይገባቸው ነው 'ጭንቅላቷ ተቃውሷል' ብለው ሳይካትሪስት የቀጠሩልኝ....

"ፖኒ ያቺ አሻንጉሊት ናት!" እንደገባው ራሱን ነቀነቀ.... "በጣም ልጅ ሆነን ለሁለት አንድ አሻንጉሊት ተገዛልን:: እሷ ስም አወጣችላት:: አልተቃወምኩም:: .... የሆነ ቀን እኔ ስጫወት ደርሳ ካልወሰድኩ አለች ... ተደባደብን ... አባታችን መጥቶ አሻንጉሊቷን ከእኔ ቀምቶ ለሷ ሰጣት ... ቀን ቀን በአሻንጉሊቷ መጫወት የምትችለው እሷ መሆኗን አወጀ:: ከፈለግኩ ማታ እሷ ስትተኛ መጫወት እንደምትችል... ያውም እሷ ከፈቀደችልኝ..... ነገረኝ:: ምርርርርርር ብዬ አለቀስኩ::...... ያስለቀሰኝ ከአባታችን ለሷ ማገዝ በላይ የሷ መደሰት ነበር:: እንዳለመታደል ሆኖ ሁሌም እሷ ስትተኛ ጠብቄ ለመጫወት እቀመጥና እንቅልፍ ቀድሞ ስለሚጥለኝ ያልፈኛል::.... ምን ማለቷ ነው? ስትሞት ትታልኝ የምትሞተው?"

"ምን ማለቷ ይመስልሻል አንቺ?"

"እኔ ምን አውቅላታለሁ? ህይወትሽን የቀማሁሽ እዛጋ ነው ... ከዛ ጀምሪ ማለቷ? ያውልሽ ይስፋሽ ማለቷ? እኔ ምን አውቅላታለሁ ምን አድርጊ እንደምትለኝ? ቆይ እሷ ራሷን እንደክርስቶስ ነው የምታየው? ማነኝ ብላ ነው የምታስበው ህይወቷን ስትሰጠኝ ..... በቃ ሞተችልኝ ብዬ በደስታ የምኖር ነው የመሰላት? ደሞ ቆይ ክርስቶስኮ ለአንድ ሰው አልሞተም .... ለዓለም ህዝብ ነው የሞተው... ክርስቶስ ለአንተ እንደሞተልህ ብታውቅም ስላላመንከው እኔ አሁን የሚሰማኝ አይነት ሸክም አይሰማህም .... ሌላ የሆነ ሰው አምኖ እንደሚያገለግለው ታውቃለህ ... እሷ ምን አስባ ነው ለአንድ ለእኔ ህይወት ከፍላ ... ከዛ በደስታ እንድኖርላት የምትፈልገው? ቆይ የቱጋ ሀ ብዬ መኖር እንድጀምርላት ነው? ቆይ አንተ ስታስበው ጤነኛ ሆኜ ራሱ መኖር የምችል ይመስልሃል?"

"አዎ ይመስለኛል!!"

"እኮ እንዴት?" ..... እስከዛሬ ያላወራሁበትን ሰዓታት ጨምሬ ለፈለፍኩ::

"ራስሽን ይቅር በማለት ትጀምሪያለሽ!!"

"ሌላ 30 ዓመት መኖር ቢሰጥሽም መኖር አትጀምሪም አትለኝም ታዲያ?"

"ሳይኖሩ ከመሞት መኖር ጀምሮ መሞቱ አይሻልም ታዲያ? ...... "
......
.....
"ለራሴ ስል መኖር አልፈልግም..... ለሷ ስል ደግሞ መሞት አልፈልግም"

.....

"ሁለቱን ለማስታረቅ ነው ከራስሽ መታረቅ ያለብሽ..... "

................. ጨርሰናል................

(አላለቀም ብትሉም አልቋል..... አልቋል ብትሉም እንደዛው)

(ሜሪ ፈለቀ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
( ረድኤት ተረፈ )

@ethio_poem
.
.
.
የማይወዳደር እኩያ የሚያጣ
ከልቤ ግርጌ ስር አንዳች ስሜት ወጣ
ተሰማኝ ወደድኩህ ያንተን ጣዕም ለየሁኝ
ቆዳዬ ቀመሰህ ምላሴን ከዳሁኝ

ከየትኛው አካሌ ፍቅርህ የወደቀው
የሚያርበተብተኝ ጥፍሬን የሚነዝረው
አካልስ አለ ወይ የሚታይ ሚቀመስ
ሴትነት ገላዬን ነክቶ ሚያጎለምስ

ንገረኝ አንተዬ ከደጅ እንዳያድር ዳስም ልጣልለት
እንዲህ ያለ ፍቅር አያድርም ከኔ ቤት
በአዳፋዬ ባያድፍ ንፁህ ጥሩ ፍቅርህ
ከቆሸሸ ገላ ከዚህ በድን ይሽሽ

እንዲህ ያለ ልመና ሚዛን አያነሳም
የፍቅር ባህሪ ዙፋንን አይሻም
የት ጋር ነው የሚሰማኝ ምኔን ነው የያዝከው
የት ጋር ነው ያገኘኸኝ ምኔን ነው ያጣኸው
ብቻ ከልቤ ስር ስሜቴ ይፈልቃል
የደረስክበትን ያልደረስክበትን
ረቂቁ ፍቅርህ እሱ ብቻ ያውቃል።

ረድኤት ተረፈ

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethiop_poem
ቀጥረሽኝ....
ፈላስፋ አደረግሽኝ(ርእሱ ነው)
(በላይ በቀለ ወያ)

@ethio_poem
.
.
ላገኝህ ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፣ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፣ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፣ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፣ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሰአቱ እስኪደርስ ፤ ሰአት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፣ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን...
እንዴት እንደምሔድ ፣ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፣ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዴ እግሬን ስጎትት፣ አንዴ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፣ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፣ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፣ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው...
ኒስትሮ ጋ ሔድኩኝ ፣ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው...
በወስፌ መንጠቆው ፣ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፣ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ...
"የህይወት ትንሽ ሽንቁር...
ጊዜና ግመልን ፣ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት ፣
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፣ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣።።፣።፣
እየተጣደፍኩኝ...
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፣ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፣ "ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዲ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፣ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ...
መፈለግ ነው ብዬ ፣ የፍልስፍና አቅም፡፡
፡፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፣ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፣ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፣ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፣ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፣ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ....
ትቼው መጥቻለሁ ፣ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር...
ላይጠግን ይሰፋል ፣ በወስፌ ተቀዶ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜ መጥቼ ፣ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ....
እጅጉን ይሻላል ፣ አርፍዶ የመጣ፡፡
ሰው የሚሉት ፍጡር...
ነፍስ ከስጋ ጋር ፣ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፣ ፍፁም የሚስተው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜሽ መጥቼ ፣ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው ፣ መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፣ ማይጠነቀቀው!!!

(በላይ በቀለ ወያ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
ብሶት የወለደው ወቅታዊ ሆያ ሆዬ
(በላይ በቀለ ወያ)

@ethio_poem
.
.
መጣና በአመቱ
ሰበር ዜና ተመልከቱ
በሎም በሎም ነው
የምንለው
ሆያ ሆዬ ናና
ተንከባለል በጎዳና
ሆያ ሆዬ ጉዴ
ጦርነት ነው ልማዴ
።።።፣
የኢትዮጵያ ህዝቦች /ሆ/ እንደምን ናቹ
ከቆላ ተንቤን / ሆ/ መጣንላቹ
ሆ ስንል አመፅ /ሆ / እንዳይመስላቹ
ሆያ ሆዬ ነው /ሆ/ ምንልላቹ
ሆያ ሆዬ ዝና
ተቆፃፀር ደምስስና
።።
ሆያ ሆዬ /ሆ/ ሆይ የኔ ጌታ /ሆ/ ጌታ ጠንበለል
ድሮኗ መጣች /ሆ/ ወዴት ልጠለል
ምሽጌ ሁሉ /ሆ/ ተደረማምሷል
የዘር ጥላቻ /ሆ/ በአንድነት ፈርሷል
ጉድጓድ ውስጥ ሆኖ /ሆ/ የት ይደረሳል
ሆያ ሆዬ ጉዴ
መፈርጠጥ ነው ልማዴ
ሆያ ሆዬ ናና
እዝ በወሬ ደምስስና
።።
የኛማ አብይ "ሆ/ ጥርሰ በረዶ
የማይናደፍ "ሆ" ከንብ ተወልዶ
በለውጥ ሰበብ /ሆ/ሲገድለን ስንቱ
ወንጌል ይመሥል ሆ/ ህገ መንግስቱ
ምህረት ፍቅር ነው ሆ/ ሁሌም ቃላቱ
ብለን ስናማው "ሆ" ንቀን ስናየው
ጭስ ሆኖ መጣ /ሆ / ንብ ላሰቃየው
በሎም በሎም ነው የምንለው
በነጋታው ደግሞ ወየው ወየው
ህወሀቴ ናና
በጡዘት ጎዳና
እዛ ማዶ ሆ እሳት ይነዳል
እዚህ ማዶ ሆ ቦንብ ይፈነዳል
ድሮኗን ያየ /ሆ/ ዓለም ይፈርዳል
እንኳን ከገደል /ሆ/ ሲኦል ያወርዳል

ዓመት ዓውደ አመት /ድገምና/ አመት /ድገምና/
ኢትዮጵያ ሀገራችን /ድገምና/ አመት /ድገምና/
ምድራዊ ገነት /ድገምና/ አመት /ድገምና/
ከሲኦል ተላቃ /ድገምና/ አመት /ድገምና /
ሰላም ይብዛላት /ድገምና/ ዓመት ድገምና
ፍቅር ይፍሰስባት "ድገምና" አመት /ድገምና /
አመት ድገምና
አመት ድገምና
ዓመት ድገምና
ድገም በስንዴ ድገም በጤፍ
ጠላቷ ይርገፍ
እንሾላ ፍሬ እንደቆላ ጤፍ።
ድገም በስንዴ ድገም በጤፍ
ከማንም ከምንም ኢትዮጵያ ትግዘፍ
፣፣፣፣

(በላይ በቀለ ወያ)

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
free በላይ በቀለ ወያ 😡😡😡😡
"ለምን ሞትህ" ቢሉት ...
አልሞትኩም እያለ ፣ ትውልድ ይሟገታል
ድሮስ
ኖሮ የማያውቅ ህዝብ ፣ ምን ሆኖ ይሞታል?!!!
።።።።።
(በላይ በቀለ ወያ ©)
💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
@ethio_Poem
@ethio_Poem
@ethio_Poem
(በላይ በቀለ ወያ)
@ethio_poem


እምዬ ኢትዮጵያ ፣ ሞኝ ነሽ ተላላ
ትዝ ትይኛለሽ ፣ ሸንኮራ ስበላ፡፡
"እንዴት " አትበይኝ!
እንደዚህ ነው ብዬ ፣ ካንቺ አልሟገትም
ጥርሳም ገዢ ሁሉ...
ጠአምሽን መጦ ፣ ይጥልሻል የትም!!!

(በላይ በቀለ ወያ)
💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
(በላይ በቀለ ወያ)

@ethio_poem

ምን አይነት ቄስ ናቸው ፣ ምፀት የለመዱ
"አባት ይፍቱኝ" ስል
"አብይ ይፍታህ "ብለው ፣ አሳልመውኝ ሔዱ
።።።።።
ዳሩ እውነት አላቸው ፣ ቀልዳቸው ቢመርም
ምህረት ያውቃልና
እኛ ብናጠፋም ፣ አምላክ ሰው አያስርም።

(( በላይ በቀለ ወያ ))

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
@ethio_poem
@ethio_poem
@ethio_poem
ተለቋል....😍💪💪💪💪💪
አዝማች
የግጥም ኮንሰርት
ከ ረድኤት ተረፈ ጋር

ሐሙስ
ሰኔ 30
በአለም ሲኒማ
ምሽት 11:30
ቄለም ወለጋ 😪😪😭😭😭😭😭

የወገኖቻችን ሞት ይብቃ።
10ሺ ሴቶች ወርቅ
ለተሰንበት ግደይ
ወንዶች ማራቶን ወርቅ
ታምራት ቶላ
ሴቶች ማራቶን ወርቅ
ጎተይቶም ገብረስላሴ
5ሺ ሴቶች ወርቅ
ጉደፍ ፀጋዬ
2025/02/21 17:29:40
Back to Top
HTML Embed Code: