ሀገር አለችን የሀገር አውራ
ባባቶቻችን አፅም ወጋግራ
በሥጋና በደም አሻራ
የታነፀች የተሰራች
በጥበብ የደመቀች
በአብሮነት የተዋበች
በአንድነትዋ ፅናት
ጠላት የማይደፍራት
እናም
አባቶች ሞተው የሰርዋት
እኛ በጥጋብ አናፍርሳት
ቢገባን ኖሮ ትርጉሙ
ኢትዮጵያ ማለት ወርቅ ሰሙ
ህብር ነው በቃ አንድነት
ከብሔር በላይ ሰውነት
ኢትዮጵያ ማለት ቅኔ ትርጉሙ
አንድ ነው የሰው ልጅ መላው አለሙ
ልዩነት ቢሻለን ኖሮ
ያበጁት ነበር ድሮ
ኢትዮጵያ አናፍርሳት
ለጠላት አሳልፈን አንስጣት
በአንድነታችን ስንንሸራተት
ያኔ ነው ጠላት የሚያገኛት
የኢትዮጵያ ትጥቅ ማለት
ነውና ህብረ ብሔራዊነት
ጉራጌ ብቻ
ትግራይ ብቻ
ኦሮሞ ብቻ
አማራ ብቻ
ቤንሻንጉል ብቻ
ሶማሌ ብቻ
ወላይታ ብቻ
ሲዳማ ብቻ
ምን ጥቅም አለው ከማነስ ሌላ
የጎጃም ማር ሸዋ ላይ ካልተበላ
የጅማ ቡና መቀሌ ላይ ካልተጠጣ
የወለጋ ቅቤ ሸገር ድረስ ካልመጣ
የሶማሌ ግመል አፋር ካልተሸጠ
አንዱን ያንዱን ፍሬ ካልተለዋወጠ
መለያየት ሞት ነው
እንዴት ለብቻ ይበላል ?
እረ እንዴት ለብቻ ይኖራል?
ሰው እንዴት ከሰው ይርቃል ?
ከሰው ወዴት ይሸሻል?
ሰው ነው የሰው መድኃኒቱ
እንዳለው የአበው ተረቱ
የአባቶችህን ታሪክ ሰልስ
ያገርህ ክብር መልስ
በጠላትህ አዙሪት አትሽከርከር
እንደ አባቶችህ አገርህ አክብር
አትቁም በልዩነት ላይ
አብራላት የአንድነት ፀሐይ
ወድቀህ እንዳትገኝ አደራ
አንድነት አጥብቅ ታሪክ ሥራ
እንደ አሉላ እንደ ቴዎድሮስ
እንደ ምኒልክ እንደ ዮሐንስ
እንደ አብዲሳ አጋ እንደ አባጅፋር
አክሱም ነህ ሲሉ ድረስ ወደ ጎንደር
ጅማ ላይ ክተም ሸገር ላይ እመር
አሥመራ ያንተናት ሂድ ተሻገር
በዛላንበሳ በደብረቢዘን
ሱባኤ ግባ ካሻህ በግሸን
አክሱም ፂዮን ላይ ሄደህ ተቀባ
ወደ ቤተመንግስት ዘልቀህ ልትገባ
ነፍስህን ስጣት ለውድ አገርህ
ተምረህ ተገኝ ከአያት ካባትህ
አገር ሽጦ የት ይታደራል?
የተሸመተው የትስ ይበላል?
