Telegram Web
Audio
#ኪታብ ዑምደቱል አህካም
#በፈትህ አባቦራ መስጂድ
#ዘወትር ረቡዕ እና ጁመዓ ከመግሪብ- ዒሻ #በኡስታዝ ካሚል ጣሃ   ደርስ በድምፅ ክፍል #57 መከታተልና መቅራት ትችላላችሁ። #እንዳያመልጥዎ
ሰላማዊ ቀልብ!

ከአብደላህ ቢን ዑመር (رضي الله عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፦

﴿قيل لرسولِ اللهِ صلَّى اللهُ عليْهِ وسلَّمَ أيُّ الناسِ أفضلُ قال كلُّ مخمومِ القلبِ صدوقِ اللسانِ قالوا صدوقُ اللسانِ نعرفُه فما مخمومُ القلبِ قال هو التقيُّ النقيُّ لا إثمَ فيه ولا بغيَ ولا غِلَّ ولا حسدَ﴾

“የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ተባሉ፦ ከሰዎች በላጭ ማነው? አሉ፦ ቀልቡ መኽሙውም (ንፁህ) የሆነና እውነት ተናጋሪ የሆነ ምላስ (አንደበት) ያለው ነው። በዚህ ግዜ ሰሃቦች እንዲህ አሉ፡ እውነት ተናጋሪ ምላስ ምን እንደሆነ እናውቃለን። ንፁህ ቀልብ ያለው ሲባል ምን ማለት ነው? አሉ፡ እሱ ማለት አላህን የሚፈራና ንፁህ የሆነ፣ በውስጡ በደል ምቀኝነትና ክፋት ጥላቻ የሌለው የሆነ ነው።”

📚 ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል፡ 3416



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ጁምዓ 0⃣2⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
የአሹራ ቀን ፆም!

📌ለመልካም ስራ አስተዋሽ እንሁን

ከኢብኑ አባስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾

“የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1134

ከአቢ ቀታዳ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾

“የአሹራ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#ሰብት 0⃣3⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
ከረመዳን ቀጥሎ በላጩ ፆም!

ከአቡ ሁረይራ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿أفضلُ الصِّيامِ بعدَ رمضانَ شَهْرُ اللَّهِ المُحرَّمُ﴾

“ከረመዳን በመቀጠል በላጩ ፆም የአላህ ወር የሆነው የሙሐረም ወር ፆም ነው።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1123

ማስታወሻ፦ የሙሀረም ወር ፆም በኢትዮጵያ ካላንደር አቆጣጠር አርብ ሰኔ 27 ላይ ይሆናል። ከበፊቱ ወይም ከበስተኋላው ያለውን አንድ ቀን ጨምሮ መፆም መዘንጋት የለበትም።



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 0⃣4⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
የመንገድ ሐቅ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿"فَأَعْطُوا الطَّرِيقَ حَقَّهَا" قَالُوا : وَمَا حَقُّ الطَّرِيقِ ؟ قَالَ : " غَضُّ الْبَصَرِ، وَكَفُّ الْأَذَى، وَرَدُّ السَّلَامِ، وَأَمْرٌ بِالْمَعْرُوفِ، وَنَهْيٌ عَنِ الْمُنْكَرِ﴾

“ለ‘መንገድ ሀቁን ስጡት።’ የ‘መንገድ ሀቅ’ ምንድንነው? ሲባሉ፦ እይታን ሰበር ማድረግ፣ አስቸጋሪ የሆነን ነገር ማስወገድ፣ ለሰላምታ ምላሽ መስጠትና በመልካም ነገር ማዘዝ ከመጥፎ ነገር መከልከል ነው።”

📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 2465



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልስነይን 0⃣5⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
ለጌታህ ትዕዛዝ በማደር ከሸይጣን ተለይ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إذا قَرَأَ ابنُ آدَمَ السَّجْدَةَ فَسَجَدَ اعْتَزَلَ الشَّيْطانُ يَبْكِي، يقولُ: يا ويْلِي، أُمِرَ ابنُ آدَمَ بالسُّجُودِ فَسَجَدَ فَلَهُ الجَنَّةُ، وأُمِرْتُ بالسُّجُودِ فأبَيْتُ فَلِيَ النّارُ﴾

