Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ኢዜማ መብትን በሰላማዊ እና ህጋዊ መንገድ መጠየቅን ይደግፋል!
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ላለፉት ረጅም ዓመታት ከሙያቸው ጋር በተገናኘ በርካታ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ እንደነበረ ይታወቃል። ሆኖም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የመንግስት አካል ቀና ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በቸልተኝነት በማየት ተጨባጭ ያልሆነ ተስፋ ከመስጠት የዘለለ ይህ ነው የሚባል ተግባራዊ መፍትሔ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡
በተለይም ላለፈው አንድ ወር የጤና ባለሙያዎች ጥያቄያቸውን በፅሁፍ ጭምር እንዳሳወቁ እና መልስ እንዲሰጣቸው በአደባባይ እየጠየቁ የሚገኙ ቢሆንም መንግስት ለጉዳዩ ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ በተቃራኒው እንቅስቃሴ ሲያደርግ መታየቱ አግባብነት ያለው ተግባር አይደለም፡፡
የባለሙያዎቹን ጥያቄ የመጠየቅ ህገመንግስታዊ መብት አክብሮ መንግስት በግልፅ ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠቱ፣ ችግራቸውን የመረዳት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ አለማድረጉ እና ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሲብስም የተደረጉ ሙከራዎች ካሉ በወቅቱ በተገቢው መንገድ አለማሳወቁ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው።
የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄዎች ተገቢ መልስ የሚሰጥ የመንግስት አካል በመጥፋቱ ባለፈው ሳምንት ጥያቄው ከፍ ብሎ ወደ ከፊል ስራ ማቆም አድማ አምርቷል። በዚህም ምክንያት የጤና አገልግሎት ፈላጊው የማሕበረሰቡ ክፍል ለእንግልት እና ለስቃይ እየተዳረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ ከቀጠለም ማሕበረሰቡ ለተጨማሪ እንግልት እንዳይዳረግ ያሳስበናል፡፡
ባለሙያዎቹ ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው እና የትኛውም የፖለቲካ አካል ጥያቄያቸውን ተንተርሶ ትርፍ ለማግኘት እንዳይንቀሳቀስ ደጋግመው ማሳሰባቸው፤ ከኢዜማ መርህ ጋር የሚስማማ በመሆኑ መልዕክቱን በማክበር ኢዜማ ምንም አይነት ሀሳብ ላለመሰጠት በጥንቃቄ ሲመለከት ቆይቷል፡፡ ነገር ግን አሁን ያለው እንቅስቃሴ ወደ መፍትሔ ከማምራት ይልቅ እየተወሳሰበ ሕዝቡን ከፍተኛ ዋጋ እንዳያስከፍል ብሎም ለተጨማሪ ሀገራዊ ትርምስ የሚጋብዝ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ደረጃ ላይ መገኘቱ አሳስቦናል። ሒደቱ በዚሁ ከቀጠለ በተግባር ለባለሙያው ጥያቄ መልስ ከማስገኘት ይልቅ ጠቃሚ ወዳልሆነ ሀገራዊ አለመረጋጋት የማምራት አዝማሚያ እያሳየ ነው፡፡
ኢዜማ የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄ በአግባቡ የሚረዳው እና መብትን በሰላማዊ መንገድ መጠየቅን የሚደግፈው ተግባር ነው፡፡ በእርግጥ መብትን ለማስከበር የሚኬድበት ስልት ግን ዜጎችን ለአደጋ የማያጋልጥ ሊሆን ይገባል የሚል ፅኑ እምነት አለን። ሁላችንም እንደምንረዳው የስራ ማቆም አድማ የማድረግ መብት ለጤናው ዘርፍ ሲሆን ቀጥተኛ ገፈት ቀማሹ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት የሚመጣው የሕብረተሰብ ክፍል መሆኑ እሙን ነው። ይህ ከመሆኑ አንፃር አጣዳፊ ህክምና የሚፈልጉ ዜጎች በስቃይ ውስጥ የመቆየት ብሎም የመኖር ያለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት በመሆኑ እንዲሁም ተያያዥ የሞራል ጥያቄ የሚያስነሳ ከመሆኑ አንፃር ትክክለኛ ስልት አይሆንም፡፡
ይህን ታሳቢ በማድረግም ወደ መፍትሔው ለመሄድ እና ከአላስፈላጊ ውጥረት ለመውጣት
1ኛ. መንግስት ስህተቱን አምኖ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እየተደረገ ካለው የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የታሰሩ የጤና ባለሙያዎችን እንዲፈታ ብሎም በመገናኛ ብዙኃን ወጥቶ ለባለሙያዎቹ ጥያቄዎች ያለውን መረዳት በአግባቡ እንዲገልፅ እንዲሁም ለመፍትሔው ከባለሙያዎቹ ጋር ተባብሮ እንደሚሰራ ቃል እንዲገባ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ. የጤና ባለሙያዎችም ከስራ ማቆም አድማው ተመልሰው የመፍትሔው አካል ለመሆን በጋራ እንዲሰሩ እንጠይቃለን።
3ኛ. የጤና ባለሙያ ማህበራትን ያቀፈ እና የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት ያካተተ ብሔራዊ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ፣ በመካከለኛ ጊዜ እንዲሁም በረጅም ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ጥያቄዎችን በመለየት ግብረ ኃይሉ ለባለሙያው እና ለማህበረሰቡ የደረሰበትን ውጤት በመገናኛ ብዙኃን እንዲያሳውቅ ምክረ ሀሳባችንን እናቀርባለን፡፡
በመጨረሻም በባለሙያዎቹ ደጋግሞ እንደተባለው ከዚህ ሂደት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መሞከርን እኛም አብዝተን የምንፀየፈው መሆኑን አስምረን እያረጋገጥን! ይህን መጥፎ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሀገራዊ ትርምስ እና ሁከት በመፍጠር መንግስት ላይ ያለን የፖለቲካ ቅሬታ መወጣጫ ለማድረግ መሞከርም ሆነ ሌሎች አድማዎችን አቀጠጣጥሎ የመንግስት ስልጣን ለመነቀነቅ የሚሞከር የሞኝ ሙከራ ጊዜው ያለፈበት የከሰረ መንገድ አድርገን የምንረዳው መሆኑን ለመግለፅ እንፈልጋለን፡፡
በዚህ የመብት ትግል ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ስትሳተፉ እስር እንግልት እና አፈና ለደረሰባችሁ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ መብትን መጠየቅ በምንም መልኩ ሊያሳስር እና ሊያሳፍን እንደማይገባ በዚህ መንገድ ጥያቄውን ለማፈን መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በአስቸኳይ እንዲያቆም ድርጊቱን እኛም አጥብቀን የምናወግዝ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 10/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ላለፉት ረጅም ዓመታት ከሙያቸው ጋር በተገናኘ በርካታ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ እንደነበረ ይታወቃል። ሆኖም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የመንግስት አካል ቀና ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በቸልተኝነት በማየት ተጨባጭ ያልሆነ ተስፋ ከመስጠት የዘለለ ይህ ነው የሚባል ተግባራዊ መፍትሔ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡
በተለይም ላለፈው አንድ ወር የጤና ባለሙያዎች ጥያቄያቸውን በፅሁፍ ጭምር እንዳሳወቁ እና መልስ እንዲሰጣቸው በአደባባይ እየጠየቁ የሚገኙ ቢሆንም መንግስት ለጉዳዩ ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ በተቃራኒው እንቅስቃሴ ሲያደርግ መታየቱ አግባብነት ያለው ተግባር አይደለም፡፡
የባለሙያዎቹን ጥያቄ የመጠየቅ ህገመንግስታዊ መብት አክብሮ መንግስት በግልፅ ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠቱ፣ ችግራቸውን የመረዳት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ አለማድረጉ እና ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሲብስም የተደረጉ ሙከራዎች ካሉ በወቅቱ በተገቢው መንገድ አለማሳወቁ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው።
የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄዎች ተገቢ መልስ የሚሰጥ የመንግስት አካል በመጥፋቱ ባለፈው ሳምንት ጥያቄው ከፍ ብሎ ወደ ከፊል ስራ ማቆም አድማ አምርቷል። በዚህም ምክንያት የጤና አገልግሎት ፈላጊው የማሕበረሰቡ ክፍል ለእንግልት እና ለስቃይ እየተዳረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ ከቀጠለም ማሕበረሰቡ ለተጨማሪ እንግልት እንዳይዳረግ ያሳስበናል፡፡
ባለሙያዎቹ ፖለቲካዊ ዓላማ እንደሌላቸው እና የትኛውም የፖለቲካ አካል ጥያቄያቸውን ተንተርሶ ትርፍ ለማግኘት እንዳይንቀሳቀስ ደጋግመው ማሳሰባቸው፤ ከኢዜማ መርህ ጋር የሚስማማ በመሆኑ መልዕክቱን በማክበር ኢዜማ ምንም አይነት ሀሳብ ላለመሰጠት በጥንቃቄ ሲመለከት ቆይቷል፡፡ ነገር ግን አሁን ያለው እንቅስቃሴ ወደ መፍትሔ ከማምራት ይልቅ እየተወሳሰበ ሕዝቡን ከፍተኛ ዋጋ እንዳያስከፍል ብሎም ለተጨማሪ ሀገራዊ ትርምስ የሚጋብዝ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ደረጃ ላይ መገኘቱ አሳስቦናል። ሒደቱ በዚሁ ከቀጠለ በተግባር ለባለሙያው ጥያቄ መልስ ከማስገኘት ይልቅ ጠቃሚ ወዳልሆነ ሀገራዊ አለመረጋጋት የማምራት አዝማሚያ እያሳየ ነው፡፡
ኢዜማ የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄ በአግባቡ የሚረዳው እና መብትን በሰላማዊ መንገድ መጠየቅን የሚደግፈው ተግባር ነው፡፡ በእርግጥ መብትን ለማስከበር የሚኬድበት ስልት ግን ዜጎችን ለአደጋ የማያጋልጥ ሊሆን ይገባል የሚል ፅኑ እምነት አለን። ሁላችንም እንደምንረዳው የስራ ማቆም አድማ የማድረግ መብት ለጤናው ዘርፍ ሲሆን ቀጥተኛ ገፈት ቀማሹ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት የሚመጣው የሕብረተሰብ ክፍል መሆኑ እሙን ነው። ይህ ከመሆኑ አንፃር አጣዳፊ ህክምና የሚፈልጉ ዜጎች በስቃይ ውስጥ የመቆየት ብሎም የመኖር ያለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት በመሆኑ እንዲሁም ተያያዥ የሞራል ጥያቄ የሚያስነሳ ከመሆኑ አንፃር ትክክለኛ ስልት አይሆንም፡፡
ይህን ታሳቢ በማድረግም ወደ መፍትሔው ለመሄድ እና ከአላስፈላጊ ውጥረት ለመውጣት
1ኛ. መንግስት ስህተቱን አምኖ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እየተደረገ ካለው የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የታሰሩ የጤና ባለሙያዎችን እንዲፈታ ብሎም በመገናኛ ብዙኃን ወጥቶ ለባለሙያዎቹ ጥያቄዎች ያለውን መረዳት በአግባቡ እንዲገልፅ እንዲሁም ለመፍትሔው ከባለሙያዎቹ ጋር ተባብሮ እንደሚሰራ ቃል እንዲገባ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ. የጤና ባለሙያዎችም ከስራ ማቆም አድማው ተመልሰው የመፍትሔው አካል ለመሆን በጋራ እንዲሰሩ እንጠይቃለን።
3ኛ. የጤና ባለሙያ ማህበራትን ያቀፈ እና የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት ያካተተ ብሔራዊ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ፣ በመካከለኛ ጊዜ እንዲሁም በረጅም ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ጥያቄዎችን በመለየት ግብረ ኃይሉ ለባለሙያው እና ለማህበረሰቡ የደረሰበትን ውጤት በመገናኛ ብዙኃን እንዲያሳውቅ ምክረ ሀሳባችንን እናቀርባለን፡፡
በመጨረሻም በባለሙያዎቹ ደጋግሞ እንደተባለው ከዚህ ሂደት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መሞከርን እኛም አብዝተን የምንፀየፈው መሆኑን አስምረን እያረጋገጥን! ይህን መጥፎ ሁኔታ እንደመልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሀገራዊ ትርምስ እና ሁከት በመፍጠር መንግስት ላይ ያለን የፖለቲካ ቅሬታ መወጣጫ ለማድረግ መሞከርም ሆነ ሌሎች አድማዎችን አቀጠጣጥሎ የመንግስት ስልጣን ለመነቀነቅ የሚሞከር የሞኝ ሙከራ ጊዜው ያለፈበት የከሰረ መንገድ አድርገን የምንረዳው መሆኑን ለመግለፅ እንፈልጋለን፡፡
በዚህ የመብት ትግል ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ስትሳተፉ እስር እንግልት እና አፈና ለደረሰባችሁ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ መብትን መጠየቅ በምንም መልኩ ሊያሳስር እና ሊያሳፍን እንደማይገባ በዚህ መንገድ ጥያቄውን ለማፈን መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በአስቸኳይ እንዲያቆም ድርጊቱን እኛም አጥብቀን የምናወግዝ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 10/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ ) ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄን አስመልክቶ ከአዲስ ኮምፓስ ሚዲያ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ይመልከቱ።
https://www.youtube.com/live/6VlxY6lNNC8?si=5hl1S_UohRtGxVMj
https://www.youtube.com/live/6VlxY6lNNC8?si=5hl1S_UohRtGxVMj
YouTube
"ብሔራዊ ግብረ-ሃይል"፣ "ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣ "የፍርሃት ቆፈን?"
"ብሔራዊ ግብረ-ሃይል"፣
"ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣
"የፍርሃት ቆፈን?"
"ጊዜ ያለፈበት የከሸፈ መንገድ"፣
"የፍርሃት ቆፈን?"
የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!!
የኢዜማ አባል የሆኑት ሲኒየር ፋርማሲስት ኃይለማርያም ብርሃኑ የድሪም ኬር አጠቃላይ ሆስፒታል የፉርማሲ ክፍል ኃላፊ፣ የኢዜማ የባህርዳር ከተማ የስራ አስፈፃሚ፣ በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የስራ አስፈፃሚ፣ ፓርቲውን በመወከል የ2013 ዓ.ም የክልሉ ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ እንዲሁም በአማራ ክልል በነበረው ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ንቁ ተሳታፊ የነበሩ በሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ያሉ ቆራጥ፣ ሀገር እና ወገንን ቀን ከሌት በማገልገል የሚተጉ ዜጋ ናቸው።
አባላችን ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም ምሽት በ2፡00 ሰዓት በፓሊሶች ከቤታቸው ተወስደው በባህርዳር ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለምንም ክስ የታሰሩ ሲሆን ፤ በግንቦት 4 ቀን አካልን ነፃ የማውጣት ክስ ተመስርቶ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም የባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ያስተላለፈ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ከነበሩበት ቦታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፡፡
መንግስት አንድን ዜጋ ከሕግ በላይ ሆኖ አስሮ ማንገላታቱ ሳያንስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር ሲጨመርበት ተስፋ አስቆራጭ ነው! በመሆኑም የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በአፅንኦት እንጠይቃለን!!!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ
የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 13/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የኢዜማ አባል የሆኑት ሲኒየር ፋርማሲስት ኃይለማርያም ብርሃኑ የድሪም ኬር አጠቃላይ ሆስፒታል የፉርማሲ ክፍል ኃላፊ፣ የኢዜማ የባህርዳር ከተማ የስራ አስፈፃሚ፣ በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የስራ አስፈፃሚ፣ ፓርቲውን በመወከል የ2013 ዓ.ም የክልሉ ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ እንዲሁም በአማራ ክልል በነበረው ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ንቁ ተሳታፊ የነበሩ በሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ያሉ ቆራጥ፣ ሀገር እና ወገንን ቀን ከሌት በማገልገል የሚተጉ ዜጋ ናቸው።
አባላችን ሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም ምሽት በ2፡00 ሰዓት በፓሊሶች ከቤታቸው ተወስደው በባህርዳር ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለምንም ክስ የታሰሩ ሲሆን ፤ በግንቦት 4 ቀን አካልን ነፃ የማውጣት ክስ ተመስርቶ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም የባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ያስተላለፈ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ከነበሩበት ቦታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፡፡
መንግስት አንድን ዜጋ ከሕግ በላይ ሆኖ አስሮ ማንገላታቱ ሳያንስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር ሲጨመርበት ተስፋ አስቆራጭ ነው! በመሆኑም የሕግ የበላይነት ተከብሮ አባላቸን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በአፅንኦት እንጠይቃለን!!!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ
የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 13/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የኅዘን መግለጫ
*
በ #ኢዜማ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር መምሪያ ቋሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ መስፍን አበበ ግንቦት 26/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱም ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ 8:00 ሰዓት በሽሮሜዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የፓርቲው አመራሮች እና አባላት በአባላችን በአቶ መስፍን አበበ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ኅዘን እየገለጽን ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።
*
በ #ኢዜማ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር መምሪያ ቋሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ መስፍን አበበ ግንቦት 26/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱም ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ 8:00 ሰዓት በሽሮሜዳ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የፓርቲው አመራሮች እና አባላት በአባላችን በአቶ መስፍን አበበ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ኅዘን እየገለጽን ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።
የሰላም ጉዳይ ከምርጫው በፊት ቅድሚያ ተሰጥቶት ሊሠራበት ይገባል
ዋስይሁን ተስፋዬ (የኢዜማ ዋና ፀሐፊ)
በኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 13 ትኩረቷን ምርጫ ላይ አድርጋ የተሠናዳች ሲሆን የወሩን እንግዳ ጨምሮ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሥነብበናለች፤ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።
https://drive.google.com/file/d/1nSIwOvNLyR-FRsIApnZtgo71wnwduvmw/view?usp=drivesdk
#ኢዜማ
#የዜጎች_ልሳን
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ) የፓርቲው ከፍተኛ አካል የሆነውን ጠቅላላ ጉባኤ በያዝነው ወር ሰኔ 28 እና 29/ 2017 ዓ.ም. ለማድረግ ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የከፍተኛ አመራሮችን የሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር፣ የዋና ጸሐፊ እና ፋይናንስ /ትሬዠረር/ ኃላፊ ምርጫ ይገኝበታል።
በዚሁ መሠረት ባለፉት ወራት የእጩዎች ልየታ የተደረገ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሰኔ 02/2017 ዓ.ም. ለኃላፊነት የሚፎካከሩ ተወዳዳሪዎች የፓርቲውን የማኅበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቅመው የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚያካሒዱበትን ዕጣ አውጥተዋል፤ በተጨማሪም የውድድር እና የምረጡኝ ቅስቀሳ የስነ- ምግባር ደንብ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል።
ዕጩ ተወዳዳሪዎቹ ከሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ የምረጡኝ ቅስቀሳ እንደሚያካሂዱ አስመራጭ ኮሚቴው ለማሳወቅ ይወዳል።
በዚሁ መሠረት ባለፉት ወራት የእጩዎች ልየታ የተደረገ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሰኔ 02/2017 ዓ.ም. ለኃላፊነት የሚፎካከሩ ተወዳዳሪዎች የፓርቲውን የማኅበራዊ ትስስር ገፆች ተጠቅመው የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚያካሒዱበትን ዕጣ አውጥተዋል፤ በተጨማሪም የውድድር እና የምረጡኝ ቅስቀሳ የስነ- ምግባር ደንብ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል።
ዕጩ ተወዳዳሪዎቹ ከሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ የምረጡኝ ቅስቀሳ እንደሚያካሂዱ አስመራጭ ኮሚቴው ለማሳወቅ ይወዳል።
ኢዜማን እንደገና!
