የተከበራችሁ የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ተሳታፊዎች
የተከበራችሁ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች
እኔ ጌታቸው ጳውሎስ እና
ኤልሳቤጥ ሉቃስ
ከሰኔ 28-29/2017 ዓ.ም ድረስ በሚከናወነው የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የፓርቲያችን መተዳደሪያ ደንብ እንደሚፈቅደው አሰራር በዚህ ጉባዔ የኢዜማ ከፍተኛ የጉባዔ ተመራጭ አመራሮች መካከል በሊቀ መንበርነትና በምክትል ሊቀመንበርነት ለመወዳደር ታጭተናል። የከፍተኛ አመራሮች አስመራጭ ኮሚቴ ባደረገው የውስጥ ምዘና ላይ ኢዜማን በመሪነት ለማገልገል ብቁ ዕጩዎች መሆናችን ታምኖ ዛሬ ከፊት ለፊታችሁ ቆመናል።
በዚህ የፓርቲያችን ከፍተኛ የመወሰን ስልጣን ባለው የጠቅላላ ጉባዔ ፊት ቀርበን ለኢዜማ ምን እንደምንሰራ ያለንን ሀሳብ እንድናጋራ ስለፈቀዳችሁና ትኩረታችሁን ስለሰጣችሁን እናመሰግናለን!
ፓርቲያችን ኢዜማ ከምስረታው ጀምሮ የመጣበትን መንገድ በመገምገም ለቀጣይ ዘመን ትግል ራሱን እንዲያዘጋጅ ሁሉም የሚመለከተው የፓርቲው አካል በጋራ በመወያየት ኢዜማን እንደገና ማጠናከር: ማደራጀትና ወደ ትግል ማስገባት ይኖርብናል። ለዚህም ደግሞ በቀጣይ ፓርቲውን የቀደመ ክብሩን እንደገና ለመመለስ በአጭሩ የሚከተሉትን ሥራዎችን ለማስጀመርና በብቃት ለመምራት ተዘጋጅተናል።
የጠቅላላ ጉባዔው ሀሳባችን ተቀብሎ ይሁንታ ብናገኝና ብንመረጥ የሚከተሉትን ተግባራት እናከናውናለን!
1. ኢዜማ ይዞት የተነሳው የትግል መነሻ ሀሳብ እና ዓላማ ሳይሸራረፍ ዕውን እንዲሆን እንሰራለን:
2. ድርጅታችን በመርህ ላይ የፀና እንዲሆን እና በሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት እንዲጪምር የማድረግ ስራዎችን እንሰራለን:
3. የኢዜማ አባላት እና ደጋፊዎች ያለስስት የሚታገሉለት እና የሚኮሩበት ድርጅት እንዲሆን እናደርጋለን:
4. የምርጫ ክልሎዎች ራሳቸውን በገንዘብ፣በሰው እና ቴክኖዎሎጂ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ ከማዕከል የቴክኒክ እና ሙያ ድጋፎችን እናደርጋለን:
5. የ7ኛው ዙር ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ ብቁ: ተመራጭና ተገዳዳሪ ድርጅት እንዲሆን የማዘጋጀት ሰራዎችን ከወዲሁ እንጀምራለን:
6. አባሎቻችን ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የማንቃት: ማብቃት እና የማደራጀት ስራዎችን እንሰራለን:
7. የዜጎችን እና የአባላትን መብት እና ደህንነት እንዲከበር ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ከሚመለከታቸው አካል ጋር በትብብር እንሰራለን:
8. በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሀገራችን የመወሰን አቅም ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለመታከት እንሰራለን:
9. የብሔር ፓለቲካ ወደ ኋላ ያስቀረውን ስሁት አካሄድ በዜግነት ፖለቲካ እንዲቀየር ከሚተባበሩን ተቋማት እና ግለሰቦች ጋር እንሰራለን:
10. ኢዜማ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ የመሪነት ሚናውን እንዲጫወትና ሰላማዊ የፖለቲካ ስርዓት ማንበር ሰመናዊ ኮከባችን እንዲሆን መምሪያዎቻችንና መዋቅሮቻችን እናበቃለን:
11. የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ የጥንካሬው መሠረት በውስጡ የያዛቸው አባላት እና ደጋፊዎች እንደመሆናቸው የኢዜማ አባልነት ዜጎች ወደው ፈቅደው የሚመርጡትና በአባልነት የሚታቀፉበት በማድረግ የምርጫ ወረዳዎች እንዲጠናከሩ የሚያስችሉ ስራዎችን እንሰራለን:
12. የማህበራዊ ፍትህን ማስፈን ራዕያቸው ካደረጉ ከአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ሀገራት የሚገኙ መሰል ራዕይ ካላቸው ተቋማት ጋር በጋራ እንሰራለን።
13, ሴቶች: ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች የማህበረሰባችን አካል ተደርገው በፖለቲካ ስርዓት ውስጥ ከተመልካችነትና ከአድማጭነት ዘልቀው የመሪነት ሚናቸውን እንዲጫወቱ እንሰራለን።
ክቡራንና ክቡራት
ከላይ የጠቀስናቸውን ዐበይት ተግባራትን ስንከውን ከኢዜማ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ: የፓርቲው ብሔራዊ አመራሮች: የምርጫ ክልሎችና ከሌሎች የኢዜማ አካላት ጋር በመቀናጀት ታላቅ ዓላማና ራዕይ ያነገበውን ፓርቲያችንን እንደገና ወደ ቀደመው ክብሩ እና ለህዝባችን ይዞት የገባውን ቃል እንዲፈፅም እንሰራለን።
በዚህ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ፓርቲያችን እንደገና የመታደስና የማጠናከር ተግባር ለመፈፀም የጠቅላላ ጉባዔውን አደራ ለመቀበልና ይሁንታ ለማገኘት በታላቅ ትህትና እንጠይቃችኋለን!
ኢዜማን እንደገና!
ጌታቸው ጳውሎስ ( ዕጩ ሊቀመንበር)
ኤልሳቤጥ ሉቃስ (ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር)
የተከበራችሁ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች
እኔ ጌታቸው ጳውሎስ እና
ኤልሳቤጥ ሉቃስ
ከሰኔ 28-29/2017 ዓ.ም ድረስ በሚከናወነው የኢዜማ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የፓርቲያችን መተዳደሪያ ደንብ እንደሚፈቅደው አሰራር በዚህ ጉባዔ የኢዜማ ከፍተኛ የጉባዔ ተመራጭ አመራሮች መካከል በሊቀ መንበርነትና በምክትል ሊቀመንበርነት ለመወዳደር ታጭተናል። የከፍተኛ አመራሮች አስመራጭ ኮሚቴ ባደረገው የውስጥ ምዘና ላይ ኢዜማን በመሪነት ለማገልገል ብቁ ዕጩዎች መሆናችን ታምኖ ዛሬ ከፊት ለፊታችሁ ቆመናል።
በዚህ የፓርቲያችን ከፍተኛ የመወሰን ስልጣን ባለው የጠቅላላ ጉባዔ ፊት ቀርበን ለኢዜማ ምን እንደምንሰራ ያለንን ሀሳብ እንድናጋራ ስለፈቀዳችሁና ትኩረታችሁን ስለሰጣችሁን እናመሰግናለን!
ፓርቲያችን ኢዜማ ከምስረታው ጀምሮ የመጣበትን መንገድ በመገምገም ለቀጣይ ዘመን ትግል ራሱን እንዲያዘጋጅ ሁሉም የሚመለከተው የፓርቲው አካል በጋራ በመወያየት ኢዜማን እንደገና ማጠናከር: ማደራጀትና ወደ ትግል ማስገባት ይኖርብናል። ለዚህም ደግሞ በቀጣይ ፓርቲውን የቀደመ ክብሩን እንደገና ለመመለስ በአጭሩ የሚከተሉትን ሥራዎችን ለማስጀመርና በብቃት ለመምራት ተዘጋጅተናል።
የጠቅላላ ጉባዔው ሀሳባችን ተቀብሎ ይሁንታ ብናገኝና ብንመረጥ የሚከተሉትን ተግባራት እናከናውናለን!
1. ኢዜማ ይዞት የተነሳው የትግል መነሻ ሀሳብ እና ዓላማ ሳይሸራረፍ ዕውን እንዲሆን እንሰራለን:
2. ድርጅታችን በመርህ ላይ የፀና እንዲሆን እና በሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት እንዲጪምር የማድረግ ስራዎችን እንሰራለን:
3. የኢዜማ አባላት እና ደጋፊዎች ያለስስት የሚታገሉለት እና የሚኮሩበት ድርጅት እንዲሆን እናደርጋለን:
4. የምርጫ ክልሎዎች ራሳቸውን በገንዘብ፣በሰው እና ቴክኖዎሎጂ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ ከማዕከል የቴክኒክ እና ሙያ ድጋፎችን እናደርጋለን:
5. የ7ኛው ዙር ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ ብቁ: ተመራጭና ተገዳዳሪ ድርጅት እንዲሆን የማዘጋጀት ሰራዎችን ከወዲሁ እንጀምራለን:
6. አባሎቻችን ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የማንቃት: ማብቃት እና የማደራጀት ስራዎችን እንሰራለን:
7. የዜጎችን እና የአባላትን መብት እና ደህንነት እንዲከበር ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ከሚመለከታቸው አካል ጋር በትብብር እንሰራለን:
8. በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሀገራችን የመወሰን አቅም ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለመታከት እንሰራለን:
9. የብሔር ፓለቲካ ወደ ኋላ ያስቀረውን ስሁት አካሄድ በዜግነት ፖለቲካ እንዲቀየር ከሚተባበሩን ተቋማት እና ግለሰቦች ጋር እንሰራለን:
10. ኢዜማ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ የመሪነት ሚናውን እንዲጫወትና ሰላማዊ የፖለቲካ ስርዓት ማንበር ሰመናዊ ኮከባችን እንዲሆን መምሪያዎቻችንና መዋቅሮቻችን እናበቃለን:
11. የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ የጥንካሬው መሠረት በውስጡ የያዛቸው አባላት እና ደጋፊዎች እንደመሆናቸው የኢዜማ አባልነት ዜጎች ወደው ፈቅደው የሚመርጡትና በአባልነት የሚታቀፉበት በማድረግ የምርጫ ወረዳዎች እንዲጠናከሩ የሚያስችሉ ስራዎችን እንሰራለን:
12. የማህበራዊ ፍትህን ማስፈን ራዕያቸው ካደረጉ ከአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ሀገራት የሚገኙ መሰል ራዕይ ካላቸው ተቋማት ጋር በጋራ እንሰራለን።
13, ሴቶች: ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች የማህበረሰባችን አካል ተደርገው በፖለቲካ ስርዓት ውስጥ ከተመልካችነትና ከአድማጭነት ዘልቀው የመሪነት ሚናቸውን እንዲጫወቱ እንሰራለን።
ክቡራንና ክቡራት
ከላይ የጠቀስናቸውን ዐበይት ተግባራትን ስንከውን ከኢዜማ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ: የፓርቲው ብሔራዊ አመራሮች: የምርጫ ክልሎችና ከሌሎች የኢዜማ አካላት ጋር በመቀናጀት ታላቅ ዓላማና ራዕይ ያነገበውን ፓርቲያችንን እንደገና ወደ ቀደመው ክብሩ እና ለህዝባችን ይዞት የገባውን ቃል እንዲፈፅም እንሰራለን።
በዚህ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ፓርቲያችን እንደገና የመታደስና የማጠናከር ተግባር ለመፈፀም የጠቅላላ ጉባዔውን አደራ ለመቀበልና ይሁንታ ለማገኘት በታላቅ ትህትና እንጠይቃችኋለን!
ኢዜማን እንደገና!
ጌታቸው ጳውሎስ ( ዕጩ ሊቀመንበር)
ኤልሳቤጥ ሉቃስ (ዕጩ ምክትል ሊቀመንበር)
👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
እኛ የኢዜማ አመራር ለመኾን የምንወዳደር ግለሰቦች በለውጥ ሕግ እናምናለን። ግለሰቦችም ኾኑ ድርጅቶች ራሳቸውን ባልተቋረጠ መልኩ በመገምገም ዘመኑን የዋጀ ለውጥ ማድረግ አለባቸው። የድርጅታዊ አመራር ሳይንስ እንደሚያስተምረው፤ የማይለወጥ ነገር ቢኖር ራሱ ለውጥ ብቻ ነው።
ለውጥን ለማስተናገድ ዝግጁ ያልኾነ ድርጅት በፍጥነት በሚለወጡ ዓለምአቀፋዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ምክንያት ተደናቅፎ መውደቁ አይቀርም። ኢዜማ እንደ ድርጅት የአመራር መተካካትን የሚያከናውንበት ሥርዐት አለው። በየሦስት ዓመቱ ግልጽ ውድድር በማድረግ አዳዲስ አመራሮችና አስተሳሰቦች እንዲስተናገዱ ያደርጋል። ከዚህ አንፃር ፓርቲያችን ለለውጥ ዝግ አይደለም ማለት ይቻላል። ከሌሎች ድርጅታዊ የለውጥ አስተዳደር ማዕቀፎች አንፃር ግን እጅግ ብዙ መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች እንዳሉ እናምናለን።
በተለይም የአሠራርና የመዋቅር ማሻሻያዎችን እንደአስፈላጊነቱ ለመተግበር የሚያስችል የለውጥ አስተዳደር ሥርዐት ባለመኖሩ፤ የድርጅታችንን ዕድገት እንዳይፋጠን አድርጎታል። ለአሠራር ምቹ ያልኾኑ ጉዳዮች ዕየታዩ ሳይሻሻሉ በመቆየታቸው የኢዜማ ድርጅታዊ ጥንካሬ እንዲላላ ኾኗል።
በመኾኑም የታቀደና ግብታዊ ያልኾነ ለውጥ ለማስናገድ አልተቻለም። ስለዚህም፤ ንሥር ራሱን እያደሠ ሕይወቱን እንደ አዲስ እንደሚኖረው፤ ኢዜማም ዘመኑን የዋጀ የለውጥ አስተዳደር እንዲኖረው አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከተቋማዊ የለውጥ አስተዳደር አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk.
#ኢዜማን_በልኩ !!
ተቋማዊ የለውጥ አስተዳደር
እኛ የኢዜማ አመራር ለመኾን የምንወዳደር ግለሰቦች በለውጥ ሕግ እናምናለን። ግለሰቦችም ኾኑ ድርጅቶች ራሳቸውን ባልተቋረጠ መልኩ በመገምገም ዘመኑን የዋጀ ለውጥ ማድረግ አለባቸው። የድርጅታዊ አመራር ሳይንስ እንደሚያስተምረው፤ የማይለወጥ ነገር ቢኖር ራሱ ለውጥ ብቻ ነው።
ለውጥን ለማስተናገድ ዝግጁ ያልኾነ ድርጅት በፍጥነት በሚለወጡ ዓለምአቀፋዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ምክንያት ተደናቅፎ መውደቁ አይቀርም። ኢዜማ እንደ ድርጅት የአመራር መተካካትን የሚያከናውንበት ሥርዐት አለው። በየሦስት ዓመቱ ግልጽ ውድድር በማድረግ አዳዲስ አመራሮችና አስተሳሰቦች እንዲስተናገዱ ያደርጋል። ከዚህ አንፃር ፓርቲያችን ለለውጥ ዝግ አይደለም ማለት ይቻላል። ከሌሎች ድርጅታዊ የለውጥ አስተዳደር ማዕቀፎች አንፃር ግን እጅግ ብዙ መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች እንዳሉ እናምናለን።
በተለይም የአሠራርና የመዋቅር ማሻሻያዎችን እንደአስፈላጊነቱ ለመተግበር የሚያስችል የለውጥ አስተዳደር ሥርዐት ባለመኖሩ፤ የድርጅታችንን ዕድገት እንዳይፋጠን አድርጎታል። ለአሠራር ምቹ ያልኾኑ ጉዳዮች ዕየታዩ ሳይሻሻሉ በመቆየታቸው የኢዜማ ድርጅታዊ ጥንካሬ እንዲላላ ኾኗል።
በመኾኑም የታቀደና ግብታዊ ያልኾነ ለውጥ ለማስናገድ አልተቻለም። ስለዚህም፤ ንሥር ራሱን እያደሠ ሕይወቱን እንደ አዲስ እንደሚኖረው፤ ኢዜማም ዘመኑን የዋጀ የለውጥ አስተዳደር እንዲኖረው አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከተቋማዊ የለውጥ አስተዳደር አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk.
👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
ሴቶችን እና አካል ጉዳተኞችን በፖለቲካ ፓርቲ አባልነት እንዲሁም አመራርነት በስፋት ማሳተፍ ከኮታ ማሟያነት ባለፈ ማኅበራዊ ፍትሕን ለማስፈን አንዱ መሣሪያ እንደኾነ "ኢዜማን በልኩ!" ብለን የተሰባሰብን ዕጩ አመራሮች በጽኑ እናምናለን። ዋነኛው የኢዜማ ልክ አካታችነት መኾኑንም እንገነዘባለን።
አካታችነት የሚካተቱ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ለማስደሰት የሚደረግ ብቻ ሳይኾን፤ ለዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ችግሮች መፍትሔ የማፍለቂያ መንገድም ጭምር ነው። በታሪክ ሂደትና በፖሊሲዎች አለመፈጸም ምክንያት ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በተለይም በፖለቲካው ዘርፍ በሚገባው ልክ አለመሳተፋቸው ብዙ ክፍተቶችን ፈጥሯል።
ከምንም በላይ ሴቶች እና አካል ጉዳተኛ ዜጎች በግለሰብ ደረጃ ያላቸውን አቅም ለሀገር እንዳያበረክቱ ኾኗል። ማኅበራዊና ቤተሰባዊ ቁርኝቶች እንዲበላሹ ያደረገውም ሴቶችና አካል ጉዳተኞችን የሚያካትት ባሕል ባለመኖሩ ምክንያት ነው። በመኾኑም፤ “ኢዜማን በልኩ!” በሚል መርሕ የተሰባሰብነውን አመራሮች ከመረጣችሁን ከሴቶችና አካል ጉዳተኞች አካታችነት አንፃር የሚከተሉትን ቁልፍ ተግባራት እናከናውናለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
#ኢዜማን_በልኩ !!
የሴቶችና የአካል ጉዳተኞች አካታችነት
ሴቶችን እና አካል ጉዳተኞችን በፖለቲካ ፓርቲ አባልነት እንዲሁም አመራርነት በስፋት ማሳተፍ ከኮታ ማሟያነት ባለፈ ማኅበራዊ ፍትሕን ለማስፈን አንዱ መሣሪያ እንደኾነ "ኢዜማን በልኩ!" ብለን የተሰባሰብን ዕጩ አመራሮች በጽኑ እናምናለን። ዋነኛው የኢዜማ ልክ አካታችነት መኾኑንም እንገነዘባለን።
አካታችነት የሚካተቱ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ለማስደሰት የሚደረግ ብቻ ሳይኾን፤ ለዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ችግሮች መፍትሔ የማፍለቂያ መንገድም ጭምር ነው። በታሪክ ሂደትና በፖሊሲዎች አለመፈጸም ምክንያት ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በተለይም በፖለቲካው ዘርፍ በሚገባው ልክ አለመሳተፋቸው ብዙ ክፍተቶችን ፈጥሯል።
ከምንም በላይ ሴቶች እና አካል ጉዳተኛ ዜጎች በግለሰብ ደረጃ ያላቸውን አቅም ለሀገር እንዳያበረክቱ ኾኗል። ማኅበራዊና ቤተሰባዊ ቁርኝቶች እንዲበላሹ ያደረገውም ሴቶችና አካል ጉዳተኞችን የሚያካትት ባሕል ባለመኖሩ ምክንያት ነው። በመኾኑም፤ “ኢዜማን በልኩ!” በሚል መርሕ የተሰባሰብነውን አመራሮች ከመረጣችሁን ከሴቶችና አካል ጉዳተኞች አካታችነት አንፃር የሚከተሉትን ቁልፍ ተግባራት እናከናውናለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት
#ኢዜማን_በልኩ !!
ለአንድ ተቋም ስኬት አስፈላጊ ምሶሶ ከኾኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ የፋይናንስ ሥርዐት ነው። ኢዜማ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የፋይናንስ የሥራ ክፍል በማቋቋም ድርጅቱ ዓላማውን እንዲያሳካ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
በተለይም በምርጫ 2013 ወቅት ለቅስቀሳና ለምርጫ አፈጻጸም የሚያስፈልጉ ወጪዎችን ለመሸፈን ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ተከናውነዋል። ነገር ግን ከምርጫው መጠናቀቅ በኋላ የምርጫ ወረዳዎች ራሳቸውን በገቢ ባለመቻላቸው አብዛኛዎቹ መዋቅሮቻችን ያለቢሮ በየቤቱና በየካፌው ስብሰባ ለማድረግ ተገድደዋል።
ዛሬም ለኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ የሚሳተፉ አባላት ወጪያቸውን በምርጫ ወረዳቸው ደረጃ ሸፍነው መሳተፍ አልቻሉም፡፡
በእርግጥ ችግሩ ከሌሎች ድርጅታዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዘ ቢኾንም፤ ድርጅታዊ የፋይናንስ አስተዳደር ሥርዐቱ ግን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራበት አይደለም። በዚህም ምክንያት የሃብት ማሰባሰብ፣ የገቢ ምንጮችን ማስፋት፣ ያሉትን የፋይናንስ ሃብቶች ማስተዳደር እንዲሁም ቀጣይ የፋይናንስ ዕቅዶችን በተመለከተ በድርጅታችን ውስጥ ሰፊ ክፍተቶች ይስተዋላሉ። ዓመታዊ በጀቶችን ስትራቴጂያዊ ለኾኑ ጉዳዮች በብልሀት የመጠቀም ድክመትም የችግሩ መገለጫ ነው።
በመኾኑም፤ የድርጅታችንን ስትራቴጂያዊ ግቦች የሚያግዝ የፋይናንስ ሥርዐት ለማስፈን አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከውጤታማ የፋይናንስ አስተዳደር አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
#ኢዜማን_በልኩ !!
ውጤታማ የፋይናንስ አስተዳደር
ለአንድ ተቋም ስኬት አስፈላጊ ምሶሶ ከኾኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ የፋይናንስ ሥርዐት ነው። ኢዜማ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የፋይናንስ የሥራ ክፍል በማቋቋም ድርጅቱ ዓላማውን እንዲያሳካ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
በተለይም በምርጫ 2013 ወቅት ለቅስቀሳና ለምርጫ አፈጻጸም የሚያስፈልጉ ወጪዎችን ለመሸፈን ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ተከናውነዋል። ነገር ግን ከምርጫው መጠናቀቅ በኋላ የምርጫ ወረዳዎች ራሳቸውን በገቢ ባለመቻላቸው አብዛኛዎቹ መዋቅሮቻችን ያለቢሮ በየቤቱና በየካፌው ስብሰባ ለማድረግ ተገድደዋል።
ዛሬም ለኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ የሚሳተፉ አባላት ወጪያቸውን በምርጫ ወረዳቸው ደረጃ ሸፍነው መሳተፍ አልቻሉም፡፡
በእርግጥ ችግሩ ከሌሎች ድርጅታዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዘ ቢኾንም፤ ድርጅታዊ የፋይናንስ አስተዳደር ሥርዐቱ ግን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራበት አይደለም። በዚህም ምክንያት የሃብት ማሰባሰብ፣ የገቢ ምንጮችን ማስፋት፣ ያሉትን የፋይናንስ ሃብቶች ማስተዳደር እንዲሁም ቀጣይ የፋይናንስ ዕቅዶችን በተመለከተ በድርጅታችን ውስጥ ሰፊ ክፍተቶች ይስተዋላሉ። ዓመታዊ በጀቶችን ስትራቴጂያዊ ለኾኑ ጉዳዮች በብልሀት የመጠቀም ድክመትም የችግሩ መገለጫ ነው።
በመኾኑም፤ የድርጅታችንን ስትራቴጂያዊ ግቦች የሚያግዝ የፋይናንስ ሥርዐት ለማስፈን አባላት ድምጽ ሰጥተው የሚመርጡን ከኾነ ከውጤታማ የፋይናንስ አስተዳደር አንፃር የሚከተሉትን ጉዳዮች ተግባራዊ እናደርጋለን።
ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇
https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk
ከላይ በዝርዝር ለመግለፅ እንደተሞከረው ኢዜማ እንደገና ስንል ምን ማለታችን ነው? በማለት በገለፅነው መሰረት የፓርቲያችን ማሻሻያዎች ለዘለቀታነት ከሚያስፈልጋቸው የውስጥ ግምገማ: የመዋቅርና አደረጃጀት ኹናቴ እና ተተኪ አባላትና አመራሮችን ከማፍራት አኳይ ተመልክተናል። ይህ ከመሆኑ በፊት የኢዜማ እንደገና ማሻሻያ ሀሳብ አስፈላጊነት ለምንድን ነው የሚለውን መግለፅ አስፈላጊ ነው። ፓርቲያችን ሀገራዊ ተደራሽነት ያለው እንደመሆኑ ከሚጠበቅብን ሀላፊነት አንፃር የኢዜማ እንደገና ማሻሻያ ሀሳብ በግልፅ የሚተገበርበትን አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ይጠበቅብናል።
ኢዜማን እንደገና ማሻሻል ጊዜውን የሚመጥን እና ወቅታዊውን የፖለቲካ ተለዋዋጭነት የሚስተካከል ቁመና ላይ ለማድረስ ይረዳናል። ከዚህ ቀደም ፓርቲያችን በሚመሰረትበት ወቅት የነበረው ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ የፖለቲካ ብያነ ከአሁኑ እና ወደፊት ሊመጣ ከሚችለው የፖለቲካ ውስብስብነት አንፃር ፓርቲያችን ራሱን በውስጥ ተሀድሶ በመገምገም እንደገና ማሻሻል አለበት ብለን እናምናለን። ኢዜማ ሲደራጅ የነበረው የኢትዮጵያ ነገባራዊ ፖለቲካ በአሁኑ ሰዓት የተለየ ቅርፅና ይዘት ላይ ስለሆነ በዚያው ትዪዩ ዋና ዋና የፕሮግራም: የደንብ: የፖሊሲ: የአሠራር: የአደረጃጀትና ሌሎች መስኮችን በማጥናትና በማስጠናት ብቁ ተወዳዳሪ ብቻ ሳይሆን መሪ የፖለቲካ ድርጅት እንዲሆን ኢዜማን እንደገና መስራት ይጠበቅብናል።
የዚህ የማሻሻያ ሀሳብ የሚፈለግበት ዐበይት ምክንያቶቹ እንደሚከተሉት ቀርቀዋል።
1, በሀገር አቀፍ ደርጃ የምንታገልለት የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታን በመገምገም በቀጣይ ለምናደርገው የማህበራዊ ፍትህ መርሆዎች ግብ ለመምታት
2, የኢዜማ የውስጥ ደክመቶቹንና ውጫዊ ገፅታ ግንባታውን ለማሻሻል
3, የፓርቲያችን ነባር አደረጃጀቶችን ለማጠናከርና አዲስ አደረጃጀቶችን ለመፍጠር
4, ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎች ቅድሜ ዝግጅት ለማድረግ
5, የኢዜማን ህዝባዊ ቅቡልነት ለማደስና አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ ፓርቲያችን ኢዜማ ማሻሻያ ተደርጎበት እንደገና ወደ ገናናነቱ መመለስ ስላለበት እኛም እናንተ ብትመርጡን በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን አድርገን እንሰራለን።
ኢዜማን እንደገና ለማሻሻል የያዝናቸው የመነሻ ምክንያቶች በሙሉ እና በቅንጅት የፓርቲያችን ህልውና የሚያረጋግጡ ናቸው ብለን እናምናለን። ከላይ የተጠቀሱትን በዝርዝር ለመመልከት በቅን ልቦና የራስን Ego (ዕብሪት) በማክሸፍ በቀጣይ ሁላችንም በመሰጠት የምንታገልላቸው የጋራ ዓላማዎቻችን ናቸው። እያንዳንዱን ነጥቦችን በአጭሩና በግልፅ ቋንቋ ማብራራቱ አስፈላጊ በመሆኑ እንደሚከተለው ዘርዝረናቸዋል።
1, በሀገር አቀፍ ደርጃ የምንታገልለት የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታን በመገምገም በቀጣይ ለምናደርገው የማህበራዊ ፍትህ መርሆዎች ግብ ለመምታት
ኢዜማን እንደገና ማሻሻል እንዳለብን እናምናለን። ፓርቲያችን በውስጡ ዴሞክራሲን እየተለማመደ የሚገኝ ፈር ቀዳጅ ድርጅት መሆኑ እሙን ነው። ይህ ለሰለጠነ ፖለቲካ ከሚፈለጉት ግንባር ቀደም ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በቀጣይም ኢዜማ አካታችነቱ ላይ በማትኮር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ሴቶች የሚወስኑበት: አካል ጉዳተኞች የሚመሩት እና ወጣቶች የሚሰበስቡት የፖለቲካ ጥምረት መፍጠር ይገባናል ብለን እናምናለን። ኢዜማ አካታችነቱ እየሰፋ የሚሄድ ፓርቲ ሆኖ ግልፀኝነቱ አርዓያ ሊሆን ይገባዋል ብለን እናምናለን። የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች በዋናነት ለሚቆሙለት የዜጎች የጤና አጠባበቅ: የትምህርትና አዕምሮ ማጎልመቻ ስልጠናዎች ተደራሽነትና ጥራት: የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ከየተቋማቱ በመገምገም በቀጣይ ለሚከናወነው ፖለቲካ ትግል በአትኩሮት የሚሰራበትን ዘርፍ መለየትና አተገባበሩን እንደፓርቲ መምራት አስፈላጊ በመሆኑ መሠረታዊ የማህበራዊ ፍትህ አምዶችን በመለየት ለአዲስ የትግል ንቅናቄ መዘጋጀት ስላለበት ፓርቲያችን እንደገና ማሻሻያ ማድረግ ይኖርበታል ብለን እናምናለን።
2, የኢዜማ የውስጥ ደክመቶቹንና ውጫዊ ገፅታ ግንባታውን ለማሻሻል
ፓርቲያችን ከሌላ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ሲነፃፀር የተሻለ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው። ህግና መመሪያን በማዘጋጀት: ደንቦችን ወደ ተግባር በመለወጥ: በአንፃራዊነት የተሻለ መሠረት ላይ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው። ቢሆንም ኢዜማ እንደሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ዕኩልነት ፍትህ ለሚያደርገው የዓላማ ፅናቱ እና ከሚጠበቅበት አንፃር ልል የአሠራር ክፍተቶችና የውስጥ ድክመቶች እንዳሉት አይካድም። በህግና በመመሪያ ፓርቲያችን ያልተማከለ ስርዓት የቀረፀ ቢሆንም ግን አፈፃፀም ላይ የሚስተዋለው የሀይልና የስልጣን ማዕከላዊነትን ማስቀረት ተቀዳሚ ሥራችን ይሆናል። የኢዜማ ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው የጠቅላላ ጉባዔ ለቀጣይ 3 ዓመታት ፓርቲያችንን በአመራርነት እንድናገለግል ከመረጠን በየውይይት አጀንዳው የሚከሰተውን የሀብት ማሰባሰብ ስራን በአንድ መምሪያ አደራጅተን ለቀጣይ የሀብት አሰባሰብ የስራ ክፍልን እናደራጃለን። ከድክመቶቻችን አንዱና በአደባባይ ከሚያስወቅሰን መካከል ቀዳሚ የፓርቲ ልህቃንና ገለልተኛ ልህቃን ከኢዜማ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ማጥበቅ ዋና ተግባራችን ይሆናል። ስለዚህ ኢዜማን እንደገና በማሻሻል የተሻለ ቅርርብና ግንኙነት እንድኖረን እናደርጋለን።
3, የፓርቲያችን ነባር አደረጃጀቶችን ለማጠናከርና አዲስ አደረጃጀቶችን ለመፍጠር ኢዜማ እንደገና ማሻሻያ መደረግ አለበት።
የኢዜማ አደረጃጀት እንደሚታወቀው ከታችኛው የምርጫ ክልል መሠረት የተጣለለትና በመሰረቱ የፀና ፓርቲ ነው። አሃዛዊ መረጃውች እንደሚጠቁሙን ኢዜማ በምስረታው ወቅት ከነበረው መጠነ ተደራሽነት በአሁኑ ሰዓት በእጅጉ ቀንሶ እንደሚገኝ ይታወቃል። ይህ እያሽቆለቆለ ያለውን የመዋቅር ቁጥር ለመታደግ በየአስተዳደራዊ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የኢዜማን መዋቅር የሚደግፉ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ቢሮዎች ለመክፈት ፓርቲው የተወሰኑ ማሻሻያዎችን ማድረግ አለበት። ይህ በምርጫ ክልሎች የሚሳበብ ድክመትን ለማስቀረት እንዲሁም የአባላት ፖለቲካዊ ተሳትፎን ለመጨመር አስፈላጊ ማሻሻያ ማድረግ ይጠበቅብናል።
የኢዜማ እንቅስቃሴ ዘመን ያፈራውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁሉም ትግል በአካል ስለማይፈፀም እንደፓርቲ 'ዲጂታል ኢዜማ' የሚል ፕሮግራም ቀርፀን በዲጂታል ዓለምና በሰው መሰል አስተውሎት የተደገፉ ስራዎችን ለመስራት ከአሁን የአደረጃጀት ማሻሻያዎችን እንደገና መፈተሽ አለበት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በቀጠይ ከሚፈትናቸው የሰው መሰል አስተውሎትና የዲጂታል ውንጀላዎች አንፃር ኢዜማ ከወዲሁ ቅድሜ ዝግጅት አድርጎ ጠቅላላ ጉባዔው የፓርቲያችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ጊዜ ያመጣቸውን ዘመነኛ ዕውቀቶችን በመጠቀም ከዘመኑ ጋር ዕኩል መራመድ ይጠበቅበታል ብለን እናምናለን።
4, ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎች ቅድሜ ዝግጅት ለማድረግ ኢዜማን እንደገና ማደራጀትና ማሻሻል እንደሚያስፈልግ እንረዳለን።
ኢዜማን እንደገና ማሻሻል ጊዜውን የሚመጥን እና ወቅታዊውን የፖለቲካ ተለዋዋጭነት የሚስተካከል ቁመና ላይ ለማድረስ ይረዳናል። ከዚህ ቀደም ፓርቲያችን በሚመሰረትበት ወቅት የነበረው ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ የፖለቲካ ብያነ ከአሁኑ እና ወደፊት ሊመጣ ከሚችለው የፖለቲካ ውስብስብነት አንፃር ፓርቲያችን ራሱን በውስጥ ተሀድሶ በመገምገም እንደገና ማሻሻል አለበት ብለን እናምናለን። ኢዜማ ሲደራጅ የነበረው የኢትዮጵያ ነገባራዊ ፖለቲካ በአሁኑ ሰዓት የተለየ ቅርፅና ይዘት ላይ ስለሆነ በዚያው ትዪዩ ዋና ዋና የፕሮግራም: የደንብ: የፖሊሲ: የአሠራር: የአደረጃጀትና ሌሎች መስኮችን በማጥናትና በማስጠናት ብቁ ተወዳዳሪ ብቻ ሳይሆን መሪ የፖለቲካ ድርጅት እንዲሆን ኢዜማን እንደገና መስራት ይጠበቅብናል።
የዚህ የማሻሻያ ሀሳብ የሚፈለግበት ዐበይት ምክንያቶቹ እንደሚከተሉት ቀርቀዋል።
1, በሀገር አቀፍ ደርጃ የምንታገልለት የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታን በመገምገም በቀጣይ ለምናደርገው የማህበራዊ ፍትህ መርሆዎች ግብ ለመምታት
2, የኢዜማ የውስጥ ደክመቶቹንና ውጫዊ ገፅታ ግንባታውን ለማሻሻል
3, የፓርቲያችን ነባር አደረጃጀቶችን ለማጠናከርና አዲስ አደረጃጀቶችን ለመፍጠር
4, ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎች ቅድሜ ዝግጅት ለማድረግ
5, የኢዜማን ህዝባዊ ቅቡልነት ለማደስና አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ ፓርቲያችን ኢዜማ ማሻሻያ ተደርጎበት እንደገና ወደ ገናናነቱ መመለስ ስላለበት እኛም እናንተ ብትመርጡን በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን አድርገን እንሰራለን።
ኢዜማን እንደገና ለማሻሻል የያዝናቸው የመነሻ ምክንያቶች በሙሉ እና በቅንጅት የፓርቲያችን ህልውና የሚያረጋግጡ ናቸው ብለን እናምናለን። ከላይ የተጠቀሱትን በዝርዝር ለመመልከት በቅን ልቦና የራስን Ego (ዕብሪት) በማክሸፍ በቀጣይ ሁላችንም በመሰጠት የምንታገልላቸው የጋራ ዓላማዎቻችን ናቸው። እያንዳንዱን ነጥቦችን በአጭሩና በግልፅ ቋንቋ ማብራራቱ አስፈላጊ በመሆኑ እንደሚከተለው ዘርዝረናቸዋል።
1, በሀገር አቀፍ ደርጃ የምንታገልለት የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታን በመገምገም በቀጣይ ለምናደርገው የማህበራዊ ፍትህ መርሆዎች ግብ ለመምታት
ኢዜማን እንደገና ማሻሻል እንዳለብን እናምናለን። ፓርቲያችን በውስጡ ዴሞክራሲን እየተለማመደ የሚገኝ ፈር ቀዳጅ ድርጅት መሆኑ እሙን ነው። ይህ ለሰለጠነ ፖለቲካ ከሚፈለጉት ግንባር ቀደም ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በቀጣይም ኢዜማ አካታችነቱ ላይ በማትኮር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ሴቶች የሚወስኑበት: አካል ጉዳተኞች የሚመሩት እና ወጣቶች የሚሰበስቡት የፖለቲካ ጥምረት መፍጠር ይገባናል ብለን እናምናለን። ኢዜማ አካታችነቱ እየሰፋ የሚሄድ ፓርቲ ሆኖ ግልፀኝነቱ አርዓያ ሊሆን ይገባዋል ብለን እናምናለን። የማህበራዊ ፍትህ ጥያቄዎች በዋናነት ለሚቆሙለት የዜጎች የጤና አጠባበቅ: የትምህርትና አዕምሮ ማጎልመቻ ስልጠናዎች ተደራሽነትና ጥራት: የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ከየተቋማቱ በመገምገም በቀጣይ ለሚከናወነው ፖለቲካ ትግል በአትኩሮት የሚሰራበትን ዘርፍ መለየትና አተገባበሩን እንደፓርቲ መምራት አስፈላጊ በመሆኑ መሠረታዊ የማህበራዊ ፍትህ አምዶችን በመለየት ለአዲስ የትግል ንቅናቄ መዘጋጀት ስላለበት ፓርቲያችን እንደገና ማሻሻያ ማድረግ ይኖርበታል ብለን እናምናለን።
2, የኢዜማ የውስጥ ደክመቶቹንና ውጫዊ ገፅታ ግንባታውን ለማሻሻል
ፓርቲያችን ከሌላ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ሲነፃፀር የተሻለ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው። ህግና መመሪያን በማዘጋጀት: ደንቦችን ወደ ተግባር በመለወጥ: በአንፃራዊነት የተሻለ መሠረት ላይ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው። ቢሆንም ኢዜማ እንደሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ዕኩልነት ፍትህ ለሚያደርገው የዓላማ ፅናቱ እና ከሚጠበቅበት አንፃር ልል የአሠራር ክፍተቶችና የውስጥ ድክመቶች እንዳሉት አይካድም። በህግና በመመሪያ ፓርቲያችን ያልተማከለ ስርዓት የቀረፀ ቢሆንም ግን አፈፃፀም ላይ የሚስተዋለው የሀይልና የስልጣን ማዕከላዊነትን ማስቀረት ተቀዳሚ ሥራችን ይሆናል። የኢዜማ ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው የጠቅላላ ጉባዔ ለቀጣይ 3 ዓመታት ፓርቲያችንን በአመራርነት እንድናገለግል ከመረጠን በየውይይት አጀንዳው የሚከሰተውን የሀብት ማሰባሰብ ስራን በአንድ መምሪያ አደራጅተን ለቀጣይ የሀብት አሰባሰብ የስራ ክፍልን እናደራጃለን። ከድክመቶቻችን አንዱና በአደባባይ ከሚያስወቅሰን መካከል ቀዳሚ የፓርቲ ልህቃንና ገለልተኛ ልህቃን ከኢዜማ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ማጥበቅ ዋና ተግባራችን ይሆናል። ስለዚህ ኢዜማን እንደገና በማሻሻል የተሻለ ቅርርብና ግንኙነት እንድኖረን እናደርጋለን።
3, የፓርቲያችን ነባር አደረጃጀቶችን ለማጠናከርና አዲስ አደረጃጀቶችን ለመፍጠር ኢዜማ እንደገና ማሻሻያ መደረግ አለበት።
የኢዜማ አደረጃጀት እንደሚታወቀው ከታችኛው የምርጫ ክልል መሠረት የተጣለለትና በመሰረቱ የፀና ፓርቲ ነው። አሃዛዊ መረጃውች እንደሚጠቁሙን ኢዜማ በምስረታው ወቅት ከነበረው መጠነ ተደራሽነት በአሁኑ ሰዓት በእጅጉ ቀንሶ እንደሚገኝ ይታወቃል። ይህ እያሽቆለቆለ ያለውን የመዋቅር ቁጥር ለመታደግ በየአስተዳደራዊ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የኢዜማን መዋቅር የሚደግፉ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ቢሮዎች ለመክፈት ፓርቲው የተወሰኑ ማሻሻያዎችን ማድረግ አለበት። ይህ በምርጫ ክልሎች የሚሳበብ ድክመትን ለማስቀረት እንዲሁም የአባላት ፖለቲካዊ ተሳትፎን ለመጨመር አስፈላጊ ማሻሻያ ማድረግ ይጠበቅብናል።
የኢዜማ እንቅስቃሴ ዘመን ያፈራውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሁሉም ትግል በአካል ስለማይፈፀም እንደፓርቲ 'ዲጂታል ኢዜማ' የሚል ፕሮግራም ቀርፀን በዲጂታል ዓለምና በሰው መሰል አስተውሎት የተደገፉ ስራዎችን ለመስራት ከአሁን የአደረጃጀት ማሻሻያዎችን እንደገና መፈተሽ አለበት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በቀጠይ ከሚፈትናቸው የሰው መሰል አስተውሎትና የዲጂታል ውንጀላዎች አንፃር ኢዜማ ከወዲሁ ቅድሜ ዝግጅት አድርጎ ጠቅላላ ጉባዔው የፓርቲያችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ጊዜ ያመጣቸውን ዘመነኛ ዕውቀቶችን በመጠቀም ከዘመኑ ጋር ዕኩል መራመድ ይጠበቅበታል ብለን እናምናለን።
4, ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎች ቅድሜ ዝግጅት ለማድረግ ኢዜማን እንደገና ማደራጀትና ማሻሻል እንደሚያስፈልግ እንረዳለን።
እንደሚታወቀው የፖለቲካ ፓርቲዎች በዋናነት የሚደራጁት በሰላማዊ መንገድ ስልጣን ተረክበው ፖሊሲያቸውን ማስፈፀምና ያመኑበት ለመወሰን ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ በየምርጫ ውድድሩ የሚከናወኑትን ሂደቶችን በማለፍ ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረት ነው። እኛም ፓርቲያችን በቀጣይ በሚደረገው 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ የየምክር ቤቶችን ወንበር መቆናጠጥ ይጠበቅብናል። ለዚህ ደግሞ የሚጠበቅብን ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ ብቻ ሳይ ግዴታችንም ነው። ካለፈው 6ኛው ሀገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ በቀሰምነው ልምድና ዕውቀት በቀጣይ ለሚከናወነው ምርጫ ራሱን በአደረጃጀትም ሆነ በፖሊሲ ቁመና የደረጀ ዕጩዎችንና ተመራጮችን ለማዘጋጀት ሲባል በአዲሱ የምርጫ ቦርድ አዋጅ መሠረት ኢዜማም እንደገና ራሱን በመፈተሽ የማሻሻያ እርምጃዎችን መውሰድ አለበት።
5, የኢዜማን ህዝባዊ ቅቡልነት ለማደስና አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ
ፓርቲያችን ኢዜማ ማሻሻያ ተደርጎበት እንደገና ወደ ገናናነቱ መመለስ ስላለበት ኢዜማ እንደገና ራሱን ማቅረብ አለበት የሚል አቋም አለን። የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ የህልውናው መሠረት በውስጡ የያዘው ፖሊሲ እና መሪዎቹ ላይ ያለው ህዝባዊ ቅቡልነት ነው። ኢዜማ ተወዳጅ አመራሮች እና የተሻሉ ፖሊሲዎችን በውስጡ ይዞ ህዝባዊ ቅቡልነትን እስካላገኘ ድረስ በቀጣይ ለሚጠብቀን ሀገራዊ ሀላፊነት ዐቢይ ተግዳሮት ይሆንብናል። የኢዜማ አባላት እና ደጋፊዎቹ በፓርቲያቸው አጠቃል አቋም ላይ የመተማመኛ ድምፅ እንዲሰጡ ከተደረገ በኋላ ህዝባዊ ቅቡልነት ያሳጡንን ውሳኔዎቻችን የመቀልበስ ግዴታ አለብን ብለን እናምናለን። ኢዜማ በአባላቱም ይሁን በመራጩ ህዝብ ተቀባይነትንና ቅቡልነት ለማግኘት እስከዛሬ የመጣበትንና የወሰናቸውን ውሳኔዎችን እንደገና በማጤን ወደ ግቡ መድረስ አለበት።
የኢዜማን ማሻሻያ የጠቅላላ ጉባዔው እንዲቀበል የምንጠይቅበት ምክንያቶች በዋናነት ከላይ የጠቅስናቸው ሲሆኑ እኛ በዕጩነት የቀረብነው ተወዳዳሪዎች ኢዜማን እንደገና ማሻሻል አስፈላጊነቱን ያመንበትን ምክንያቶችን አቅረበንላችኋል። የጉባዔ ተሳታፊዎች በሙሉ ድምፅ የኢዜማን እንደገና መሻሻል በመቀበል ለአገልጋይነት እንድትመርጡን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃችኋለን።
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ
5, የኢዜማን ህዝባዊ ቅቡልነት ለማደስና አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ
ፓርቲያችን ኢዜማ ማሻሻያ ተደርጎበት እንደገና ወደ ገናናነቱ መመለስ ስላለበት ኢዜማ እንደገና ራሱን ማቅረብ አለበት የሚል አቋም አለን። የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ የህልውናው መሠረት በውስጡ የያዘው ፖሊሲ እና መሪዎቹ ላይ ያለው ህዝባዊ ቅቡልነት ነው። ኢዜማ ተወዳጅ አመራሮች እና የተሻሉ ፖሊሲዎችን በውስጡ ይዞ ህዝባዊ ቅቡልነትን እስካላገኘ ድረስ በቀጣይ ለሚጠብቀን ሀገራዊ ሀላፊነት ዐቢይ ተግዳሮት ይሆንብናል። የኢዜማ አባላት እና ደጋፊዎቹ በፓርቲያቸው አጠቃል አቋም ላይ የመተማመኛ ድምፅ እንዲሰጡ ከተደረገ በኋላ ህዝባዊ ቅቡልነት ያሳጡንን ውሳኔዎቻችን የመቀልበስ ግዴታ አለብን ብለን እናምናለን። ኢዜማ በአባላቱም ይሁን በመራጩ ህዝብ ተቀባይነትንና ቅቡልነት ለማግኘት እስከዛሬ የመጣበትንና የወሰናቸውን ውሳኔዎችን እንደገና በማጤን ወደ ግቡ መድረስ አለበት።
የኢዜማን ማሻሻያ የጠቅላላ ጉባዔው እንዲቀበል የምንጠይቅበት ምክንያቶች በዋናነት ከላይ የጠቅስናቸው ሲሆኑ እኛ በዕጩነት የቀረብነው ተወዳዳሪዎች ኢዜማን እንደገና ማሻሻል አስፈላጊነቱን ያመንበትን ምክንያቶችን አቅረበንላችኋል። የጉባዔ ተሳታፊዎች በሙሉ ድምፅ የኢዜማን እንደገና መሻሻል በመቀበል ለአገልጋይነት እንድትመርጡን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃችኋለን።
ዶ/ር ካሣሁን ደለነ
ዕጩ ዋና ፀሐፊ