Forwarded from Association of Ethiopian Architects | AEA
🚨 New Date Alert! 🚨
Due to an unforeseen government event, AEA’s 24th Annual General Assembly is now happening Next Week, Saturday, March 1, 2025! 🏛📅
Your voice matters! Join us as we discuss key developments, elect new leadership, and shape the future of our profession.
📌 Already registered? No worries - your spot is still secured!
Haven’t registered yet? Sign up now! 👇
👉 Registration Here
#AEA2025 #Architects #GeneralAssembly
Due to an unforeseen government event, AEA’s 24th Annual General Assembly is now happening Next Week, Saturday, March 1, 2025! 🏛📅
Your voice matters! Join us as we discuss key developments, elect new leadership, and shape the future of our profession.
📌 Already registered? No worries - your spot is still secured!
Haven’t registered yet? Sign up now! 👇
👉 Registration Here
#AEA2025 #Architects #GeneralAssembly
Google Docs
Registration for the 24th Annual General Assembly
We invite you to the 24th Annual General Assembly, to be held on Saturday, February 22, 2025 @ Elilly International Hotel. This will be an event where key decisions will be made regarding the association by the members.
Agenda of meeting shall be:
1. Election…
Agenda of meeting shall be:
1. Election…
የንግድ ባንክ ሕንጻ ተመርቆ ሲከፈት
ኅዳር 7 ቀን 1958 ዓም
ምንጭ: Zerihun Gultie
በጀማል አብዱልአዚዝ በኩል
@ethiopianarchitectureandurbanism
ኅዳር 7 ቀን 1958 ዓም
ምንጭ: Zerihun Gultie
በጀማል አብዱልአዚዝ በኩል
@ethiopianarchitectureandurbanism
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
የአደጋ_ደህንነት_ደንብ_ቁ_132_2014_የጸደቀ_250222_210150.pdf
327.8 KB
“ ማንኛውም ሰው በተቋሙ ውስጥ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ካላሟላ ከ10 ሺሕ ያላነሰ ከ100 ሺሕ ያልበለጠ ቅጣት ይጣልበታል ” - ኮሚሽኑ
የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ አካላት የገንዘብና የሥራ ፈቃድን እስከማሳገድ ቅጣትን የሚደነግግ ደንብ ማውጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና ስጋት ሥራ አመራር አስታወቀ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደንቡ፣ “ማንኛውም ሰው በተቋሙ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ሳያሟላ የቀረ እንደሆነ እንደ ደረጃው ከ10 ሺሕ ያላነሰና ከ100 ሺሕ ያልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ይጣልበታል” ይላል።
በኮሚሽኑ ደንብ መሠረት፦
ደንቡ፣ የህንፃዎችና የግንባታዎች ዲዛይን፣ ስለህንፃ፣ ግንባታና የግንባታ ሂደት መሟላት ያለባቸው የአደጋ ስጋት ደኅንነት መስፈርቶችንና የህንፃ አጠቃቀምን የተመለከቱ ግዴታዎችን አካቶ ይዟል።
የህንፃዎች ዲዛይን የሌሎች ሰዎችን ንብረቶች ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ መሆን እንደሌለባቸው፣ በዲዛይኑ የእሳትና ሌሎች አደጋዎችን መከላከያና መቆጣጠሪያ መስፈርቶች መሟላት እንዳለባቸውም ደንቡ ያትታል።
ነባር ህንፃዎች ጥገና ወይም ለውጥ በሚደረግባቸው ጊዜ አደጋን ለመቆጣጠር/ለመከላከል የተገጠሙ ሲስተሞች ስለመሟላታቸው ፍተሻ ተደርጎ የአደጋ ደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መውሰድ ግዴታ መሆኑ ተመልክቷል።
በግንባታ ሂደት ያለ ህንፃ ሲጠናቀቅ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለሚያዙ ክፍሎች አስፈላጊ የደኅንነት ተግባራት መሟላታቸው ካልተረጋገጠ ለተጠቃሚዎች መተላለፍ እንደማይችልም በድንጋጌው ተጠቅሷል።
ህንፃ ተከራዮች አደጋን አስቀድሞ ለመከላከል ወይም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአደጋ ደኀንነት መስፈርቶችን እንዲያሟሉ፣ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ያላሟላ ነባር ህንፃ ባለቤት ለማሟላት የሚጠበቅበትን የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በደንቡ ተገልጿል።
“ማንኛውም የጅምር ህንፃ ተጠቃሚ ከሚመለከተው አካል የመጠቀሚያ ፈቃድ መያዝ ይኖርበታል”ም ብሏል ደንቡ።
በተጨማሪም፣ አደገኛ ንጥረ ነገሮች የሚያከማቹ የሚያጎጉዙ፣ የሚጠቀሙ የደኀንነት የደኅንነት ብቃት ማረጋገጫ ሊኖራቸው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ የተከማቹ አደገኛ ንጥረ ነገሮችን እንደሚያስወግድ አትቷል።
እንዲሁም የተከለከሉ ድርጊቶችን ዝርዝር ያስቀመጠው ደንቡ የንግድ/የሥራ ፈቃድ እስከማሳገድ የሚደርስ እርምጃ እንደሚያስወስድ ገልጾ፣ እርምጃ አወሳሰድና አስተዳደራዊ ቅጣት ዝርዝር ድንጋጌዎችን ደንቡ አስቀምጧል።
ኮሚሽኑ ይህንኑ ደንብና ለማህበረሰቡ ሊቀርብ ስለሚገባ ግንዛቤ በተመለከተ ከሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ትላንት በሳሬም ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፣ ተጨማሪ ይኖረናል።
(ሙሉ ድንጋጌ የያዘው ደንቡ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ አካላት የገንዘብና የሥራ ፈቃድን እስከማሳገድ ቅጣትን የሚደነግግ ደንብ ማውጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና ስጋት ሥራ አመራር አስታወቀ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደንቡ፣ “ማንኛውም ሰው በተቋሙ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ሳያሟላ የቀረ እንደሆነ እንደ ደረጃው ከ10 ሺሕ ያላነሰና ከ100 ሺሕ ያልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ይጣልበታል” ይላል።
በኮሚሽኑ ደንብ መሠረት፦
ደንቡ፣ የህንፃዎችና የግንባታዎች ዲዛይን፣ ስለህንፃ፣ ግንባታና የግንባታ ሂደት መሟላት ያለባቸው የአደጋ ስጋት ደኅንነት መስፈርቶችንና የህንፃ አጠቃቀምን የተመለከቱ ግዴታዎችን አካቶ ይዟል።
የህንፃዎች ዲዛይን የሌሎች ሰዎችን ንብረቶች ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ መሆን እንደሌለባቸው፣ በዲዛይኑ የእሳትና ሌሎች አደጋዎችን መከላከያና መቆጣጠሪያ መስፈርቶች መሟላት እንዳለባቸውም ደንቡ ያትታል።
ነባር ህንፃዎች ጥገና ወይም ለውጥ በሚደረግባቸው ጊዜ አደጋን ለመቆጣጠር/ለመከላከል የተገጠሙ ሲስተሞች ስለመሟላታቸው ፍተሻ ተደርጎ የአደጋ ደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መውሰድ ግዴታ መሆኑ ተመልክቷል።
በግንባታ ሂደት ያለ ህንፃ ሲጠናቀቅ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለሚያዙ ክፍሎች አስፈላጊ የደኅንነት ተግባራት መሟላታቸው ካልተረጋገጠ ለተጠቃሚዎች መተላለፍ እንደማይችልም በድንጋጌው ተጠቅሷል።
ህንፃ ተከራዮች አደጋን አስቀድሞ ለመከላከል ወይም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአደጋ ደኀንነት መስፈርቶችን እንዲያሟሉ፣ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ያላሟላ ነባር ህንፃ ባለቤት ለማሟላት የሚጠበቅበትን የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በደንቡ ተገልጿል።
“ማንኛውም የጅምር ህንፃ ተጠቃሚ ከሚመለከተው አካል የመጠቀሚያ ፈቃድ መያዝ ይኖርበታል”ም ብሏል ደንቡ።
በተጨማሪም፣ አደገኛ ንጥረ ነገሮች የሚያከማቹ የሚያጎጉዙ፣ የሚጠቀሙ የደኀንነት የደኅንነት ብቃት ማረጋገጫ ሊኖራቸው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ የተከማቹ አደገኛ ንጥረ ነገሮችን እንደሚያስወግድ አትቷል።
እንዲሁም የተከለከሉ ድርጊቶችን ዝርዝር ያስቀመጠው ደንቡ የንግድ/የሥራ ፈቃድ እስከማሳገድ የሚደርስ እርምጃ እንደሚያስወስድ ገልጾ፣ እርምጃ አወሳሰድና አስተዳደራዊ ቅጣት ዝርዝር ድንጋጌዎችን ደንቡ አስቀምጧል።
ኮሚሽኑ ይህንኑ ደንብና ለማህበረሰቡ ሊቀርብ ስለሚገባ ግንዛቤ በተመለከተ ከሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ትላንት በሳሬም ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፣ ተጨማሪ ይኖረናል።