ዶ/ር ካሳሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
እኔ የኢዜማ የሙያና የሠራተኛ ማህበራት መምሪያ ሃላፊ ዶ/ር ካሳሁን ከዚህ ቀደም በፓርቲያችን ኢዜማ ውስጥ በተለያዩ ሃላፊነቶች ያገለገልኩ ሲሆን ፓርቲው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለመታከትና ያለማቋረጥ በቅንነትና በመሰጠት እያገለገልኩ እገኛለሁ። በኢዜማ ላስካ መደበኛ ምርጫ ክልል በአባልነት የጀመርኩት የፖለቲካ ትግል ጉዞ በምርጫ 2013 ላይ የምርጫ ክልሌን በመወከል ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢዜማ ዕጩ ሆኜ መቅረቤ ይታወቃል። በኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባልነት በቅንነት ከማገልገል ጀምሬ በፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባልነት: የደቡብ ክልል የኢዜማ አደረጃጀቶች አስተባባሪ በመሆን አገልግያለሁ። በመቀጠልም የድርጅት ጉዳይ መምሪያን በምክትል ሃላፊነት በማገልገል የፓርቲውን መዋቅሮች የማጠናከርና የማስቀጠል ትልቅ ሀላፊነቶችን ተወጥቻለሁ።
እኔ ፓርቲያችን በመወከል የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውስጥ በአመራርነት አገልግያለሁ። በኢዜማ የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዘርፍን በአስተባባሪነት በመምራት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የጋራ ምክር ቤቶች ወደ ሰላማዊና ጤናማ የፖለቲካ ሥራ እንዲሰሩ የበኩሌን አስተዋፅዖ ተወጥቻለሁ።
በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት በአመራርነት እያገለገልኩ ከዚህ ቀደም ምክር ቤቱን ወክዬ በአውሮፓ ህብረት የውጭ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ኮሚሽን የወጣቶች አማካሪ ቦርድ አባላነት በዕጩነት ተወዳድርያለሁ።
ከሀገር አቀፍ ፖለቲካ በተጨማሪ በመላው አፍሪካዊያን አንድነት ትግል ውስጥ በንቃት የተሳተፍኩ ስሆን ከዚህ ቀደም Global Pan Africanism Network-GPAN የተሰኘ ንቅናቄን በምክትል ፕረዚዳንትነት የመራሁና በአፍሪካ ህብረት በወጣቶች ቋሚ መልዕክተኛ ቢሮም አገልግያለሁ። በአሁኑ ሰዓትም የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የወጣቶች ድምፅ ውስጥ በአባልነት እየተሳተፍኩ እገኛለሁ። የ Model African Union Ethiopia የተሰኘ የሲቪክ ማህበር መስራች አባል በመሆን ከሌሎች ፓን አፍሪካዊ ወጣቶች ጋር በቀጣይ የአህጉራዊ አንድነት ላይ ከሚሰሩ አካላት ጋርም በንቃትና በቁርጠኝነት እያገለገልኩ ነው።
በሙያዬም በታታሪነት የተመሰከረልኝና በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች ውስጥ እየሰራው ነው። በተጨማሪም በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የማህበረሰብ ሳይንስና ፖለቲካ ትምህርት ክፍል ውስጥ Comparative Politics በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ ተከታትያለሁ። በጥናታቸውም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች አደረጃጀትን በማነፃፀር ተመልክቻለሁ።
በዚህ የኢዜማ የከፍተኛ አመራሮች ምርጫ ውድድር ላይ በዋና ፀሐፊነት ለማገልገል በዕጩነት ቀርብያለሁ። የዜግነት ፖለቲካና ማህበራዊ ፍትህ በተሰናሰለ መልኩ ለመጪዋ ኢትዮጵያ ለማስረፅ ድጋፍ እንድትሰጡኝና እንድትመርጡኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ!
ዶ/ር ካሳሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
እኔ የኢዜማ የሙያና የሠራተኛ ማህበራት መምሪያ ሃላፊ ዶ/ር ካሳሁን ከዚህ ቀደም በፓርቲያችን ኢዜማ ውስጥ በተለያዩ ሃላፊነቶች ያገለገልኩ ሲሆን ፓርቲው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለመታከትና ያለማቋረጥ በቅንነትና በመሰጠት እያገለገልኩ እገኛለሁ። በኢዜማ ላስካ መደበኛ ምርጫ ክልል በአባልነት የጀመርኩት የፖለቲካ ትግል ጉዞ በምርጫ 2013 ላይ የምርጫ ክልሌን በመወከል ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢዜማ ዕጩ ሆኜ መቅረቤ ይታወቃል። በኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባልነት በቅንነት ከማገልገል ጀምሬ በፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባልነት: የደቡብ ክልል የኢዜማ አደረጃጀቶች አስተባባሪ በመሆን አገልግያለሁ። በመቀጠልም የድርጅት ጉዳይ መምሪያን በምክትል ሃላፊነት በማገልገል የፓርቲውን መዋቅሮች የማጠናከርና የማስቀጠል ትልቅ ሀላፊነቶችን ተወጥቻለሁ።
እኔ ፓርቲያችን በመወከል የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውስጥ በአመራርነት አገልግያለሁ። በኢዜማ የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዘርፍን በአስተባባሪነት በመምራት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የጋራ ምክር ቤቶች ወደ ሰላማዊና ጤናማ የፖለቲካ ሥራ እንዲሰሩ የበኩሌን አስተዋፅዖ ተወጥቻለሁ።
በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት በአመራርነት እያገለገልኩ ከዚህ ቀደም ምክር ቤቱን ወክዬ በአውሮፓ ህብረት የውጭ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ኮሚሽን የወጣቶች አማካሪ ቦርድ አባላነት በዕጩነት ተወዳድርያለሁ።
ከሀገር አቀፍ ፖለቲካ በተጨማሪ በመላው አፍሪካዊያን አንድነት ትግል ውስጥ በንቃት የተሳተፍኩ ስሆን ከዚህ ቀደም Global Pan Africanism Network-GPAN የተሰኘ ንቅናቄን በምክትል ፕረዚዳንትነት የመራሁና በአፍሪካ ህብረት በወጣቶች ቋሚ መልዕክተኛ ቢሮም አገልግያለሁ። በአሁኑ ሰዓትም የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የወጣቶች ድምፅ ውስጥ በአባልነት እየተሳተፍኩ እገኛለሁ። የ Model African Union Ethiopia የተሰኘ የሲቪክ ማህበር መስራች አባል በመሆን ከሌሎች ፓን አፍሪካዊ ወጣቶች ጋር በቀጣይ የአህጉራዊ አንድነት ላይ ከሚሰሩ አካላት ጋርም በንቃትና በቁርጠኝነት እያገለገልኩ ነው።
በሙያዬም በታታሪነት የተመሰከረልኝና በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች ውስጥ እየሰራው ነው። በተጨማሪም በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የማህበረሰብ ሳይንስና ፖለቲካ ትምህርት ክፍል ውስጥ Comparative Politics በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ ተከታትያለሁ። በጥናታቸውም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች አደረጃጀትን በማነፃፀር ተመልክቻለሁ።
በዚህ የኢዜማ የከፍተኛ አመራሮች ምርጫ ውድድር ላይ በዋና ፀሐፊነት ለማገልገል በዕጩነት ቀርብያለሁ። የዜግነት ፖለቲካና ማህበራዊ ፍትህ በተሰናሰለ መልኩ ለመጪዋ ኢትዮጵያ ለማስረፅ ድጋፍ እንድትሰጡኝና እንድትመርጡኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ!