Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የ #ኢዜማ 6ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ን እና የኢዜማ አካዳሚ ምርቃትን አስመልክቶ የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ ያቀረቡት ንግግር።
ኢዜማ ከመንግሥት ጋር አብሮ መስራቱ መርህ የለሽ ሊያስብለው አይችልም
አሰፉ ተረፈ (የኢዜማ ብሔራዊ ኦዲት ኮሚቴ አባል)
በኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 12 ትኩረቷን ፖለቲካ እና መርህ ላይ አድርጋ የተሠናዳች ሲሆን የወሩን እንግዳ ጨምሮ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሥነብበናለች፤ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።
https://drive.google.com/file/d/1ciHhYDVU-IojlXWD1UkAp1rC7aTA5pjx/view?usp=drivesdk
#ኢዜማ
#የዜጎች_ልሳን
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በኢዜማ አካዳሚ ምርቃት መርኃ ግብር ላይ የአካዳሚው አስተባባሪ ሐሮሌ ዮሴፍ ያደረጉት ንግግር።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ፀሐፊ ደስታ ዲንቃ በ #ኢዜማ አካዳሚ ምርቃት ላይ ያደረጉት ንግግር።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ኢዜማ መብትን በሰላማዊ እና ህጋዊ መንገድ መጠየቅን ይደግፋል!
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ላለፉት ረጅም ዓመታት ከሙያቸው ጋር በተገናኘ በርካታ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ እንደነበረ ይታወቃል። ሆኖም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የመንግስት አካል ቀና ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በቸልተኝነት በማየት ተጨባጭ ያልሆነ ተስፋ ከመስጠት የዘለለ ይህ ነው የሚባል ተግባራዊ መፍትሔ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡
በተለይም ላለፈው አንድ ወር የጤና ባለሙያዎች ጥያቄያቸውን በፅሁፍ ጭምር እንዳሳወቁ እና መልስ እንዲሰጣቸው በአደባባይ እየጠየቁ የሚገኙ ቢሆንም መንግስት ለጉዳዩ ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ በተቃራኒው እንቅስቃሴ ሲያደርግ መታየቱ አግባብነት ያለው ተግባር አይደለም፡፡
የባለሙያዎቹን ጥያቄ የመጠየቅ ህገመንግስታዊ መብት አክብሮ መንግስት በግልፅ ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠቱ፣ ችግራቸውን የመረዳት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ አለማድረጉ እና ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሲብስም የተደረጉ ሙከራዎች ካሉ በወቅቱ በተገቢው መንገድ አለማሳወቁ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው።
የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄዎች ተገቢ መልስ የሚሰጥ የመንግስት አካል በመጥፋቱ ባለፈው ሳምንት ጥያቄው ከፍ ብሎ ወደ ከፊል ስራ ማቆም አድማ አምርቷል። በዚህም ምክንያት የጤና አገልግሎት ፈላጊው የማሕበረሰቡ ክፍል ለእንግልት እና ለስቃይ እየተዳረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ ከቀጠለም ማሕበረሰቡ ለተጨማሪ እንግልት እንዳይዳረግ ያሳስበናል፡፡
ባለሙያዎቹ ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው እና የትኛውም የፖለቲካ አካል ጥያቄያቸውን ተንተርሶ ትርፍ ለማግኘት እንዳይንቀሳቀስ ደጋግመው ማሳሰባቸው፤ ከኢዜማ መርህ ጋር የሚስማማ በመሆኑ መልዕክቱን በማክበር ኢዜማ ምንም አይነት ሀሳብ ላለመሰጠት በጥንቃቄ ሲመለከት ቆይቷል፡፡ ነገር ግን አሁን ያለው እንቅስቃሴ ወደ መፍትሔ ከማምራት ይልቅ እየተወሳሰበ ሕዝቡን ከፍተኛ ዋጋ እንዳያስከፍል ብሎም ለተጨማሪ ሀገራዊ ትርምስ የሚጋብዝ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ደረጃ ላይ መገኘቱ አሳስቦናል። ሒደቱ በዚሁ ከቀጠለ በተግባር ለባለሙያው ጥያቄ መልስ ከማስገኘት ይልቅ ጠቃሚ ወዳልሆነ ሀገራዊ አለመረጋጋት የማምራት አዝማሚያ እያሳየ ነው፡፡
ኢዜማ የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄ በአግባቡ የሚረዳው እና መብትን በሰላማዊ መንገድ መጠየቅን የሚደግፈው ተግባር ነው፡፡ በእርግጥ መብትን ለማስከበር የሚኬድበት ስልት ግን ዜጎችን ለአደጋ የማያጋልጥ ሊሆን ይገባል የሚል ፅኑ እምነት አለን። ሁላችንም እንደምንረዳው የስራ ማቆም አድማ የማድረግ መብት ለጤናው ዘርፍ ሲሆን ቀጥተኛ ገፈት ቀማሹ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት የሚመጣው የሕብረተሰብ ክፍል መሆኑ እሙን ነው። ይህ ከመሆኑ አንፃር አጣዳፊ ህክምና የሚፈልጉ ዜጎች በስቃይ ውስጥ የመቆየት ብሎም የመኖር ያለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት በመሆኑ እንዲሁም ተያያዥ የሞራል ጥያቄ የሚያስነሳ ከመሆኑ አንፃር ትክክለኛ ስልት አይሆንም፡፡
ይህን ታሳቢ በማድረግም ወደ መፍትሔው ለመሄድ እና ከአላስፈላጊ ውጥረት ለመውጣት
1ኛ. መንግስት ስህተቱን አምኖ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እየተደረገ ካለው የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የታሰሩ የጤና ባለሙያዎችን እንዲፈታ ብሎም በመገናኛ ብዙኃን ወጥቶ ለባለሙያዎቹ ጥያቄዎች ያለውን መረዳት በአግባቡ እንዲገልፅ እንዲሁም ለመፍትሔው ከባለሙያዎቹ ጋር ተባብሮ እንደሚሰራ ቃል እንዲገባ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ. የጤና ባለሙያዎችም ከስራ ማቆም አድማው ተመልሰው የመፍትሔው አካል ለመሆን በጋራ እንዲሰሩ እንጠይቃለን።
3ኛ. የጤና ባለሙያ ማህበራትን ያቀፈ እና የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት ያካተተ ብሔራዊ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ፣ በመካከለኛ ጊዜ እንዲሁም በረጅም ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ጥያቄዎችን በመለየት ግብረ ኃይሉ ለባለሙያው እና ለማህበረሰቡ የደረሰበትን ውጤት በመገናኛ ብዙኃን እንዲያሳውቅ ምክረ ሀሳባችንን እናቀርባለን፡፡
በመጨረሻም በባለሙያዎቹ ደጋግሞ እንደተባለው ከዚህ ሂደት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መሞከርን እኛም አብዝተን የምንፀየፈው መሆኑን አስምረን እያረጋገጥን! ይህን መጥፎ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሀገራዊ ትርምስ እና ሁከት በመፍጠር መንግስት ላይ ያለን የፖለቲካ ቅሬታ መወጣጫ ለማድረግ መሞከርም ሆነ ሌሎች አድማዎችን አቀጠጣጥሎ የመንግስት ስልጣን ለመነቀነቅ የሚሞከር የሞኝ ሙከራ ጊዜው ያለፈበት የከሰረ መንገድ አድርገን የምንረዳው መሆኑን ለመግለፅ እንፈልጋለን፡፡
በዚህ የመብት ትግል ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ስትሳተፉ እስር እንግልት እና አፈና ለደረሰባችሁ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ መብትን መጠየቅ በምንም መልኩ ሊያሳስር እና ሊያሳፍን እንደማይገባ በዚህ መንገድ ጥያቄውን ለማፈን መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በአስቸኳይ እንዲያቆም ድርጊቱን እኛም አጥብቀን የምናወግዝ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 10/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ላለፉት ረጅም ዓመታት ከሙያቸው ጋር በተገናኘ በርካታ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ እንደነበረ ይታወቃል። ሆኖም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የመንግስት አካል ቀና ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በቸልተኝነት በማየት ተጨባጭ ያልሆነ ተስፋ ከመስጠት የዘለለ ይህ ነው የሚባል ተግባራዊ መፍትሔ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡
በተለይም ላለፈው አንድ ወር የጤና ባለሙያዎች ጥያቄያቸውን በፅሁፍ ጭምር እንዳሳወቁ እና መልስ እንዲሰጣቸው በአደባባይ እየጠየቁ የሚገኙ ቢሆንም መንግስት ለጉዳዩ ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ በተቃራኒው እንቅስቃሴ ሲያደርግ መታየቱ አግባብነት ያለው ተግባር አይደለም፡፡
የባለሙያዎቹን ጥያቄ የመጠየቅ ህገመንግስታዊ መብት አክብሮ መንግስት በግልፅ ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠቱ፣ ችግራቸውን የመረዳት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ አለማድረጉ እና ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሲብስም የተደረጉ ሙከራዎች ካሉ በወቅቱ በተገቢው መንገድ አለማሳወቁ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው።
የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄዎች ተገቢ መልስ የሚሰጥ የመንግስት አካል በመጥፋቱ ባለፈው ሳምንት ጥያቄው ከፍ ብሎ ወደ ከፊል ስራ ማቆም አድማ አምርቷል። በዚህም ምክንያት የጤና አገልግሎት ፈላጊው የማሕበረሰቡ ክፍል ለእንግልት እና ለስቃይ እየተዳረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ ከቀጠለም ማሕበረሰቡ ለተጨማሪ እንግልት እንዳይዳረግ ያሳስበናል፡፡
ባለሙያዎቹ ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው እና የትኛውም የፖለቲካ አካል ጥያቄያቸውን ተንተርሶ ትርፍ ለማግኘት እንዳይንቀሳቀስ ደጋግመው ማሳሰባቸው፤ ከኢዜማ መርህ ጋር የሚስማማ በመሆኑ መልዕክቱን በማክበር ኢዜማ ምንም አይነት ሀሳብ ላለመሰጠት በጥንቃቄ ሲመለከት ቆይቷል፡፡ ነገር ግን አሁን ያለው እንቅስቃሴ ወደ መፍትሔ ከማምራት ይልቅ እየተወሳሰበ ሕዝቡን ከፍተኛ ዋጋ እንዳያስከፍል ብሎም ለተጨማሪ ሀገራዊ ትርምስ የሚጋብዝ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ደረጃ ላይ መገኘቱ አሳስቦናል። ሒደቱ በዚሁ ከቀጠለ በተግባር ለባለሙያው ጥያቄ መልስ ከማስገኘት ይልቅ ጠቃሚ ወዳልሆነ ሀገራዊ አለመረጋጋት የማምራት አዝማሚያ እያሳየ ነው፡፡
ኢዜማ የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄ በአግባቡ የሚረዳው እና መብትን በሰላማዊ መንገድ መጠየቅን የሚደግፈው ተግባር ነው፡፡ በእርግጥ መብትን ለማስከበር የሚኬድበት ስልት ግን ዜጎችን ለአደጋ የማያጋልጥ ሊሆን ይገባል የሚል ፅኑ እምነት አለን። ሁላችንም እንደምንረዳው የስራ ማቆም አድማ የማድረግ መብት ለጤናው ዘርፍ ሲሆን ቀጥተኛ ገፈት ቀማሹ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት የሚመጣው የሕብረተሰብ ክፍል መሆኑ እሙን ነው። ይህ ከመሆኑ አንፃር አጣዳፊ ህክምና የሚፈልጉ ዜጎች በስቃይ ውስጥ የመቆየት ብሎም የመኖር ያለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት በመሆኑ እንዲሁም ተያያዥ የሞራል ጥያቄ የሚያስነሳ ከመሆኑ አንፃር ትክክለኛ ስልት አይሆንም፡፡
ይህን ታሳቢ በማድረግም ወደ መፍትሔው ለመሄድ እና ከአላስፈላጊ ውጥረት ለመውጣት
1ኛ. መንግስት ስህተቱን አምኖ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እየተደረገ ካለው የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የታሰሩ የጤና ባለሙያዎችን እንዲፈታ ብሎም በመገናኛ ብዙኃን ወጥቶ ለባለሙያዎቹ ጥያቄዎች ያለውን መረዳት በአግባቡ እንዲገልፅ እንዲሁም ለመፍትሔው ከባለሙያዎቹ ጋር ተባብሮ እንደሚሰራ ቃል እንዲገባ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ. የጤና ባለሙያዎችም ከስራ ማቆም አድማው ተመልሰው የመፍትሔው አካል ለመሆን በጋራ እንዲሰሩ እንጠይቃለን።
3ኛ. የጤና ባለሙያ ማህበራትን ያቀፈ እና የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት ያካተተ ብሔራዊ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ፣ በመካከለኛ ጊዜ እንዲሁም በረጅም ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ጥያቄዎችን በመለየት ግብረ ኃይሉ ለባለሙያው እና ለማህበረሰቡ የደረሰበትን ውጤት በመገናኛ ብዙኃን እንዲያሳውቅ ምክረ ሀሳባችንን እናቀርባለን፡፡
በመጨረሻም በባለሙያዎቹ ደጋግሞ እንደተባለው ከዚህ ሂደት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መሞከርን እኛም አብዝተን የምንፀየፈው መሆኑን አስምረን እያረጋገጥን! ይህን መጥፎ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሀገራዊ ትርምስ እና ሁከት በመፍጠር መንግስት ላይ ያለን የፖለቲካ ቅሬታ መወጣጫ ለማድረግ መሞከርም ሆነ ሌሎች አድማዎችን አቀጠጣጥሎ የመንግስት ስልጣን ለመነቀነቅ የሚሞከር የሞኝ ሙከራ ጊዜው ያለፈበት የከሰረ መንገድ አድርገን የምንረዳው መሆኑን ለመግለፅ እንፈልጋለን፡፡
በዚህ የመብት ትግል ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ስትሳተፉ እስር እንግልት እና አፈና ለደረሰባችሁ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ መብትን መጠየቅ በምንም መልኩ ሊያሳስር እና ሊያሳፍን እንደማይገባ በዚህ መንገድ ጥያቄውን ለማፈን መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በአስቸኳይ እንዲያቆም ድርጊቱን እኛም አጥብቀን የምናወግዝ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 10/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ ) ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄን አስመልክቶ ከአዲስ ኮምፓስ ሚዲያ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ይመልከቱ።
https://www.youtube.com/live/6VlxY6lNNC8?si=5hl1S_UohRtGxVMj
https://www.youtube.com/live/6VlxY6lNNC8?si=5hl1S_UohRtGxVMj
YouTube
"ብሔራዊ ግብረ-ሃይል"፣ "ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣ "የፍርሃት ቆፈን?"
"ብሔራዊ ግብረ-ሃይል"፣
"ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣
"የፍርሃት ቆፈን?"
"ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣
"የፍርሃት ቆፈን?"
የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!!
የኢዜማ አባል የሆኑት ሲኒየር ፋርማሲስት ኃይለማርያም ብርሃኑ የድሪም ኬር አጠቃላይ ሆስፒታል የፉርማሲ ክፍል ኃላፊ፣ የኢዜማ የባህርዳር ከተማ የስራ አስፈፃሚ፣ በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የስራ አስፈፃሚ፣ ፓርቲውን በመወከል የ2013 ዓ.ም የክልሉ ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ እንዲሁም በአማራ ክልል በነበረው ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ንቁ ተሳታፊ የነበሩ በሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ያሉ ቆራጥ፣ ሀገር እና ወገንን ቀን ከሌት በማገልገል የሚተጉ ዜጋ ናቸው።
አባላችን ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም ምሽት በ2፡00 ሰዓት በፓሊሶች ከቤታቸው ተወስደው በባህርዳር ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለምንም ክስ የታሰሩ ሲሆን ፤ በግንቦት 4 ቀን አካልን ነፃ የማውጣት ክስ ተመስርቶ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም የባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ያስተላለፈ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ከነበሩበት ቦታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፡፡
መንግስት አንድን ዜጋ ከሕግ በላይ ሆኖ አስሮ ማንገላታቱ ሳያንስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር ሲጨመርበት ተስፋ አስቆራጭ ነው! በመሆኑም የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በአፅንኦት እንጠይቃለን!!!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ
የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 13/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የኢዜማ አባል የሆኑት ሲኒየር ፋርማሲስት ኃይለማርያም ብርሃኑ የድሪም ኬር አጠቃላይ ሆስፒታል የፉርማሲ ክፍል ኃላፊ፣ የኢዜማ የባህርዳር ከተማ የስራ አስፈፃሚ፣ በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የስራ አስፈፃሚ፣ ፓርቲውን በመወከል የ2013 ዓ.ም የክልሉ ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ እንዲሁም በአማራ ክልል በነበረው ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ንቁ ተሳታፊ የነበሩ በሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ያሉ ቆራጥ፣ ሀገር እና ወገንን ቀን ከሌት በማገልገል የሚተጉ ዜጋ ናቸው።
አባላችን ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም ምሽት በ2፡00 ሰዓት በፓሊሶች ከቤታቸው ተወስደው በባህርዳር ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለምንም ክስ የታሰሩ ሲሆን ፤ በግንቦት 4 ቀን አካልን ነፃ የማውጣት ክስ ተመስርቶ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም የባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ያስተላለፈ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ከነበሩበት ቦታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፡፡
መንግስት አንድን ዜጋ ከሕግ በላይ ሆኖ አስሮ ማንገላታቱ ሳያንስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር ሲጨመርበት ተስፋ አስቆራጭ ነው! በመሆኑም የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በአፅንኦት እንጠይቃለን!!!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ
የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 13/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የኅዘን መግለጫ
*
በ #ኢዜማ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር መምሪያ ቋሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ መስፍን አበበ ግንቦት 26/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱም ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ 8:00 ሰዓት በሽሮሜዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የፓርቲው አመራሮች እና አባላት በአባላችን በአቶ መስፍን አበበ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ኅዘን እየገለጽን ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።
*
በ #ኢዜማ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር መምሪያ ቋሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ መስፍን አበበ ግንቦት 26/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱም ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ 8:00 ሰዓት በሽሮሜዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የፓርቲው አመራሮች እና አባላት በአባላችን በአቶ መስፍን አበበ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ኅዘን እየገለጽን ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።