አገር እያለልህ በጥበብ የተሰራ
ተው አይበጅህም አፍርሼ ልስራ ።
።
ብርሃኑ ኮሬ(እመጓ)27/10/2013
@fikren
@Rasyisak
ባባቶቻችን አፅም ወጋግራ
በሥጋና በደም አሻራ
የታነፀች የተሰራች
በጥበብ የደመቀች
በአብሮነት የተዋበች
በአንድነትዋ ፅናት
ጠላት የማይደፍራት
እናም
አባቶች ሞተው የሰርዋት
እኛ በጥጋብ አናፍርሳት
ቢገባን ኖሮ ትርጉሙ
ኢትዮጵያ ማለት ወርቅ ሰሙ
ህብር ነው በቃ አንድነት
ከብሔር በላይ ሰውነት
ኢትዮጵያ ማለት ቅኔ ትርጉሙ
አንድ ነው የሰው ልጅ መላው አለሙ
ልዩነት ቢሻለን ኖሮ
ያበጁት ነበር ድሮ
ኢትዮጵያ አናፍርሳት
ለጠላት አሳልፈን አንስጣት
በአንድነታችን ስንንሸራተት
ያኔ ነው ጠላት የሚያገኛት
የኢትዮጵያ ትጥቅ ማለት
ነውና ህብረ ብሔራዊነት
ጉራጌ ብቻ
ትግራይ ብቻ
ኦሮሞ ብቻ
አማራ ብቻ
ቤንሻንጉል ብቻ
ሶማሌ ብቻ
ወላይታ ብቻ
ሲዳማ ብቻ
ምን ጥቅም አለው ከማነስ ሌላ
የጎጃም ማር ሸዋ ላይ ካልተበላ
የጅማ ቡና መቀሌ ላይ ካልተጠጣ
የወለጋ ቅቤ ሸገር ድረስ ካልመጣ
የሶማሌ ግመል አፋር ካልተሸጠ
አንዱን ያንዱን ፍሬ ካልተለዋወጠ
መለያየት ሞት ነው
እንዴት ለብቻ ይበላል ?
እረ እንዴት ለብቻ ይኖራል?
ሰው እንዴት ከሰው ይርቃል ?
ከሰው ወዴት ይሸሻል?
ሰው ነው የሰው መድኃኒቱ
እንዳለው የአበው ተረቱ
የአባቶችህን ታሪክ ሰልስ
ያገርህ ክብር መልስ
በጠላትህ አዙሪት አትሽከርከር
እንደ አባቶችህ አገርህ አክብር
አትቁም በልዩነት ላይ
አብራላት የአንድነት ፀሐይ
ወድቀህ እንዳትገኝ አደራ
አንድነት አጥብቅ ታሪክ ሥራ
እንደ አሉላ እንደ ቴዎድሮስ
እንደ ምኒልክ እንደ ዮሐንስ
እንደ አብዲሳ አጋ እንደ አባጅፋር
አክሱም ነህ ሲሉ ድረስ ወደ ጎንደር
ጅማ ላይ ክተም ሸገር ላይ እመር
አሥመራ ያንተናት ሂድ ተሻገር
በዛላንበሳ በደብረቢዘን
ሱባኤ ግባ ካሻህ በግሸን
አክሱም ፂዮን ላይ ሄደህ ተቀባ
ወደ ቤተመንግስት ዘልቀህ ልትገባ
ነፍስህን ስጣት ለውድ አገርህ
ተምረህ ተገኝ ከአያት ካባትህ
አገር ሽጦ የት ይታደራል?
የተሸመተው የትስ ይበላል?
አገር እያለልህ በጥበብ የተሰራ
ተው አይበጅህም አፍርሼ ልስራ ።
።
ብርሃኑ ኮሬ(እመጓ)27/10/2013
@fikren
@Rasyisak
ዛሬ ቀኑ በጣም ደስ ይላል 😍
😍
አንድ ነገር አስታውስ ሰወች የሚሰጡህ ዋጋ ራስህ ባወጣኸው መሰረት ነው፤ውድ ነሳኝ ብለህ አስበህ ራስህን አክብረህ ከኖርክ ሁሉም ውድ እንደሆንክ አምኖ ያከብርሀል። ራስህን ካረከስክ እና ለራስህ ያለህ ግምት ዝቅ ያለ ከሆነ ምን ትጠብቃለህ ሁሉም ሰው ዝቅ አርጎ ያይሀል፤ ምርጫው ያንተ ነው።
ራስህን ከፍ አርገህ ሰዎች ባይቀበሉህ እንኳን ላንተ ያላቸው ክብር አይቀንስም እንደውም "በውስጣቸው እሱ ግን ራሱን እንደማን ነው ሚያስበው? እኔ የእሱ ድፍረትና በራስ መተማመን ቢኖረኝ የት እደርስ ነበር" ይላሉ። ወዳጄ አይነግሩህም እንጂ ድብን አርገው ነው ሚቀኑብህ። እራስህን አክብረው ወዳጄ
ሸጋ እና የተባረከ የስኬት ቀን ይሁንልን 💚💛❤
@fikren
@Rasyisak
😍
አንድ ነገር አስታውስ ሰወች የሚሰጡህ ዋጋ ራስህ ባወጣኸው መሰረት ነው፤ውድ ነሳኝ ብለህ አስበህ ራስህን አክብረህ ከኖርክ ሁሉም ውድ እንደሆንክ አምኖ ያከብርሀል። ራስህን ካረከስክ እና ለራስህ ያለህ ግምት ዝቅ ያለ ከሆነ ምን ትጠብቃለህ ሁሉም ሰው ዝቅ አርጎ ያይሀል፤ ምርጫው ያንተ ነው።
ራስህን ከፍ አርገህ ሰዎች ባይቀበሉህ እንኳን ላንተ ያላቸው ክብር አይቀንስም እንደውም "በውስጣቸው እሱ ግን ራሱን እንደማን ነው ሚያስበው? እኔ የእሱ ድፍረትና በራስ መተማመን ቢኖረኝ የት እደርስ ነበር" ይላሉ። ወዳጄ አይነግሩህም እንጂ ድብን አርገው ነው ሚቀኑብህ። እራስህን አክብረው ወዳጄ
ሸጋ እና የተባረከ የስኬት ቀን ይሁንልን 💚💛❤
@fikren
@Rasyisak
....በህይወት ትልቁ ቁም ነገር ትምርት መውሰድ ነው። መቼም በስለንም አውቀንም አንጨርስም። ባወቅን ቁጥር ሁሌም እንማር ፣ ሁሌም ለመለወጥ ዝግጁ እንሁን፣ሁሌም ብሩህ ተስፋ ይኑረን።
ብልህ ሰው ዛሬ ላይ አዋቂ ነኝ፣ትክክል ነኝ እኔ ብቻ የሚል ሳይሆን ዛሬ ላይ የህይወትን ትምህርት ከሕፃናት ሳይቀር ለመማር ነገ ላይ ለመሙላት የሚሰናዳ ነው። ብልህ ሰው ትናንትናንና ነገን አስታርቆ የሚኖር ሲሆን በሰው ሁሉ ለመወደድ ሳይሆን ሰውን ሁሉ ለመውደድ የሚጥር ነው።
👉ሜሎሪና ገፅ 184👈
ውብ አሁን 💚💛❤
@fikren
@Rasyisak
ብልህ ሰው ዛሬ ላይ አዋቂ ነኝ፣ትክክል ነኝ እኔ ብቻ የሚል ሳይሆን ዛሬ ላይ የህይወትን ትምህርት ከሕፃናት ሳይቀር ለመማር ነገ ላይ ለመሙላት የሚሰናዳ ነው። ብልህ ሰው ትናንትናንና ነገን አስታርቆ የሚኖር ሲሆን በሰው ሁሉ ለመወደድ ሳይሆን ሰውን ሁሉ ለመውደድ የሚጥር ነው።
👉ሜሎሪና ገፅ 184👈
ውብ አሁን 💚💛❤
@fikren
@Rasyisak
Forwarded from መፅሃፍቶች እና የግጥም ስብስብ..
Start ብላቹ ተሸላሚ አድርጉኝ 🙏 ሽልማቱን አካፍላቹሀለው