(ሙሉ ድንጋጌ የያዘው ደንቡ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የወላይታ ሶዶ ከተማ የቶፖግራፊ ካርታ ዝግጅት
የወላይታ አውራጃ ካርታ እንዲነሣ እና የሰባቱ ወረዳዎች ይዞታ በካርታው ላይ እንዲሰፍር ካደረግሁ በኋላ፣ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ኘላን ወደ ማዘጋጀት ዕቅዴ ገባሁ፡፡ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ፕላን እንዲዘጋጅ ማድረግ የከተማዋ ዕድገት በዕቅድ እንዲመራ ያግዛል፡፡ ለዚህ ሥራ ደግሞ አስቀድሞ የቶፖግራፊ ካርታ መዘጋጀት አለበት፡፡ የቶፖግራፊ ካርታውን ለማዘጋጀት ሰርቬየሮች ከአገር ግዛት ሚኒስቴር የማዘጋጃ ቤቶች ክፍል እንዲሰጡኝ ብጠይቅ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ፡፡ለአስተዳደሩም ሆነ ለሕዝቡ አመች እንዲሆን አውራጃውን በአዲስ መልክ ለማዋቀር ከአገር ግዛት ሚኒስቴር ፈቃደኝነት ሳጣ፣ ቀደም ብሎ የአውራጃውን ካርታ በማንሳት ወደ ተባበሩኝ መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ፊቴን አዞርኩኝና እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የሥራ ሰዓት ሳይጠብቁና ቅዳሜ፣ እሁድ፣ የበዓል ቀን ሳይሉ፣ ለሶዶ ከተማ ማስተር አጠናቀቁልን፡፡ ባለሙያዎቹ የሕዝብና ቤት ቆጠራውን ስለአካሄዱልን እንዲሁም ፕላን ሥራ አስፈላጊ የሆነውን የቶፖግራፊ ካርታ ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ብዙ የልማት ሥራዎችን በዕቅድ ለማከናወን የሚያስፈልገውንና ለልማት ሥራ መሠረት የሆነውን የአውራጃውንም ሆነ የሶዶ ከተማን ካርታ ስላነሱልንና ለወላይታ አውራጃ ልማት ከፍ ያለ አስተዋፅኦ ስላደረጉ ባለውለታዎች ናቸው፡፡ በጊዜው ምስጋና ያቀረብኩላቸው ቢሆንም እዚህ ላይ ስማቸው ሲጠራ እንዲኖር ደግሜ አመሰግናቸዋለሁ፡፡ ሥራውን አጠናቀው ሲያስረክቡንም አብረው የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎችን ጭምር ለግሰውናል፡፡
#የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎቹን ልገሳ ያደረጉልን፣ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት ሄጄ የካርታ ሥራ ባለሙያዎቹን ርዳታ በጠየኩበት ወቅት ከዕቃ ግምጃ ቤታቸው የመግባት እድል አጋጥሞኝ ነበር፡፡ መሥሪያ ቤቱ በርዳታ ያገኛቸው ብዙ የቅየሳ መሣሪያዎች(ቴዎዶላይቶች፣ ጃሎዎች፣ ስታድያዎችና ባለመቶ ሃምሳና ሰላሳ ሜትር፣ አደጋ የሚችሉ እና ለገጠር ሥራ አገልግሎት የተሠሩ ጥቅል ሜትሮች) የዕቃ ግምጃ ቤቱን ያጨናነቁት መሆኑንም አይቼ ነበር፡፡ ስለዚህ የውሀ ልማት ባለሙያዎች ወደ አውራጃው ይዘዋቸው የሄዱትን የቅየሳ መሣሪዎች እዛው ለአውራጃው ግዛት ለልማት ሥራ አገልግሎት እንዲውሉ፣ ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ እንደሚባለው ሆኜ ሥራው ሲያልቅ መሣሪያዎቹን ሁሉ ትተውልን እንዲሄዱ አድርጌያለሁ፡፡
#የባለሙያዎቹ ኃላፊ የነበረው ስሙን የዘነጋሁት መሐንዲስ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ባየኝ ቁጥር «ባገለገልን ፈንታ መሣሪያዎቻችንን ነጥቀህ አባረርከን›› እያለ በውስጠ ወይራ ቀልድ እየወቀሰኝ እንሳሳቅ ነበር፡፡ የቅየሳ መሣሪያዎቻቸውም በወላይታ አውራጃ ለወረዳ ከተማዎች መንገዶች ቅየሳ እንዲሁም በአበላና በሌ ለሰፈሩት ጭሰኞች ለአንድ ሰው አምስት ሄክታር (250 በ200 ሜትር) መሬት እየሸነሸኑ ለመስጠት አገልግለውናል፡፡ በተጨማሪም የሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ምክትል አስተዳዳሪ በነበርኩበት ጊዜ ከዲላ እስከ ሞያሌ : ባለው ኢንተርናሽናል መንገድ ላይ ላሉ ከተሞች ቶፖግራፊ ካርታ ለማዘጋጀት ለቅየሳ ሥራ ተጠቅመንባቸዋል፡፡ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት በባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በቅየሳ መሣሪዎችም ርዳታ ስላበረከተልን ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል፡፡
▼ሕይወቴ ፤ ደጃዝማች ወልደሰማዕት ገብረወልድ ፣ 262-3
Via Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም
@ethiopianarchitectureandurbanism
የወላይታ አውራጃ ካርታ እንዲነሣ እና የሰባቱ ወረዳዎች ይዞታ በካርታው ላይ እንዲሰፍር ካደረግሁ በኋላ፣ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ኘላን ወደ ማዘጋጀት ዕቅዴ ገባሁ፡፡ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ፕላን እንዲዘጋጅ ማድረግ የከተማዋ ዕድገት በዕቅድ እንዲመራ ያግዛል፡፡ ለዚህ ሥራ ደግሞ አስቀድሞ የቶፖግራፊ ካርታ መዘጋጀት አለበት፡፡ የቶፖግራፊ ካርታውን ለማዘጋጀት ሰርቬየሮች ከአገር ግዛት ሚኒስቴር የማዘጋጃ ቤቶች ክፍል እንዲሰጡኝ ብጠይቅ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ፡፡ለአስተዳደሩም ሆነ ለሕዝቡ አመች እንዲሆን አውራጃውን በአዲስ መልክ ለማዋቀር ከአገር ግዛት ሚኒስቴር ፈቃደኝነት ሳጣ፣ ቀደም ብሎ የአውራጃውን ካርታ በማንሳት ወደ ተባበሩኝ መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ፊቴን አዞርኩኝና እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የሥራ ሰዓት ሳይጠብቁና ቅዳሜ፣ እሁድ፣ የበዓል ቀን ሳይሉ፣ ለሶዶ ከተማ ማስተር አጠናቀቁልን፡፡ ባለሙያዎቹ የሕዝብና ቤት ቆጠራውን ስለአካሄዱልን እንዲሁም ፕላን ሥራ አስፈላጊ የሆነውን የቶፖግራፊ ካርታ ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ብዙ የልማት ሥራዎችን በዕቅድ ለማከናወን የሚያስፈልገውንና ለልማት ሥራ መሠረት የሆነውን የአውራጃውንም ሆነ የሶዶ ከተማን ካርታ ስላነሱልንና ለወላይታ አውራጃ ልማት ከፍ ያለ አስተዋፅኦ ስላደረጉ ባለውለታዎች ናቸው፡፡ በጊዜው ምስጋና ያቀረብኩላቸው ቢሆንም እዚህ ላይ ስማቸው ሲጠራ እንዲኖር ደግሜ አመሰግናቸዋለሁ፡፡ ሥራውን አጠናቀው ሲያስረክቡንም አብረው የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎችን ጭምር ለግሰውናል፡፡
#የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎቹን ልገሳ ያደረጉልን፣ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት ሄጄ የካርታ ሥራ ባለሙያዎቹን ርዳታ በጠየኩበት ወቅት ከዕቃ ግምጃ ቤታቸው የመግባት እድል አጋጥሞኝ ነበር፡፡ መሥሪያ ቤቱ በርዳታ ያገኛቸው ብዙ የቅየሳ መሣሪያዎች(ቴዎዶላይቶች፣ ጃሎዎች፣ ስታድያዎችና ባለመቶ ሃምሳና ሰላሳ ሜትር፣ አደጋ የሚችሉ እና ለገጠር ሥራ አገልግሎት የተሠሩ ጥቅል ሜትሮች) የዕቃ ግምጃ ቤቱን ያጨናነቁት መሆኑንም አይቼ ነበር፡፡ ስለዚህ የውሀ ልማት ባለሙያዎች ወደ አውራጃው ይዘዋቸው የሄዱትን የቅየሳ መሣሪዎች እዛው ለአውራጃው ግዛት ለልማት ሥራ አገልግሎት እንዲውሉ፣ ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ እንደሚባለው ሆኜ ሥራው ሲያልቅ መሣሪያዎቹን ሁሉ ትተውልን እንዲሄዱ አድርጌያለሁ፡፡
#የባለሙያዎቹ ኃላፊ የነበረው ስሙን የዘነጋሁት መሐንዲስ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ባየኝ ቁጥር «ባገለገልን ፈንታ መሣሪያዎቻችንን ነጥቀህ አባረርከን›› እያለ በውስጠ ወይራ ቀልድ እየወቀሰኝ እንሳሳቅ ነበር፡፡ የቅየሳ መሣሪያዎቻቸውም በወላይታ አውራጃ ለወረዳ ከተማዎች መንገዶች ቅየሳ እንዲሁም በአበላና በሌ ለሰፈሩት ጭሰኞች ለአንድ ሰው አምስት ሄክታር (250 በ200 ሜትር) መሬት እየሸነሸኑ ለመስጠት አገልግለውናል፡፡ በተጨማሪም የሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ምክትል አስተዳዳሪ በነበርኩበት ጊዜ ከዲላ እስከ ሞያሌ : ባለው ኢንተርናሽናል መንገድ ላይ ላሉ ከተሞች ቶፖግራፊ ካርታ ለማዘጋጀት ለቅየሳ ሥራ ተጠቅመንባቸዋል፡፡ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት በባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በቅየሳ መሣሪዎችም ርዳታ ስላበረከተልን ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል፡፡
▼ሕይወቴ ፤ ደጃዝማች ወልደሰማዕት ገብረወልድ ፣ 262-3
Via Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም
@ethiopianarchitectureandurbanism
ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ከተማ ለምትገኙ የሪል እስቴት አልሚዎች በሙሉ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት ስራ ላይ የተሰማራችሁ አልሚዎች በሪል አስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ እንዲሁም ይህንን ለማስፈጸም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ስለሚካሄድ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባምቢስ አጠገብ በሚገኘው በዲል ኦፖል ሆቴል ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት ጀምሮ ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ወኪል የሆናችሁ ሁሉ በመገኘት የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ እናሰተላልፋለን፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ።
