Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
1. https://drive.google.com/file/d/1x3ZVOHM36elV1Eq89RXXA8JX7S9urJKn/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን በድምጽ ያድምጡ)
2. https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን ያንብቡ)
#ኢዜማ በልኩን ይምረጡ!!
#ኢዜማን_በልኩ !!
1. https://drive.google.com/file/d/1x3ZVOHM36elV1Eq89RXXA8JX7S9urJKn/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን በድምጽ ያድምጡ)
2. https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን ያንብቡ)
#ኢዜማ በልኩን ይምረጡ!!
የኢዜማ እንደገና ማሻሻያዎች
ኢዜማን እንደገና ለማሻሻል በጠቅላላ ጉባዔው ይሁንታን ካገኘንና ፓርቲያችንን የምናሻሽልበት አጋጣሚው ከተፈጠረ ምን ዓይነት ማሻሻያዎችን ለማድረግ አስበናል? የምናሻሽልበት ምክንያቶቻችን ላይ ከተስማማን ለምን እንደምናሻሽል ከተግባባን በቀጣይ ደግሞ ዋና ዋና ማሻሻያዎቻችን ምንድን ናቸው?
ከምርጫ ክልል ጀምሮ መሠረቱን ያፀና ትልቅ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ በየጊዜው ራሱን እያሻሻለ እስካልሄደ ድርስ ከግብ መድረስ አይቻለውም። ይህን ተከትሎ እኛ በመረጮቻችን በጎ ፍቃድ የፓርቲ ማሻሻያ ስራ እንድንሰራ አደራው ከተሰጠን በቀጣይ
1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች
2, ድርጅታዊ (መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች
3, ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንተገብራለን።
በሦስቱ ዓበይት የማሻሻያ ሀሳቦቻችን ዝርዝር ትንታኔዎችን የምንሰጥ ሲሆን ለአንባቢ በሚጠቅም መልኩ በአጭሩ ለማብራራት እንወዳለን።
1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎቻችን
ኢዜማ በፖለቲካ መስመር ጥራትና ቁርጠኝነት በሰፊው ህዝብ ዘንድ የታመነበት ፓርቲ መሆኑ ይታወቃል። ይህ የጠራ የፖለቲካ አረዳድ እና አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ የተሀድሶ አተገባበር ይከተላል። በጥንቃቄ የሚመራ የፖለቲካ ተሀድሶ ዋና መዳረሻው የዜግነት ፖለቲካ እና የማህበራዊ ፍትህ ማስፈን ሲሆን በሀገራዊ ሉዓላዊነት ላይና በዜጎች ደህንነት ላይ የተመረኮዘ ይሆናል። ኢዜማ በተሃድሶ ፕሮግራሙ የውስጠ ፓርቲ ፍትሃዊነትን: ስብጥርንና ዝግጁነትን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የአርቆ አሳቢዎች ቡድን (Think Tank) ቡድኖች ጋር በትብብር የሚሰራ: የማህበራዊ ፍትህ ተደራሽነትን በገለልተኝነት የሚከታተል አካል እና የኢትዮጵያን ሰላማዊ የውጭ ግንኙነቶችን የሚደግፍ የተልዕኮ ማዕቀፍ ያስፈልገዋል። ይህን ማድረጉ በቀጣይ ጊዜውን ለሚመጥን የፖሊሲ ዝግጅት ግብዓት ይሆነናል። ኢዜማ ያሉትን ፖሊሲዎችን ለአባላት ከማሳወቁ በፊት ከአሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመምከር ለሀገር ያለውን ጠቀሜታ በዝርዝር ለየመዋቅሮቾ እንዲያደርስ እናደርጋለን።
ኢዜማን እንደገና ለማደስ የተሃድሶ ስትራቴጂ ቀርፀን ፓርቲው የነበሩበትን ክፍተቶችን በማስተካከል ለአዲሱ የፖለቲካ ትውልድ መዳራሻ እናደርገዋለን። የጠቅላላ ጉባዔዎች ውሳኔዎቻችን እንደገና በመገምገም ከጊዜውና ከወቅቱ ጋር የሚሄዱትንና ከእኛ የሚጠበቁትን ውሳኔዎቻችን እናስቀጥላለን። በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያሳጡንን ውሳኔዎች ካገኘን የህዝብን ድምፅ በማክበር ውሳኔዎቻችን ዳግም እናጤናቸዋለን።
ፓርቲያችን የመሃል ከተማ ፓርቲ ብቻ እንዳይሆን ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመቅረብ ሰላማዊ ስልጡን ፖለቲካን እናራምዳለን። አባላት ብቻ ሳይሆኑ ደጋፊዎቻችንም በቀጣይ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶቻችን ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ሁኔታዎችን እናመቻቻለን።
በሀገራችን ከሚገኙ ከተለያዩ አሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመተባበር ኢዜማን ከሚገዳደሩ የዘርና የጎሳ ፖለቲካ ትርክቶች የሚያስወጡንን አሰላሳዮችን በማድመጥ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲ እንተጋለን።
2, ድርጅታዊ ( መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች
የፓርቲያችን ህልውና የሚፀናው ባለን መዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንደሆኑ ይታወቃል። የኢዜማ አደረጃጀት ከምርጫ ክልል የሚጀምር እና በተያዩ ደጋፊ: አስተባባሪና አጋዥ መዋቅሮች መደገፋቸው ፓርቲውን የሚያጠነክረው አካሄድ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ የሥራ ዘርፍ ሃላፊነት የሚታጨው አመራር ግን በብስአኮ የሚሾም ከሚሆን በፓርቲያችን የጠቅላላ ጉባዔ ተመራጭ ሆኖ ተወዳድሮ እንዲመረጥ ምክረ ሀሳብ እናቀርባለን። የድርጅት ጉዳይ ዘርፍን የሚመራው አካል የጉባዔ ተመራጭ ሆኖ በምርጫ እንዲሰየም እንጠይቃለን። ይህን የፓርቲያችን የጀርባ አጥንት የሚመራው አካል እንደሌሎች የስራ ክፍሎች በግለሰቦች በጎ ፍቃድ ላይ መወሰኑን አግባብነት የሌለው እንደሆነ እንረዳለን።
ፓርቲያችን በሚያንቀሳቅሳቸው የመዋቅር አደረጃጀቶች በሙሉ የምንስማማበት ሲሆን በተጨማሪነት የሚርጫ ክልሎችንና ለአሰራር እንዲመች ተብለው የተደራጁ የዞን ማስተባበሪያዎችን በቅርበት የሚያግዝ በክልል እና በከተማ አስተዳደሮች የሚንቀሳቀስ ተጨማሪ አጋዥ ጽ/ቤቶችን በመክፈት በቅርበት የምናግዝበት መንገድ እንፈጥራለን። ይህን በማድረግ በቀጣይ ለሚከናወነው ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ ብቡ አጋዥ መዋቅር እናደራጃለን።
የአዳዲስ አባላት ምልመላና ጥሪ ግብዣን በቋሚነት በየመንፈቅ ዓመቱ በየመዋቅሩ በዘመቻ መልክ እንዲሰራ እናደርጋለን። ጠቅላላ ጉባዔው ለሚቀጥሉት ጊዜያት በትጋት እንድናገለግለው ይሁንታ ከሰጠን በአባልነት መስፈርቶች ላይ ማሻሻያ እናደርጋለን። ለአብነት ያኽል ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ካለባቸው የፋይናንስ እጥረት በመነሳት በየምርጫ ክልላቸው ከሌሎች አባላት በግማሽ ያነሰ የአባልነት መዋጮ እንዲከፍሉ በማድረግ የወጣቶችን ተሳትፎ እናበረታታለን። ይህ ኢዜማ በአዲሱ ትውልድ ላይ ለሚሰራው የፖለቲካ ስራ አመቺ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያ እንተገብረዋለን።
ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ለውጥ አብዛኛው የሰው ልጅ ህልውና በዲጂታል ስርዓት የታገዘ በመሆኑ እኛ ከተመረጥን 'ዲጂታል ኢዜማ' የሚል ፕሮግራም በመቅረፅ ሰፊዎን መራጭ ህዝብ በስነ ዜጋ: በምርጫ: በዴሞክራሲ: በመብቶችና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲ ስራዎች ላይ በተከታታይ የሚሰራ ሀገር አቀፍ የዲጂታል ንቅናቄ በፓርቲ ደረጃ እንተገብራለን። የፓርቲው ድረ ገፅ በቀላሉ ከማሰራት በተጨማሪም አባላት በቀጥታ ስለፓርቲያቸው ሙሉ መረጃ የሚያገኙበትን መንገድ እንፈጥራለን። የሞባይል መተግበሪያዎችን በማሰራት የአባልነት ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ማናቸውም ነገሮች በዲጂታል ኢዜማ ክፍል እንዲሰራ እናስደርጋለን። በፓርቲያችን ዋና ጽ/ቤት የመረጃ ማከማቻ ቋት Cloud Archive ወደ ስራ በማስገባት ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን።
3, ተቋማዊ ማሻሻያዎች
ፓርቲያችን እስካሁን የመጣበትን ተቋማዊ ቅርፅ የበለጠ ጉልህና የሚታይ ለማድረግ የተወሰኑ ማሻሻያዎችን ማድረግ ተገቢ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ እንዲረዳ ተቋሙ በዋና ቢሮ ያሉትን የመምሪያ እና የስራ ክፍሎችን አዲስ በምናዋቅረው አጋዥ የክልሎችና የከተማ አስተዳድሮች ጽ/ቤቶች እናስፋፋለን። እነዚህ የጎንዮሽ ትዪዩ መምሪያዎች ወደ አጋዥ ቅርንጫፍ መዋቅሮቻችን የሚተባበሩበትንና በትስስር የሚሰሩበትን መመሪያዎችን የፓርቲያችን የህገ ደንብ ተርጓሚና አስፈፃሚ ኮሚቴ ካፀደቀልን ወደ ተግባር እንገባለን።
የሚደራጁ ጽ/ቤቶች ተቋሚ ይዘታቸውን ሳይለቁ ፈጣን ተደራሽ የመረጃ መለዋወጫ መስመር በመዘርጋት በየመዋቅሩ የሚደረጉ ፖለቲካዊ ተሳትፎአችን እናጠናክራል። በየደረጃው ያሉ መመሪያዎች: ደንቦና አሠራሮችን እጅግ ፈጣንና ለስራ ምቹ በሚሆኑ መልኩ ማሻሻያ እናስደርግባቸዋለን።
ኢዜማ እስከዛሬ ድረስ የፓርቲውን ፋይናንስ ስራ ከሌሎች አቻ ፓርቲዎች በተሻለ ሁኔታ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን የኢዜማ የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር (Treasurer) በሁለት የተከፈለ ስራ ሲኖረው የፋይናንስ እና የንብረት አስተዳደር ክፍሎች ብቻ ናቸው። ይህ በሁለት ዘርፎች የተከፈለውን አሰራር በነበረበት በባለሙያ ብቻ እንዲመራ በማድረግ መምሪያውን ከፖለቲካ ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ የባለሙያ ስራ እናደርገዋለን። ከዚህ ጋር በተቀራረበ ሁኔታ አብሮት የሚሰራ 'የሀብት አሰባሳቢ መምሪያ' ራሱን ችሎ እንዲደራጅና እንደሌሎች የሥራ ክፍሎች የሙሉ ጊዜ ስራው የኢዜማን ገቢ የማሳደግና ሀብት የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ራሱን የቻለ መምሪያ እንዲኖር እንሰራለን።
ኢዜማን እንደገና ለማሻሻል በጠቅላላ ጉባዔው ይሁንታን ካገኘንና ፓርቲያችንን የምናሻሽልበት አጋጣሚው ከተፈጠረ ምን ዓይነት ማሻሻያዎችን ለማድረግ አስበናል? የምናሻሽልበት ምክንያቶቻችን ላይ ከተስማማን ለምን እንደምናሻሽል ከተግባባን በቀጣይ ደግሞ ዋና ዋና ማሻሻያዎቻችን ምንድን ናቸው?
ከምርጫ ክልል ጀምሮ መሠረቱን ያፀና ትልቅ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ በየጊዜው ራሱን እያሻሻለ እስካልሄደ ድርስ ከግብ መድረስ አይቻለውም። ይህን ተከትሎ እኛ በመረጮቻችን በጎ ፍቃድ የፓርቲ ማሻሻያ ስራ እንድንሰራ አደራው ከተሰጠን በቀጣይ
1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች
2, ድርጅታዊ (መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች
3, ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንተገብራለን።
በሦስቱ ዓበይት የማሻሻያ ሀሳቦቻችን ዝርዝር ትንታኔዎችን የምንሰጥ ሲሆን ለአንባቢ በሚጠቅም መልኩ በአጭሩ ለማብራራት እንወዳለን።
1, ፖለቲካዊ ማሻሻያዎቻችን
ኢዜማ በፖለቲካ መስመር ጥራትና ቁርጠኝነት በሰፊው ህዝብ ዘንድ የታመነበት ፓርቲ መሆኑ ይታወቃል። ይህ የጠራ የፖለቲካ አረዳድ እና አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ የተሀድሶ አተገባበር ይከተላል። በጥንቃቄ የሚመራ የፖለቲካ ተሀድሶ ዋና መዳረሻው የዜግነት ፖለቲካ እና የማህበራዊ ፍትህ ማስፈን ሲሆን በሀገራዊ ሉዓላዊነት ላይና በዜጎች ደህንነት ላይ የተመረኮዘ ይሆናል። ኢዜማ በተሃድሶ ፕሮግራሙ የውስጠ ፓርቲ ፍትሃዊነትን: ስብጥርንና ዝግጁነትን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የአርቆ አሳቢዎች ቡድን (Think Tank) ቡድኖች ጋር በትብብር የሚሰራ: የማህበራዊ ፍትህ ተደራሽነትን በገለልተኝነት የሚከታተል አካል እና የኢትዮጵያን ሰላማዊ የውጭ ግንኙነቶችን የሚደግፍ የተልዕኮ ማዕቀፍ ያስፈልገዋል። ይህን ማድረጉ በቀጣይ ጊዜውን ለሚመጥን የፖሊሲ ዝግጅት ግብዓት ይሆነናል። ኢዜማ ያሉትን ፖሊሲዎችን ለአባላት ከማሳወቁ በፊት ከአሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመምከር ለሀገር ያለውን ጠቀሜታ በዝርዝር ለየመዋቅሮቾ እንዲያደርስ እናደርጋለን።
ኢዜማን እንደገና ለማደስ የተሃድሶ ስትራቴጂ ቀርፀን ፓርቲው የነበሩበትን ክፍተቶችን በማስተካከል ለአዲሱ የፖለቲካ ትውልድ መዳራሻ እናደርገዋለን። የጠቅላላ ጉባዔዎች ውሳኔዎቻችን እንደገና በመገምገም ከጊዜውና ከወቅቱ ጋር የሚሄዱትንና ከእኛ የሚጠበቁትን ውሳኔዎቻችን እናስቀጥላለን። በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያሳጡንን ውሳኔዎች ካገኘን የህዝብን ድምፅ በማክበር ውሳኔዎቻችን ዳግም እናጤናቸዋለን።
ፓርቲያችን የመሃል ከተማ ፓርቲ ብቻ እንዳይሆን ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመቅረብ ሰላማዊ ስልጡን ፖለቲካን እናራምዳለን። አባላት ብቻ ሳይሆኑ ደጋፊዎቻችንም በቀጣይ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶቻችን ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ሁኔታዎችን እናመቻቻለን።
በሀገራችን ከሚገኙ ከተለያዩ አሰላሳይ ቡድኖች ጋር በመተባበር ኢዜማን ከሚገዳደሩ የዘርና የጎሳ ፖለቲካ ትርክቶች የሚያስወጡንን አሰላሳዮችን በማድመጥ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲ እንተጋለን።
2, ድርጅታዊ ( መዋቅራዊ) ማሻሻያዎች
የፓርቲያችን ህልውና የሚፀናው ባለን መዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንደሆኑ ይታወቃል። የኢዜማ አደረጃጀት ከምርጫ ክልል የሚጀምር እና በተያዩ ደጋፊ: አስተባባሪና አጋዥ መዋቅሮች መደገፋቸው ፓርቲውን የሚያጠነክረው አካሄድ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ የሥራ ዘርፍ ሃላፊነት የሚታጨው አመራር ግን በብስአኮ የሚሾም ከሚሆን በፓርቲያችን የጠቅላላ ጉባዔ ተመራጭ ሆኖ ተወዳድሮ እንዲመረጥ ምክረ ሀሳብ እናቀርባለን። የድርጅት ጉዳይ ዘርፍን የሚመራው አካል የጉባዔ ተመራጭ ሆኖ በምርጫ እንዲሰየም እንጠይቃለን። ይህን የፓርቲያችን የጀርባ አጥንት የሚመራው አካል እንደሌሎች የስራ ክፍሎች በግለሰቦች በጎ ፍቃድ ላይ መወሰኑን አግባብነት የሌለው እንደሆነ እንረዳለን።
ፓርቲያችን በሚያንቀሳቅሳቸው የመዋቅር አደረጃጀቶች በሙሉ የምንስማማበት ሲሆን በተጨማሪነት የሚርጫ ክልሎችንና ለአሰራር እንዲመች ተብለው የተደራጁ የዞን ማስተባበሪያዎችን በቅርበት የሚያግዝ በክልል እና በከተማ አስተዳደሮች የሚንቀሳቀስ ተጨማሪ አጋዥ ጽ/ቤቶችን በመክፈት በቅርበት የምናግዝበት መንገድ እንፈጥራለን። ይህን በማድረግ በቀጣይ ለሚከናወነው ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ ብቡ አጋዥ መዋቅር እናደራጃለን።
የአዳዲስ አባላት ምልመላና ጥሪ ግብዣን በቋሚነት በየመንፈቅ ዓመቱ በየመዋቅሩ በዘመቻ መልክ እንዲሰራ እናደርጋለን። ጠቅላላ ጉባዔው ለሚቀጥሉት ጊዜያት በትጋት እንድናገለግለው ይሁንታ ከሰጠን በአባልነት መስፈርቶች ላይ ማሻሻያ እናደርጋለን። ለአብነት ያኽል ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ካለባቸው የፋይናንስ እጥረት በመነሳት በየምርጫ ክልላቸው ከሌሎች አባላት በግማሽ ያነሰ የአባልነት መዋጮ እንዲከፍሉ በማድረግ የወጣቶችን ተሳትፎ እናበረታታለን። ይህ ኢዜማ በአዲሱ ትውልድ ላይ ለሚሰራው የፖለቲካ ስራ አመቺ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያ እንተገብረዋለን።
ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ለውጥ አብዛኛው የሰው ልጅ ህልውና በዲጂታል ስርዓት የታገዘ በመሆኑ እኛ ከተመረጥን 'ዲጂታል ኢዜማ' የሚል ፕሮግራም በመቅረፅ ሰፊዎን መራጭ ህዝብ በስነ ዜጋ: በምርጫ: በዴሞክራሲ: በመብቶችና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲ ስራዎች ላይ በተከታታይ የሚሰራ ሀገር አቀፍ የዲጂታል ንቅናቄ በፓርቲ ደረጃ እንተገብራለን። የፓርቲው ድረ ገፅ በቀላሉ ከማሰራት በተጨማሪም አባላት በቀጥታ ስለፓርቲያቸው ሙሉ መረጃ የሚያገኙበትን መንገድ እንፈጥራለን። የሞባይል መተግበሪያዎችን በማሰራት የአባልነት ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ማናቸውም ነገሮች በዲጂታል ኢዜማ ክፍል እንዲሰራ እናስደርጋለን። በፓርቲያችን ዋና ጽ/ቤት የመረጃ ማከማቻ ቋት Cloud Archive ወደ ስራ በማስገባት ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን።
3, ተቋማዊ ማሻሻያዎች
ፓርቲያችን እስካሁን የመጣበትን ተቋማዊ ቅርፅ የበለጠ ጉልህና የሚታይ ለማድረግ የተወሰኑ ማሻሻያዎችን ማድረግ ተገቢ ነው ብለን እናምናለን። ለዚህ እንዲረዳ ተቋሙ በዋና ቢሮ ያሉትን የመምሪያ እና የስራ ክፍሎችን አዲስ በምናዋቅረው አጋዥ የክልሎችና የከተማ አስተዳድሮች ጽ/ቤቶች እናስፋፋለን። እነዚህ የጎንዮሽ ትዪዩ መምሪያዎች ወደ አጋዥ ቅርንጫፍ መዋቅሮቻችን የሚተባበሩበትንና በትስስር የሚሰሩበትን መመሪያዎችን የፓርቲያችን የህገ ደንብ ተርጓሚና አስፈፃሚ ኮሚቴ ካፀደቀልን ወደ ተግባር እንገባለን።
የሚደራጁ ጽ/ቤቶች ተቋሚ ይዘታቸውን ሳይለቁ ፈጣን ተደራሽ የመረጃ መለዋወጫ መስመር በመዘርጋት በየመዋቅሩ የሚደረጉ ፖለቲካዊ ተሳትፎአችን እናጠናክራል። በየደረጃው ያሉ መመሪያዎች: ደንቦና አሠራሮችን እጅግ ፈጣንና ለስራ ምቹ በሚሆኑ መልኩ ማሻሻያ እናስደርግባቸዋለን።
ኢዜማ እስከዛሬ ድረስ የፓርቲውን ፋይናንስ ስራ ከሌሎች አቻ ፓርቲዎች በተሻለ ሁኔታ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን የኢዜማ የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር (Treasurer) በሁለት የተከፈለ ስራ ሲኖረው የፋይናንስ እና የንብረት አስተዳደር ክፍሎች ብቻ ናቸው። ይህ በሁለት ዘርፎች የተከፈለውን አሰራር በነበረበት በባለሙያ ብቻ እንዲመራ በማድረግ መምሪያውን ከፖለቲካ ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ የባለሙያ ስራ እናደርገዋለን። ከዚህ ጋር በተቀራረበ ሁኔታ አብሮት የሚሰራ 'የሀብት አሰባሳቢ መምሪያ' ራሱን ችሎ እንዲደራጅና እንደሌሎች የሥራ ክፍሎች የሙሉ ጊዜ ስራው የኢዜማን ገቢ የማሳደግና ሀብት የማሰባሰብ ስራን የሚሰራ ራሱን የቻለ መምሪያ እንዲኖር እንሰራለን።
Telegram
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሃላፊን ከፖለቲካ አመራርነት ይልቅ በብቁ ባለሙያዎች እንዲመሩት እናስደርጋለን። የፋይናንስ ሃላፊውም ከጉባዔ ተመራጭነታቸው ይልቅ በሙያ ታምኖባቸው በግልፅ የማስታወቅያ የሚቀጠሩ የዘርፉ ሀላፊ እንዲኖሩት የጠቅላላ ጉባዔውን እንጠይቃለን።
ኢዜማን እንደገና!
ጌታቸው ጳውሎስ-ዕጩ ሊቀመንበር
ኤልሳቤጥ ሉቃስ-ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ-ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የቃል ኪዳን ሰነዳችን ሙሉውን ለማንበብ ከታች በተቀመጠው የቴሌግራም መስፈንጠሪያ በመግባት ማገኘት ይችላሉ።
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
ኢዜማን እንደገና!
ጌታቸው ጳውሎስ-ዕጩ ሊቀመንበር
ኤልሳቤጥ ሉቃስ-ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ-ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የቃል ኪዳን ሰነዳችን ሙሉውን ለማንበብ ከታች በተቀመጠው የቴሌግራም መስፈንጠሪያ በመግባት ማገኘት ይችላሉ።
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
Telegram
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
1. https://drive.google.com/file/d/1x3ZVOHM36elV1Eq89RXXA8JX7S9urJKn/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን በድምጽ ያድምጡ)
2. https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን ያንብቡ)
#ኢዜማ በልኩን ይምረጡ!!
#ኢዜማን_በልኩ !!
1. https://drive.google.com/file/d/1x3ZVOHM36elV1Eq89RXXA8JX7S9urJKn/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን በድምጽ ያድምጡ)
2. https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk (ማኒፌስቶውን ያንብቡ)
#ኢዜማ በልኩን ይምረጡ!!
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለ #ኢዜማ ን በልኩ ከተሠጡ የድጋፍ ድምፆች በጥቂቱ ይመልከቱ።
ሐ/ ደረጀውን የጠበቀ የጎንዮሽ ትስስር ከተለያዩ መምሪያዎች ጋር እፈጥራለሁ። ለአብነት ያኽል የህዝብ ግንኙነት መምሪያ: የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር መምሪያ: የወጣቶች ሴቶችና አካል ጉዳተኞች መምሪያ: የሙያና የሠራተኛ ማህበራት መምሪያዎችና ሌሎች መምሪያዎች ጋር የጠበቀ የሥራ ግንኙነት በማድረግ ለትጋት እታትራለሁ
መ/ በዋና ቢሯችን የዲጂታል መረጃ አርካይቭ በማደራጀት ከዚህ በኋላ ያሉ ማንኛውም የኢዜማ ስራዎችን በዲጂታል መልኩ እንዲቀመጥና በተፈለገ ሰዓት አገልግሎት ላይ እንዲውል አደርጋለሁ።
ሠ/ በየሩብ ዓመቱ የጽ/ቤት ስራዎችን ምዘና ለብስአኮ እና ለአባላት ይፋ በማድረግ ግልፀኝነትን አሰፍናለው።
ረ/ በክልል ደረጃ ለሚደራጁ አጋዥ ጽ/ቤቶች የተሟላ ቁሳቁስ እንዲኖር ከረድዔት ድርጅቶችን ረጂ ግለሰቦች ጋር በመነጋገር ሁሉም የኢዜማ መዋቅር አጋዥ ጽ/ቤቶች የቢሮ ቁሳቁስ እንዲሟላ እሰራለሁ።
ሰ/ አዲስ ለምናዋቅራቸው የክልል አጋዥ ጽ/ቤቶች ድጋፍ የሚውሉ 'መቶ ብር ለፍትህ!' የሚል ዘመቻ በማስተባበር በየአካባቢው ከሚገኙ አባላት እና ደጋፊዎች ጋር የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ጽ/ቤቶቹ እንዲጠናከሩ እሰራለሁ!
ሸ/ የፓርቲያችን የሆሉም ጽ/ቤት ፀሐፊዎች በየ4 ወሩ በኢዜማ አካዳሚ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንዲወስዱና ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲጨብጡ እሰራለሁ።
የተከበራችሁ የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች
ከላይ በመግቢያዬ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ይህ የእኔ ህልም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢዜማዊ የጋራ ራዕይ ነውና ይህን ዕቅዳችን ለመተግበርና አተገባበሩን ለመከታተል በጉባዔው ዕለት በሚደረገው የዋና ፀሐፊነት ቦታ ላይ እንድትመርጡኝ ስል በታላቅ ትህትና እጠይቃችኋለሁ!
ኢዜማን እንደገና!
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የቃል ኪዳን ሰነዱን ለማገኘት
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
መ/ በዋና ቢሯችን የዲጂታል መረጃ አርካይቭ በማደራጀት ከዚህ በኋላ ያሉ ማንኛውም የኢዜማ ስራዎችን በዲጂታል መልኩ እንዲቀመጥና በተፈለገ ሰዓት አገልግሎት ላይ እንዲውል አደርጋለሁ።
ሠ/ በየሩብ ዓመቱ የጽ/ቤት ስራዎችን ምዘና ለብስአኮ እና ለአባላት ይፋ በማድረግ ግልፀኝነትን አሰፍናለው።
ረ/ በክልል ደረጃ ለሚደራጁ አጋዥ ጽ/ቤቶች የተሟላ ቁሳቁስ እንዲኖር ከረድዔት ድርጅቶችን ረጂ ግለሰቦች ጋር በመነጋገር ሁሉም የኢዜማ መዋቅር አጋዥ ጽ/ቤቶች የቢሮ ቁሳቁስ እንዲሟላ እሰራለሁ።
ሰ/ አዲስ ለምናዋቅራቸው የክልል አጋዥ ጽ/ቤቶች ድጋፍ የሚውሉ 'መቶ ብር ለፍትህ!' የሚል ዘመቻ በማስተባበር በየአካባቢው ከሚገኙ አባላት እና ደጋፊዎች ጋር የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ጽ/ቤቶቹ እንዲጠናከሩ እሰራለሁ!
ሸ/ የፓርቲያችን የሆሉም ጽ/ቤት ፀሐፊዎች በየ4 ወሩ በኢዜማ አካዳሚ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንዲወስዱና ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲጨብጡ እሰራለሁ።
የተከበራችሁ የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች
ከላይ በመግቢያዬ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ይህ የእኔ ህልም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢዜማዊ የጋራ ራዕይ ነውና ይህን ዕቅዳችን ለመተግበርና አተገባበሩን ለመከታተል በጉባዔው ዕለት በሚደረገው የዋና ፀሐፊነት ቦታ ላይ እንድትመርጡኝ ስል በታላቅ ትህትና እጠይቃችኋለሁ!
ኢዜማን እንደገና!
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
የቃል ኪዳን ሰነዱን ለማገኘት
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
Telegram
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
የተከበራችሁ የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ተሳታፊዎች
የተከበራችሁ የኢዜማ የየመዋቅሩ አመራሮችና አባላት
የተከበራችሁ የኢዜማ ደጋፊዎችና ኢትዮጵያዊያን
ዛሬ ወደ እናንተ ቀርቤ መልዕክት የማስተላልፈው በከንቱ እንድትደግፉሽ ብቻ ሳይሆን በኢዜማ የፖለቲካ ሥራ ላይና በሀገራችን እንዲሰፍን ከሚፈልገው የፖለቲካ አሰራር መሻት የመነጨ ህልሜን ነው የማጋራችሁ። ይህ የኔ የግል ራዕይ ሳይሆን ለፓርቲያችን ህልውና የሚቀጥልበት እና ሀገራችን የሚፈውሰውን ፖለቲካ የምንሰራበት ራዕይ ነው።
ዛሬ ይህንን ዕድል አግኝቼ በፊታችሁ ለመመረጥ በዕጩነት ስቀርብ በቀጣይ ዓመታት በተወዳደርኩበት የአገልግሎት ቦታ የሀገራችን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲ አሰራር ለማዘመን ነው። ይህ ለእኛ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። በመንታ መንገድ ላይ ለተወዛገበው የፖለቲካ ትግላችንና ለመፃዒው የሀገራችን ዕድል ፋንታ የምንቀይስበት የታሪክ እጥፋት ነው። ዜጎች አጥብቀው የሚሹትን የፍትህ ስርዓት እንዲሰፍን: በየፊናው የሚሰማውን የድረሱልን ተማፅኖ: በቅርቡ እየተንሰራፋ የመጣውን ተስፋ የመቁረጥ አዝማሚያ ምላሽ እንዲያገኝ የተደራጀና የዘመነ የፖለቲካ ትግል ማድረግ አንድ አማራጭ ነው። የሀገራችን ጥያቄዎች ለመመለስ ለምናቀርበው የፖለቲካ ጥያቄ ራሱን የቻለ ዘመናዊ የፖለቲካ ፓርቲ አሰራሮችን መንደፍ ይጠበቅብናል። ለዚህ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው።
ይህን የምናሳካው በፓርቲያችን ጥንቃረ: አደረጃጀት: የውስጥ ሥራና ህዝባዊ አንድነት ነው። ኢዜማን እንደገና የምናደራጅበትና ወደ መነሻ ዓለማው የምንመልስበት ወቅት ዛሬ ነው።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና በማለት እዚህ በፊታችሁ ስቀርብ የፓርቲያችን ገፅታ ከቀደመው በተሻለ መልኩ ለማስተካከል የፓርቲው ማዕጰላዊ ጽ/ቤት ገፅታን ማዘመን ተገቢ ነው። የፖለቲካ ፓርቲ ሥራን ከዋና ጽ/ቤት በሚሰራው ስራ ያማረና የተሻለ ለማድረግ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል። የፓርቲያችን ጽ/ቤት የየዕለት ተግባር መተግበር: መረጃ ማደራጀት: ስብሰባዎችን ማመቻቸት ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የዜግነት ፖለቲካ እና ማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች የልብ ማረፊና እምነት የሚጣልበት ተቋም መገንባት ነው። በቀጣይ ምርጫ በፓርቲያችን የከፍተኛ ስልጣን ባለቤት በሆነው በጠቅላላ ጉባዔያችን ይህንን ታላቅ አደራና የቤት ሥራ ስትሰጡኝ ፓርቲያችን ጉልህ: የሚታይ ራዕይና ተጠያቂነትን መርሁ ያደረገ የፖለቲካ ትግል ማዕከል እናደርገዋለን።
ኢዜማን እንደገና!
ከቢሮክራሲ እስራት ወደ ልህቀት
በህገ ደንባችን ላይ በተሰጠን ሀላፊነትና ተግባር ከማዕከላዊ ቢሮው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተጠናከረ አደረጃጀት እንዲኖረን ጽ/ቤቶችንና ቢሯቸውን ያለማቋረጥ የሚደረግ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ወደ መደበኛ የሰላማዊ ፖለቲካ ትግል እናስገባቸዋለን። በዋና ቢሮም ሆነ በየመዋቅሩ የሚወሰኑ የተለያዩ ውሳኔዎችን ክትትል በማድረግ አፈፃፀማቸውንና ተግባራዊነታቸውን በቋሚነት መከታተል። በሀገራችን እንዲኖር የምንፈልገውን ተጠያቂነት በመጀመሪያ በፓርቲያችንና በራሳችን እንጀምረዋለን። ተጠያቂነት የሌለውን የፖለቲካ ፓርቲ የሚመርጠው አካል ስለሌለ በቅድሚያ ከራሳችን መዋቅሮች በማስጀመር ተጠያቂነትን እናሰፍናለን።
ይህንን ለማሳካት
1, በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ: በሰለጠኑና ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች: ግልፀኝነት በተሞላው አሰራር: ተጠያቂነትን እናሰፍናለን
2, ብያንስ የማዕከላዊ ቢሮው የሚቆጣጠረው በእያንዳንዱ የክልል ከተሞችና የከተማ አስተዳደሮች ውስጥ የፓርቲያችን አደረጃጀቶችን የሚደግፍ የጽ/ቤት ቢሮ እንዲኖር እንሰራለን
3, በየመዋቅሩ አጋዥ ቢሮ ለመክፈት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ እናስጀምራለን
4, የኢዜማ ቅርጫፍ ጽ/ቤቶችን እንቅስቃሴ ለአባሉ በየጊዜው ለማድረስ የመረጃ ማሰራጫ መንገድ እንፈጥራለን
የተጠናከረና የጎላ አስተዋፅዖ ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ለማድረግ የዜጎች: የማህበራት: የመደብና ሌሎች የትግል አቅጣጫዎችን በመከተል ሀገራችንን ያቆረቆዛትን የብሔር: የጎሳና ተመሳሳይ የፖለቲካ ትግሎችን በጋራ እናከስማቸዋለን።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና ለማጠናከር የፓርቲው ጽ/ቤቶችን ማጠናከር ቅድሚያ የምሰጠው ጉዳይ ነው። በተቻለን መጠን በዋና ቢሮ ስር የሚደራጁ የክልል አጋዥ ጽ/ቤቶች የየራሳቸው የሚያስፈልጋቸውን ተቋማዊ ቁሳቁሶችን ከተለያዩ አካላት ጋር በመነጋገር እናሟላቸዋለን። በዋና ቢሮ ደረጃም የቬርችዋል የርቀት ስብሰባ ማከናወኛ smart room ወደ ሥራ እናስገባለን። ከአባላትና ከየምርጫ ክልሉ የሚመጡትን ጥያቄዎችን በ48 ሰዓታት ውስጥ ምላሽ እየሰጠን የፍትህ ጥያቄውን እናሳልጣለን።
ይህን ለማድረግ እና በጋራ ለማሳካት የሚከተሉትን መንገዶች እንጠቀማለን
ስትራቴጂካዊ የአመራር ጥበብ
የፓርቲያችን ዋና ፀሐፊ ከሆንኩ ትልቁ ሥራዬ የኢዜማን ሀሳብና ራዕይ ወደ ተግባር የመቀየር ስራ ነው። በዋና ጽ/ቤት የሚገኙ መምሪያዎች ጋር በጥምረት በመሆን ፈጣን: ቀልጣ እና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት ነው።
የመፈፀም ብቃት ማሳደግ
ፓርቲያችን ባለው ውስን የሰው ሀይል በመጠቀም በየዕለቱ የሚሰጡንን ስራዎችን በተገቢው መንገድ መፈፀም ትልቁ የስኬት ቁልፍ ነው። የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴውን ውሳኔ በመከተል ተግባራዊነታቸውን እየተከታተልኩ መደገፍ እችላለሁ።
የተጠናከረ ወዳጅነት
የሀገራችን የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄ ለማስፈፀም ብዙ የሰው ሀይል የሚጠይቅ ስራ ቢሆንም ካሉን ሁሉም የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች ጋር የተጠናከረ ወዳጅነት በመፍጠር የፓርቲ ተልዕኳችን ከወረቀትና ከምዕናብ ሀሳብ ወደ ተግባር እቀይረዋለሁ።
ውጥረትን ማርገብ
ሀገራዊ የፖለቲካ ውጥረቶችን ለማርገብ የፓርቲያችን ውጥረቶችን መክሰም ይቀላልና በተቻለ መጠን በኢዜማ ውስጥ ያሉ የተለያዩ ውጥረቶችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመቀናጀት ሰላማዊ የሥራ ከባቢን እፈጥራለሁ። ይህ በተለያዩ ውጥረቶች ምክንያት እየተራዘመ ያለውን የህዝባችን ፖለቲካዊ ጥያቄ የሚመለስበት ጊዜ ያሳጥራል።
ቁርጠኝነትን ማጉላት
ሁሉም የኢዜማ አባል ላመነበት ፍትሃዊ ጥያቄ እስከመጨረሻም የሚታገል ቁርጠኛ እንደሆነ ይታወቃል። ለዚህማ ማሳያነት እስከዛሬ ኢዜማን በሙሉ ጊዜዬ ሳገለግል አንዳች ቀን እንኳን ሰንፌ አላውቅም። ይህን በነፃ ለኢትዮጵያ የማደርገውን በዋጋ የማይተመን ትግል በቀጣይም ለሌሎች አርዓያ በሚሆን መልኩ በቁርጠኝነት አገለግላለሁ።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና ስንል የፖለቲካ ፓርቲን የመምራትና ተቋማዊነትን ማዘመን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል በአዲስ ገፅታ መገንባት ማለታችን እንደሆነ ይታወቅልን። ለዚህም የህዝባችን ክብር በሚመጥን መልኩ የዘመነና የተጠናከረ የፖለቲካ ፓርቲ እናደርገዋለን ማለታችን ነው።
በቀጣይ በዋና ፀሐፊነት ሳገለግላችሁ የሚከተሉትን ዓበይት ተግባራትን እንደምተገብርላችሁ ለማረጋገጥ እወዳለሁ:
ሀ/ በአሁኑ ወቅት ያለውን እጅግ የተዳከመ እና ልል ተጠያቂነት ያለውን የኢዜማ ማዕከላዊ ቢሮ ዘመኑን በዋጀ የአገልግሎት ጥራት: ተጠያቂነቱ የተንሰራፋ በባለሙያ የሚመራ ተቋም: እና መረጃ እና መርህ ተኮር የአሰራር ስርዓት እዘረጋለሁ።
ለ/ የጽ/ቤት የአፈፃፀምና የማስፈፀም አቅምን የሚመዝን ወራዊ የተግባር ምዘና ስርዓት እዘረጋለሁ: የፓርቲው ውሳኔዎች: የአባላትና የመዋቅር ጥያቄዎችን: የሦስተኛ ወገን የደብዳቤ ግንኙነቶችን በብቃት አሳልጣለሁ
የተከበራችሁ የኢዜማ የየመዋቅሩ አመራሮችና አባላት
የተከበራችሁ የኢዜማ ደጋፊዎችና ኢትዮጵያዊያን
ዛሬ ወደ እናንተ ቀርቤ መልዕክት የማስተላልፈው በከንቱ እንድትደግፉሽ ብቻ ሳይሆን በኢዜማ የፖለቲካ ሥራ ላይና በሀገራችን እንዲሰፍን ከሚፈልገው የፖለቲካ አሰራር መሻት የመነጨ ህልሜን ነው የማጋራችሁ። ይህ የኔ የግል ራዕይ ሳይሆን ለፓርቲያችን ህልውና የሚቀጥልበት እና ሀገራችን የሚፈውሰውን ፖለቲካ የምንሰራበት ራዕይ ነው።
ዛሬ ይህንን ዕድል አግኝቼ በፊታችሁ ለመመረጥ በዕጩነት ስቀርብ በቀጣይ ዓመታት በተወዳደርኩበት የአገልግሎት ቦታ የሀገራችን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲ አሰራር ለማዘመን ነው። ይህ ለእኛ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። በመንታ መንገድ ላይ ለተወዛገበው የፖለቲካ ትግላችንና ለመፃዒው የሀገራችን ዕድል ፋንታ የምንቀይስበት የታሪክ እጥፋት ነው። ዜጎች አጥብቀው የሚሹትን የፍትህ ስርዓት እንዲሰፍን: በየፊናው የሚሰማውን የድረሱልን ተማፅኖ: በቅርቡ እየተንሰራፋ የመጣውን ተስፋ የመቁረጥ አዝማሚያ ምላሽ እንዲያገኝ የተደራጀና የዘመነ የፖለቲካ ትግል ማድረግ አንድ አማራጭ ነው። የሀገራችን ጥያቄዎች ለመመለስ ለምናቀርበው የፖለቲካ ጥያቄ ራሱን የቻለ ዘመናዊ የፖለቲካ ፓርቲ አሰራሮችን መንደፍ ይጠበቅብናል። ለዚህ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው።
ይህን የምናሳካው በፓርቲያችን ጥንቃረ: አደረጃጀት: የውስጥ ሥራና ህዝባዊ አንድነት ነው። ኢዜማን እንደገና የምናደራጅበትና ወደ መነሻ ዓለማው የምንመልስበት ወቅት ዛሬ ነው።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና በማለት እዚህ በፊታችሁ ስቀርብ የፓርቲያችን ገፅታ ከቀደመው በተሻለ መልኩ ለማስተካከል የፓርቲው ማዕጰላዊ ጽ/ቤት ገፅታን ማዘመን ተገቢ ነው። የፖለቲካ ፓርቲ ሥራን ከዋና ጽ/ቤት በሚሰራው ስራ ያማረና የተሻለ ለማድረግ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል። የፓርቲያችን ጽ/ቤት የየዕለት ተግባር መተግበር: መረጃ ማደራጀት: ስብሰባዎችን ማመቻቸት ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የዜግነት ፖለቲካ እና ማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች የልብ ማረፊና እምነት የሚጣልበት ተቋም መገንባት ነው። በቀጣይ ምርጫ በፓርቲያችን የከፍተኛ ስልጣን ባለቤት በሆነው በጠቅላላ ጉባዔያችን ይህንን ታላቅ አደራና የቤት ሥራ ስትሰጡኝ ፓርቲያችን ጉልህ: የሚታይ ራዕይና ተጠያቂነትን መርሁ ያደረገ የፖለቲካ ትግል ማዕከል እናደርገዋለን።
ኢዜማን እንደገና!
ከቢሮክራሲ እስራት ወደ ልህቀት
በህገ ደንባችን ላይ በተሰጠን ሀላፊነትና ተግባር ከማዕከላዊ ቢሮው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተጠናከረ አደረጃጀት እንዲኖረን ጽ/ቤቶችንና ቢሯቸውን ያለማቋረጥ የሚደረግ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ወደ መደበኛ የሰላማዊ ፖለቲካ ትግል እናስገባቸዋለን። በዋና ቢሮም ሆነ በየመዋቅሩ የሚወሰኑ የተለያዩ ውሳኔዎችን ክትትል በማድረግ አፈፃፀማቸውንና ተግባራዊነታቸውን በቋሚነት መከታተል። በሀገራችን እንዲኖር የምንፈልገውን ተጠያቂነት በመጀመሪያ በፓርቲያችንና በራሳችን እንጀምረዋለን። ተጠያቂነት የሌለውን የፖለቲካ ፓርቲ የሚመርጠው አካል ስለሌለ በቅድሚያ ከራሳችን መዋቅሮች በማስጀመር ተጠያቂነትን እናሰፍናለን።
ይህንን ለማሳካት
1, በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ: በሰለጠኑና ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች: ግልፀኝነት በተሞላው አሰራር: ተጠያቂነትን እናሰፍናለን
2, ብያንስ የማዕከላዊ ቢሮው የሚቆጣጠረው በእያንዳንዱ የክልል ከተሞችና የከተማ አስተዳደሮች ውስጥ የፓርቲያችን አደረጃጀቶችን የሚደግፍ የጽ/ቤት ቢሮ እንዲኖር እንሰራለን
3, በየመዋቅሩ አጋዥ ቢሮ ለመክፈት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ እናስጀምራለን
4, የኢዜማ ቅርጫፍ ጽ/ቤቶችን እንቅስቃሴ ለአባሉ በየጊዜው ለማድረስ የመረጃ ማሰራጫ መንገድ እንፈጥራለን
የተጠናከረና የጎላ አስተዋፅዖ ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ለማድረግ የዜጎች: የማህበራት: የመደብና ሌሎች የትግል አቅጣጫዎችን በመከተል ሀገራችንን ያቆረቆዛትን የብሔር: የጎሳና ተመሳሳይ የፖለቲካ ትግሎችን በጋራ እናከስማቸዋለን።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና ለማጠናከር የፓርቲው ጽ/ቤቶችን ማጠናከር ቅድሚያ የምሰጠው ጉዳይ ነው። በተቻለን መጠን በዋና ቢሮ ስር የሚደራጁ የክልል አጋዥ ጽ/ቤቶች የየራሳቸው የሚያስፈልጋቸውን ተቋማዊ ቁሳቁሶችን ከተለያዩ አካላት ጋር በመነጋገር እናሟላቸዋለን። በዋና ቢሮ ደረጃም የቬርችዋል የርቀት ስብሰባ ማከናወኛ smart room ወደ ሥራ እናስገባለን። ከአባላትና ከየምርጫ ክልሉ የሚመጡትን ጥያቄዎችን በ48 ሰዓታት ውስጥ ምላሽ እየሰጠን የፍትህ ጥያቄውን እናሳልጣለን።
ይህን ለማድረግ እና በጋራ ለማሳካት የሚከተሉትን መንገዶች እንጠቀማለን
ስትራቴጂካዊ የአመራር ጥበብ
የፓርቲያችን ዋና ፀሐፊ ከሆንኩ ትልቁ ሥራዬ የኢዜማን ሀሳብና ራዕይ ወደ ተግባር የመቀየር ስራ ነው። በዋና ጽ/ቤት የሚገኙ መምሪያዎች ጋር በጥምረት በመሆን ፈጣን: ቀልጣ እና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት ነው።
የመፈፀም ብቃት ማሳደግ
ፓርቲያችን ባለው ውስን የሰው ሀይል በመጠቀም በየዕለቱ የሚሰጡንን ስራዎችን በተገቢው መንገድ መፈፀም ትልቁ የስኬት ቁልፍ ነው። የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴውን ውሳኔ በመከተል ተግባራዊነታቸውን እየተከታተልኩ መደገፍ እችላለሁ።
የተጠናከረ ወዳጅነት
የሀገራችን የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄ ለማስፈፀም ብዙ የሰው ሀይል የሚጠይቅ ስራ ቢሆንም ካሉን ሁሉም የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች ጋር የተጠናከረ ወዳጅነት በመፍጠር የፓርቲ ተልዕኳችን ከወረቀትና ከምዕናብ ሀሳብ ወደ ተግባር እቀይረዋለሁ።
ውጥረትን ማርገብ
ሀገራዊ የፖለቲካ ውጥረቶችን ለማርገብ የፓርቲያችን ውጥረቶችን መክሰም ይቀላልና በተቻለ መጠን በኢዜማ ውስጥ ያሉ የተለያዩ ውጥረቶችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመቀናጀት ሰላማዊ የሥራ ከባቢን እፈጥራለሁ። ይህ በተለያዩ ውጥረቶች ምክንያት እየተራዘመ ያለውን የህዝባችን ፖለቲካዊ ጥያቄ የሚመለስበት ጊዜ ያሳጥራል።
ቁርጠኝነትን ማጉላት
ሁሉም የኢዜማ አባል ላመነበት ፍትሃዊ ጥያቄ እስከመጨረሻም የሚታገል ቁርጠኛ እንደሆነ ይታወቃል። ለዚህማ ማሳያነት እስከዛሬ ኢዜማን በሙሉ ጊዜዬ ሳገለግል አንዳች ቀን እንኳን ሰንፌ አላውቅም። ይህን በነፃ ለኢትዮጵያ የማደርገውን በዋጋ የማይተመን ትግል በቀጣይም ለሌሎች አርዓያ በሚሆን መልኩ በቁርጠኝነት አገለግላለሁ።
ክቡራንና ክቡራት
ኢዜማን እንደገና ስንል የፖለቲካ ፓርቲን የመምራትና ተቋማዊነትን ማዘመን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል በአዲስ ገፅታ መገንባት ማለታችን እንደሆነ ይታወቅልን። ለዚህም የህዝባችን ክብር በሚመጥን መልኩ የዘመነና የተጠናከረ የፖለቲካ ፓርቲ እናደርገዋለን ማለታችን ነው።
በቀጣይ በዋና ፀሐፊነት ሳገለግላችሁ የሚከተሉትን ዓበይት ተግባራትን እንደምተገብርላችሁ ለማረጋገጥ እወዳለሁ:
ሀ/ በአሁኑ ወቅት ያለውን እጅግ የተዳከመ እና ልል ተጠያቂነት ያለውን የኢዜማ ማዕከላዊ ቢሮ ዘመኑን በዋጀ የአገልግሎት ጥራት: ተጠያቂነቱ የተንሰራፋ በባለሙያ የሚመራ ተቋም: እና መረጃ እና መርህ ተኮር የአሰራር ስርዓት እዘረጋለሁ።
ለ/ የጽ/ቤት የአፈፃፀምና የማስፈፀም አቅምን የሚመዝን ወራዊ የተግባር ምዘና ስርዓት እዘረጋለሁ: የፓርቲው ውሳኔዎች: የአባላትና የመዋቅር ጥያቄዎችን: የሦስተኛ ወገን የደብዳቤ ግንኙነቶችን በብቃት አሳልጣለሁ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለ #ኢዜማ ን በልኩ ከተሠጡ የድጋፍ ድምፆች በጥቂቱ ይመልከቱ።
ማጠቃለያ!
⚖️
ከሰኔ 2-26/2017 ዓ.ም በሚቆየው የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የከፍተኛ አመራሮች የምርጫ ቅስቀሳ ስናካሂድ ቆይተናል። በእነዚህ የቀስቀሳ ቀናት በተቻለን መጠን ኢዜማ እንደገና መታደስ አለበት በሚለው ሀሳባችን በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የኢዜማ መዋቅሮች ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ፓርቲያችን ሊያደርጉ የሚገባቸውን የማሻሻያ ሀሳቦችን ጠቁመናል። የፓርቲያችንም ከፍተኛ ስልጣን ያለው የጠቅላላ ጉባዔው በዕለቱ በማሻሻያና ሪፎርም ሀሳቦች ላይ ትኩረቱን እንዲያደርግ በመላው ኢትዮጵያ የምንገኝ ኢዜማዊያን በአንድ ድምፅ አሰምተናል። በዚህም ታሪካዊ ጉባዔ ላይ ኢዜማ ራሱን ገምግሞ እንደገና ወደ ሰፊው ህዝብ እንዲቀርብ ጥያቄ ሰንዝረናል።
ሪፎርም እና ተሃድሶ አስፈላጊ በመሆናቸው ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች: መዋቅራዊ ማሻሻያዎችና ተቋማዊ ማሻሻያዎች እንደሚያስፈልጉን አምነን ሁሉም የኢዜማ አባላት ባቀረብነው ሀሳባችን ላይ እንዲወያይ አድርገናል። የጉባዔው ይሁንታ ካገኘ የኢዜማን ማሻሻያ የሚመሩ አካላትን ለመጠቆም እንወዳለን። ከታች ወደ ላይ የቀረበውን የኢዜማን ማሻሻያ ሀሳብ ከሚከተሉት ውስጥ አንዱ ሊመራው ይችላል። ሪፎርሙ ላይ ከመግባባት ከተደረሰ የፓርቲው መሪ ወይም ጉባዔው የሚሰይመው የሪፎርም ቋሚ ኮሚቴ ወይም ገለልተኛ የፖለቲካ ሙያ ኤክስፐርቶች በጥንቃቄ ሊመሩት ይችላሉ።
ይህን ተከትሎ ኢዜማ እንደገና ማሻሻያ የማድረግ ፍላጎቱ በጠቅላላ ጉባዔው ተቀባይነት ካገኘ ኢዜማን ለመጪው ዘመን ጊዜውን የዋጀ ተራማጅ የፖለቲካ ፓርቲ የማድረግ ፍላጎታችን ይሰምራል።
በዚህ የማሻሻያ ሀሳብ አስፈላጊነት የምታምኑ የጉባዔ ተሳታፊዎች የኢዜማን እንደገና ማሻሻያ ሀሳብ አስፈላጊነት የሚያምኑ አመራሮችን በምስጥራዊ የካርድ ድምፅ አሰጣጥ እንድትመርጡ አሳስባለሁ!
ለዚህ የውስጠ ፓርቲ ምርጫ ስኬት ድጋፍ ያደረጋችሁ አካላት ማለትም የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅ ኮሚቴ: የአስመራጭ ኮሚቴ: ዕጩ ተወዳዳሪዎች: የጉባዔ ተሳታፊዎች: የኢዜማ አባላትና አመራሮች እና ሌሎች በዚህ ታሪካዊ ጉባዔ ላይ ላደረጋችሁት አስተዋፅዖ ከልብ አመሰግናለሁ!
የማሻሻያ ሀሳቡን ይዘው ከቀረቡት ውስጥ
ጌታቸው ጳውሎስ-ለሊቀመንበርነት
ኤልሳቤጥ ሉቃስ- ለምክትል ሊቀመንበርነት
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ-ለዋና ፀሐፊነት
እንድትመርጡ በአክብሮት እጠይቃችኋለሁ!
ሙሉ የቃል ኩዳን ሰነዳችን ለማግኘት
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
⚖️
ከሰኔ 2-26/2017 ዓ.ም በሚቆየው የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የከፍተኛ አመራሮች የምርጫ ቅስቀሳ ስናካሂድ ቆይተናል። በእነዚህ የቀስቀሳ ቀናት በተቻለን መጠን ኢዜማ እንደገና መታደስ አለበት በሚለው ሀሳባችን በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የኢዜማ መዋቅሮች ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ፓርቲያችን ሊያደርጉ የሚገባቸውን የማሻሻያ ሀሳቦችን ጠቁመናል። የፓርቲያችንም ከፍተኛ ስልጣን ያለው የጠቅላላ ጉባዔው በዕለቱ በማሻሻያና ሪፎርም ሀሳቦች ላይ ትኩረቱን እንዲያደርግ በመላው ኢትዮጵያ የምንገኝ ኢዜማዊያን በአንድ ድምፅ አሰምተናል። በዚህም ታሪካዊ ጉባዔ ላይ ኢዜማ ራሱን ገምግሞ እንደገና ወደ ሰፊው ህዝብ እንዲቀርብ ጥያቄ ሰንዝረናል።
ሪፎርም እና ተሃድሶ አስፈላጊ በመሆናቸው ፖለቲካዊ ማሻሻያዎች: መዋቅራዊ ማሻሻያዎችና ተቋማዊ ማሻሻያዎች እንደሚያስፈልጉን አምነን ሁሉም የኢዜማ አባላት ባቀረብነው ሀሳባችን ላይ እንዲወያይ አድርገናል። የጉባዔው ይሁንታ ካገኘ የኢዜማን ማሻሻያ የሚመሩ አካላትን ለመጠቆም እንወዳለን። ከታች ወደ ላይ የቀረበውን የኢዜማን ማሻሻያ ሀሳብ ከሚከተሉት ውስጥ አንዱ ሊመራው ይችላል። ሪፎርሙ ላይ ከመግባባት ከተደረሰ የፓርቲው መሪ ወይም ጉባዔው የሚሰይመው የሪፎርም ቋሚ ኮሚቴ ወይም ገለልተኛ የፖለቲካ ሙያ ኤክስፐርቶች በጥንቃቄ ሊመሩት ይችላሉ።
ይህን ተከትሎ ኢዜማ እንደገና ማሻሻያ የማድረግ ፍላጎቱ በጠቅላላ ጉባዔው ተቀባይነት ካገኘ ኢዜማን ለመጪው ዘመን ጊዜውን የዋጀ ተራማጅ የፖለቲካ ፓርቲ የማድረግ ፍላጎታችን ይሰምራል።
በዚህ የማሻሻያ ሀሳብ አስፈላጊነት የምታምኑ የጉባዔ ተሳታፊዎች የኢዜማን እንደገና ማሻሻያ ሀሳብ አስፈላጊነት የሚያምኑ አመራሮችን በምስጥራዊ የካርድ ድምፅ አሰጣጥ እንድትመርጡ አሳስባለሁ!
ለዚህ የውስጠ ፓርቲ ምርጫ ስኬት ድጋፍ ያደረጋችሁ አካላት ማለትም የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅ ኮሚቴ: የአስመራጭ ኮሚቴ: ዕጩ ተወዳዳሪዎች: የጉባዔ ተሳታፊዎች: የኢዜማ አባላትና አመራሮች እና ሌሎች በዚህ ታሪካዊ ጉባዔ ላይ ላደረጋችሁት አስተዋፅዖ ከልብ አመሰግናለሁ!
የማሻሻያ ሀሳቡን ይዘው ከቀረቡት ውስጥ
ጌታቸው ጳውሎስ-ለሊቀመንበርነት
ኤልሳቤጥ ሉቃስ- ለምክትል ሊቀመንበርነት
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ-ለዋና ፀሐፊነት
እንድትመርጡ በአክብሮት እጠይቃችኋለሁ!
ሙሉ የቃል ኩዳን ሰነዳችን ለማግኘት
https://www.tgoop.com/ethzema/4751
https://drive.google.com/file/d/1wscQokq5GqXMs6ORl5XiXsPUWuFzDdRn/view?usp=drivesdk
Telegram
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለ #ኢዜማ ን በልኩ ከተሠጡ የድጋፍ ድምፆች ይመልከቱ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሰኔ 28-29/2017 ዓ.ም. የሚደረገውን የ #ኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ አስመልክቶ ከጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ስብሳቢ ዮሐንስ መኮንን የተላለፈ መልዕክት።