“የአደም ልጅ ቁርዓንን ቀርቶ ሱጁድን ሲያደርግ፤ ሸይጣን እያለቀሰ ይሄዳል። እንዲህም ይላል፦ ዋ! ጥፋቴ! ዋ! ሐዘኔ! የአደም ልጅ ሱጁድ እንዲያደርግ ታዘዘ ሱጁድ አደረገ ለሱ ጀነት ይኖረዋል። እኔም ሱጁድ እንዳደርግ (ለአደም ልጅ) ታዘዝኩ አመፅኩኝ እሳት በኔ ላይ ተወሰነ (ተረጋገጠ)”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 81



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 0⃣6⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
አስደሳች ዜና ከሱና ዩኒቨርሲቲ
ልዩ የክረምት ስልጠና ለሃይስኩል ተማሪዎች ለሁለቱም ፆታ

-ፊቅሁል ዒባዳ
-በአቂዳ/ተውሒድ
-ቁርአን ተፍሲር እና ሲራ
-ኢስላማዊ አዳብ/አኽላቅ
-መሰረታዊ የእስልምና እውቀት
-የህይወት ክህሎት (ተርቢያ)፡ በጊዜ አጠቃቀም ፤ ስሜ  ታዊ ብልህነት ፤ ዲጂታል ሚድያ እና የሥራ ፈጠራ ባህል

በየሁለት ሳምንቱ በታላላቅ ዓሊሞች እና ኡስታዞች የሙሀዶራ ፕሮግራም በቤተሰብና ቀድሞ ለሚመዘገብ ቅናሽ የምናደርግ መሆኑን እየገለፅን ገቢው ለሱና ዩኒቨርሲቲ ማጠናከርያ ይውላል

ምዝገባ አድራሻ፡- ጀሞ ሶስት አዲሱ ሰዒድ ያሲን 2ኛ ፎቅ አዋሽ ባንክ ባለበት መግቢያ
ወይም በስልክ ቁጥራችን በ 0935332424/ 0990452838/ 0990442838 በመደወል መመዝገብ ይቻላል
የምዝገባ ጊዜ
ከሰኔ 24-30, 2017 ዓ.ል ይካሄዳል
ከአቅም በላይ የሆነ ነገር ለገጠመው!

ከአነስ ኢብኑ ማሊክ (رضيﷲ عنه) ተይዞ: ረሱል (ﷺ) እንዲህ እያሉ ዱዓ ያደርጉ ነበር፦

﴿اللهمَّ لا سهلَ إلا ما جعلتَه سهلًا، وأنت تجعلُ الحَزْنَ إذا شئتَ سهلًا﴾

“አላህ ሆይ! አንተ ቀላል ካደረግከው ነገር ውጭ ቀላል የለም፡፡ አንተ ሀዘንን ከሻህ ቀላል ታደርጋለህ፡፡”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 2886



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልዓርቢዓዐ 0⃣7⃣ #ሙሐረም 1⃣4⃣4⃣7⃣
ዱኒያ የተረገመች ናት!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ألا إنَّ الدُّنيا ملعونةٌ ملعونٌ ما فيها، إلّا ذِكرُ اللَّهِ وما والاهُ، وعالِمٌ، أو متعلِّمٌ﴾

“አዋጅ! ዱኒያም ዱኒያ በውስጧ የያዘችው ነገር የተረገመ ነው። አላህን ለማውሳት አጋዥ የሆኑ ነገሮች፣ ዓሊም ወይም ተማሪ ሲቀሩ።”

📚 ሶሂህ አትርጊብ፡ 3244



https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
https://www.tgoop.com/fethababora
⚠️ አይበለውና በኤሌክትሪክ አደጋ የተያዘ ሰው ቢያጋጥምዎ ምን ማድረግ እንደሚኖርብዎት ያውቃሉ? ⚠️