@ethiopianarchitectureandurbanism
በአዲስ አበባ ከተማ ለምትገኙ የሪል እስቴት አልሚዎች በሙሉ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት ስራ ላይ የተሰማራችሁ አልሚዎች በሪል አስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ እንዲሁም ይህንን ለማስፈጸም በወጣው ረቂቅ ደንብ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ስለሚካሄድ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባምቢስ አጠገብ በሚገኘው በዲል ኦፖል ሆቴል ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት ጀምሮ ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ወኪል የሆናችሁ ሁሉ በመገኘት የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ እናሰተላልፋለን፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ።
@ethiopianarchitectureandurbanism
የስልጠና እድል
ስራ ፈጠራ እና የመቀጠር ክህሎት።
በቅርቡ ለተመረቁ ሴት ምሩቃን
SHE CAN Cohort 3 training registration is now open!
This free Employability & Entrepreneurship Skills Training Program is offered by Ayzon Foundation in partnership with the Satchmo American Center at the U.S. Embassy in Addis Ababa.
The training will take place every Monday and Thursday from 8:30 AM – 12:30 PM.
If you are interested to participate, please sign up at
https://forms.gle/E4FgojEJNMJzk8hh7
Eligibility Criteria:
• Must be a female recent bachelor’s degree graduate of 2024 or 2025 GC.
• Commitment to complete all 24 sessions with punctuality and full attendance.
Those selected will be contacted for an interview.
To learn more about free Satchmo Center activities, become a member at https://jazzio.land/register
and follow Satchmo programs on telegram at https://www.tgoop.com/SatchmoAmericanCenter
ምንጭ። US Embassy Addis Ababa
@ethiopianarchitectureandurbanism
ስራ ፈጠራ እና የመቀጠር ክህሎት።
በቅርቡ ለተመረቁ ሴት ምሩቃን
SHE CAN Cohort 3 training registration is now open!
This free Employability & Entrepreneurship Skills Training Program is offered by Ayzon Foundation in partnership with the Satchmo American Center at the U.S. Embassy in Addis Ababa.
The training will take place every Monday and Thursday from 8:30 AM – 12:30 PM.
If you are interested to participate, please sign up at
https://forms.gle/E4FgojEJNMJzk8hh7
Eligibility Criteria:
• Must be a female recent bachelor’s degree graduate of 2024 or 2025 GC.
• Commitment to complete all 24 sessions with punctuality and full attendance.
Those selected will be contacted for an interview.
To learn more about free Satchmo Center activities, become a member at https://jazzio.land/register
and follow Satchmo programs on telegram at https://www.tgoop.com/SatchmoAmericanCenter
ምንጭ። US Embassy Addis Ababa
@ethiopianarchitectureandurbanism