👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
ተቋማዊ ባሕል በአንድ ድርጅት ውስጥ ያሉ አባላት የሚኖራቸው የጋራ አረዳድ፣ ከሌሎች ድርጅቶች አባላት የሚለያቸው እሴት እና ስለተቋማዊ ጉዳዮች የሚኖራቸው ተቀራራቢ አመለካከትን የሚያካትት ነው። ተቋማዊ ባሕል የአንድ ድርጅት አባላት ውሳኔ የመስጠት አቅማቸው፣ አዳዲስ አሠራሮችን ለመተግበር ያላቸውን ነፃነት፣ ድርጅታዊ ጉዳዮችን በጥልቀት የመመልከት ብቃታቸውን፣ ሂደትና ውጤት እንዲተሳሰሩ የማድረግ ችሎታቸውን፣ በጋራ ተናብበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኛነት እንዲሁም ለድርጅቱና ለሥራቸው ያላቸውን ተአማኒነትን የሚመለከት ጉዳይ ነው።
ከዚህ አንፃር ኢዜማ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከተለመደው የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀትና አሠራር የተለዩ ባሕሎችን ተግባራዊ አድርጓል። ኢዜማ ከሌሎች ድርጅቶች የሚለይባቸውን ባሕሎች ለመትከል ተንቀሳቅሷል። ይኹን እንጂ፤ የተጀመሩ በጎ ባሕሎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና አዳዲስ ድርጅታዊ ባሕሎችን ለመትከል የሚያስችል ጠንካራ አመራር አልተፈጠረም። በሊቀመንበር ደረጃ የሚመራው የኢዜማ የድርጅት ክንፍ በሚጠበቀው ልክ ለመምራት አለመቻሉ ጅምር ተቋማዊ ባሕሎች በአባላት ዘንድ እንዳይሰርፁ እንዲሁም አዳዲስ የአሠራር ሂደቶች ስላልተፈጠሩ አባላት እምቅ አቅማቸውን አውጥተው እንዳይጠቀሙ ኾኗል። በመኾኑም፤ ተቋማዊ ባሕል ለኢዜማ ውጤታማነት፣ አዳዲስ አሠራሮችን ለማስተዋወቅ እና የአባላትን እምቅ አቅም ለመጠቀም ያለውን ጠቃሚነት በመገንዘብ፤ አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከተቋማዊ ባሕል አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
#ኢዜማን_በልኩ !!
የዳበረ ተቋማዊ ባሕል
ተቋማዊ ባሕል በአንድ ድርጅት ውስጥ ያሉ አባላት የሚኖራቸው የጋራ አረዳድ፣ ከሌሎች ድርጅቶች አባላት የሚለያቸው እሴት እና ስለተቋማዊ ጉዳዮች የሚኖራቸው ተቀራራቢ አመለካከትን የሚያካትት ነው። ተቋማዊ ባሕል የአንድ ድርጅት አባላት ውሳኔ የመስጠት አቅማቸው፣ አዳዲስ አሠራሮችን ለመተግበር ያላቸውን ነፃነት፣ ድርጅታዊ ጉዳዮችን በጥልቀት የመመልከት ብቃታቸውን፣ ሂደትና ውጤት እንዲተሳሰሩ የማድረግ ችሎታቸውን፣ በጋራ ተናብበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኛነት እንዲሁም ለድርጅቱና ለሥራቸው ያላቸውን ተአማኒነትን የሚመለከት ጉዳይ ነው።
ከዚህ አንፃር ኢዜማ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከተለመደው የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀትና አሠራር የተለዩ ባሕሎችን ተግባራዊ አድርጓል። ኢዜማ ከሌሎች ድርጅቶች የሚለይባቸውን ባሕሎች ለመትከል ተንቀሳቅሷል። ይኹን እንጂ፤ የተጀመሩ በጎ ባሕሎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና አዳዲስ ድርጅታዊ ባሕሎችን ለመትከል የሚያስችል ጠንካራ አመራር አልተፈጠረም። በሊቀመንበር ደረጃ የሚመራው የኢዜማ የድርጅት ክንፍ በሚጠበቀው ልክ ለመምራት አለመቻሉ ጅምር ተቋማዊ ባሕሎች በአባላት ዘንድ እንዳይሰርፁ እንዲሁም አዳዲስ የአሠራር ሂደቶች ስላልተፈጠሩ አባላት እምቅ አቅማቸውን አውጥተው እንዳይጠቀሙ ኾኗል። በመኾኑም፤ ተቋማዊ ባሕል ለኢዜማ ውጤታማነት፣ አዳዲስ አሠራሮችን ለማስተዋወቅ እና የአባላትን እምቅ አቅም ለመጠቀም ያለውን ጠቃሚነት በመገንዘብ፤ አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከተቋማዊ ባሕል አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
የመዋቅርና የጽ/ቤቶቻችን ኹናቴ
የተወደዳችሁ የኢዜማ አባላትና የጉባዔ ተሳታፊዎች
ኢዜማን እንደገና በሚለው መሪ ቃላችን ውስጥ በጉልህ የሚታወሰው የመዋቅርና የምርጫ ክልሎቻችን አሁናዊ ገፅታ አንዱ ማሳያ ነው። ይህን ከሀገራችን ፖለቲካ ፓርቲዎች ልዩ ያደረገንን ከታች ወደ ላይ የተዘረጋውን መዋቅራዊ አደረጃጀታችን ወደ ምንፈልገው ተቋማዊ ማንነት ማድረስ እንደምንችል አምነንበት ነው። ፓርቲያችን ወደ መራጩ ህዝብ ለመድረስ መዋቅራዊ ይዘቱን ተቋማዊ ቅርፅ ማስያዝ ነው። ይህን ፓርቲ ከህዝባዊ ድጋፍ በተጨማሪ የተቋም ባለቤት ልናደርገው ይገባል። መላው ኢትዮጵያዊያን በየምርጫ ክልላቸው በጋራ በመግባባት ዘመናዊ ፖለቲካ የሚሰሩትን ኹናቴ ማመቻቸት ተቀዳሚ ተልዕኳችን ይሆናል።
ፓርቲያችን ኢዜማን ከሌሎች የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚለየው የአደረጃጀት መሠረቱን ከምርጫ ክልል መጀመሩ ነው። ይህ ፓርቲው ህዝባዊ መሠረት እንዲኖሩት ካደረጉት የኢዜማ አምዶች መካከል አንዱ ነው። ፓርቲያችን በትውልድ ቅብብሎሽ እንዲሄድ ከተፈለገ የማያቋርጥ የመዋቅር አደረጃጀት ክትትል ያስፈልገዋል። የማህበራዊ መሠረቱን ተደራሽነትና ስፋት እንደገና በማጥናት እንደየአስፈላጊነቱ የመዋቅር ማሻሻያም ሊያደርግ ይገባል። የኢዜማ ተቋማዊ መሰረት ከዋና ቢሮው በተጨማሪ ሌሎች ክረምት በጋ የሚሰሩ 24/7 ለአባሎቻችን ክፍት የሆኑ የፖለቲካ ስራ የሚሰራባቸው ተቋማዊ አደረጃጀቶችን መፍጠር አለበት።
በቀጣይ ለ3 ዓመታት በእናንተ ይሁንታ የፓርቲያችን ዋና ፀሐፊ ከሆንኩ በየመዋቅሩ የሚገኙ የምርጫ ክልሎችን ከመጎብኘት ባለፈ የእያንዳንዱ ጽ/ቤት ጉዳይ የዋና ቢሮው ጉዳይ ሆኖ ህግና አሰራር በሚፈቅደው መልኩ ሁሉም የምርጫ ክልሎች የተጠናከረ ተቋም እንዲኖራቸው ያለመታከት እሰራለሁ። የጠቅላላ ጉባዔው በሚሰጠኝና በቀጣይም የሚደራጀው የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ አቅጣጫ የኢዜማን ተቋማዊነት ከዋና ቢሮ ባሻገር ወደ መራጩ ህዝብ ልብ እንዲዘልቅ እሰራለሁ!
ኢዜማን እንደገና!
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የተወደዳችሁ የኢዜማ አባላትና የጉባዔ ተሳታፊዎች
ኢዜማን እንደገና በሚለው መሪ ቃላችን ውስጥ በጉልህ የሚታወሰው የመዋቅርና የምርጫ ክልሎቻችን አሁናዊ ገፅታ አንዱ ማሳያ ነው። ይህን ከሀገራችን ፖለቲካ ፓርቲዎች ልዩ ያደረገንን ከታች ወደ ላይ የተዘረጋውን መዋቅራዊ አደረጃጀታችን ወደ ምንፈልገው ተቋማዊ ማንነት ማድረስ እንደምንችል አምነንበት ነው። ፓርቲያችን ወደ መራጩ ህዝብ ለመድረስ መዋቅራዊ ይዘቱን ተቋማዊ ቅርፅ ማስያዝ ነው። ይህን ፓርቲ ከህዝባዊ ድጋፍ በተጨማሪ የተቋም ባለቤት ልናደርገው ይገባል። መላው ኢትዮጵያዊያን በየምርጫ ክልላቸው በጋራ በመግባባት ዘመናዊ ፖለቲካ የሚሰሩትን ኹናቴ ማመቻቸት ተቀዳሚ ተልዕኳችን ይሆናል።
ፓርቲያችን ኢዜማን ከሌሎች የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚለየው የአደረጃጀት መሠረቱን ከምርጫ ክልል መጀመሩ ነው። ይህ ፓርቲው ህዝባዊ መሠረት እንዲኖሩት ካደረጉት የኢዜማ አምዶች መካከል አንዱ ነው። ፓርቲያችን በትውልድ ቅብብሎሽ እንዲሄድ ከተፈለገ የማያቋርጥ የመዋቅር አደረጃጀት ክትትል ያስፈልገዋል። የማህበራዊ መሠረቱን ተደራሽነትና ስፋት እንደገና በማጥናት እንደየአስፈላጊነቱ የመዋቅር ማሻሻያም ሊያደርግ ይገባል። የኢዜማ ተቋማዊ መሰረት ከዋና ቢሮው በተጨማሪ ሌሎች ክረምት በጋ የሚሰሩ 24/7 ለአባሎቻችን ክፍት የሆኑ የፖለቲካ ስራ የሚሰራባቸው ተቋማዊ አደረጃጀቶችን መፍጠር አለበት።
በቀጣይ ለ3 ዓመታት በእናንተ ይሁንታ የፓርቲያችን ዋና ፀሐፊ ከሆንኩ በየመዋቅሩ የሚገኙ የምርጫ ክልሎችን ከመጎብኘት ባለፈ የእያንዳንዱ ጽ/ቤት ጉዳይ የዋና ቢሮው ጉዳይ ሆኖ ህግና አሰራር በሚፈቅደው መልኩ ሁሉም የምርጫ ክልሎች የተጠናከረ ተቋም እንዲኖራቸው ያለመታከት እሰራለሁ። የጠቅላላ ጉባዔው በሚሰጠኝና በቀጣይም የሚደራጀው የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ አቅጣጫ የኢዜማን ተቋማዊነት ከዋና ቢሮ ባሻገር ወደ መራጩ ህዝብ ልብ እንዲዘልቅ እሰራለሁ!
ኢዜማን እንደገና!
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