ኤሌክትሪክ ጠቀሜታው የላቀ ቢሆንም በጥንቃቄ ጉድለት በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት ያስከትላል፤ ለሞትም ይዳርጋል፡፡ ታዲያ ሁሌም እራስዎን ከኤሌክትሪክ አደጋ መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ሊሆን ይገባል፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው በኤሌክትሪክ ቢያዝ ወዲያውኑ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ ህይወቱን ሊያድን የሚችልበት አግባብ አለ።

⛔️ አይበለውና በኤሌክትሪክ አደጋ የተያዘ ሰው ቢያጋጥምዎ ምን ማድረግ እንደሚኖርብዎት ያውቃሉ?

የኤሌክትሪክ ምንጭን ማጥፋት ወይም ቆጣሪ ብሬከር መመለስ

ይህ የመጀመሪያውና ዋነኛው እርምጃ ሲሆን፤ የቆጣሪ ብሬከሩ የት እንዳለ ካወቁ በፍጥነት ማጥፋት እና የኤሌክትሪክ ፍሰት መቆሙን ሲያረጋግጡ ብቻ ወደ ተጎጂው መቅረብ፤

ኤሌክትሪክን ወዲያውኑ ማጥፋት ካልቻሉ ተጎጂውን ከኤሌክትሪክ ምንጭ ለማራቅ ደረቅ እና ኤሌክትሪክ የማያስተላልፍ (non-conductive) ነገር ይጠቀሙ፤

በፍፁም ባዶ እጅዎን ወይም እርጥብ ነገርን አይጠቀሙ!

ለምሳሌ:- ደረቅ የእንጨት ዘንግ፣ የፕላስቲክ መጥረጊያ እጀታ፣ ወፍራም ጋዜጣ ወይም መጽሐፍ፣ ወይም የጎማ ምንጣፍ መጠቀም ይችላሉ።

ተጎጂውን አይንኩ! በኤሌክትሪክ የተያዘ ሰው ሰውነታቸው ሊያስተላልፍ ይችላል፤

የኤሌክትሪክ ንዝረት የቆዳ ላይ እና ውስጣዊ ቃጠሎ ሊያስከትል ስለሚችል የተቃጠለውን ወይም የተጎዳውን የሰውነት ክፍል በቀዝቃዛ (በረዶ ባልሆነ) ውሃ በማቀዝቀዝ ንጹህና ደረቅ በሆነ ጨርቅ ይሸፍኑት።

የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ ወደ ህክምና ተቋም ይደውሉ፤

ያስታውሱ‼️

የኤሌክትሪክ አደጋ የሚያስከትል ሁኔታ ሲመለከቱም አደጋው ከመድረሱ በፊት በአቅራቢያዎ ካለ የተቋማችን የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት በአካል ወይም በጥሪ ማዕከሉ 905 እና 904 በመደወል አልያም በማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችን ያሳውቁ!

የእርስዎ ደህንነት ቀዳሚ መሆኑን አይርሱ❗️
እራስዎን ከአደጋ ይጠብቁ❗️
ኤሌክትሪክን በቁም ነገር ይዩት🚫

#Safety_First_Always - #ሁልጊዜም_ቅድሚያ_ለጥንቃቄ⚠️

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
" የዓሹራ ቀን ፆም ያለፈን አንድ አመት ወንጀል ያስምራል»ረሱል ﷺ
ቀኑ የአሹራ 10ኛ ቀን ሲሆን ከፊት ወይም ከሗላ አንድ ቀን እንድንጨምር ታዘናል
የፊታችን ቅዳሜ 10ኛው ቀን ይሆናል!!
Audio
#ኪታብ ዑምደቱል አህካም
#በፈትህ አባቦራ መስጂድ
#ዘወትር ረቡዕ እና ጁመዓ ከመግሪብ- ዒሻ #በኡስታዝ ካሚል ጣሃ   ደርስ በድምፅ ክፍል #58 መከታተልና መቅራት ትችላላችሁ። #እንዳያመልጥዎ
2025/07/03 13:40:56
Back to Top
HTML Embed Code: