Telegram Web
( ዛሬም እንጉርጉሮ )
================

ይህ ልባችን
እስከ ስሩ እስከ ጥጉ ቢበረበር
ኩራታችን የገደለው ስንት ፍቅር
ውስጡ ነበር ....

ህይወታችን
በቅን ዳኛ በጥቂቱ ቢመረመር
ማፈራችን ያሳለፈው ስንት ጸጋ
ገጥሞት ነበር ...

በትነነው ስናበቃ
የሰጠንን ቁና ሰፍሮ
አይከብድም ወይ
አምጣ እያሉ ዛሬም ለእግዜር እንጉርጉሮ ??


@gGetem
@gGetem
#የእንቢታሽ ሱሰኛ!
(ሚካኤል አስጨናቂ)

አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን  አንግቼ …

እንደ አሞራ ዙሬሽአንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’

አጃኢብ ነው መቼም!

ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ 
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራበእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀንልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞስብሰለስል ኖሬ

ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር 
ቃላት ድል ነስተውሽበኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜለታ 
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋትዝታሽ ተረታ።

(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )

@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍1
እንደምትወዳት ንገራት,

(በእውቀቱ ስዩም)
ሕይወት የብድር በሬ፥መቼ ሁሌ ይጠመዳል
ለጊዜው ብቻ የመጣ፥ ጊዜው ሲደርስ ይሄዳል
የተሰጠህ ጸጋ ሁሉ፥ ደሞ ካንተ ይወሰዳል::

ቀለበት፥ አምባር አይደሉም
እጅህ ላይ ሁልጊዜ የሉም
-ቀናት ሳምንታት ወራት
ዛሬውኑ ፥አሁኑኑ፥ እንደምትወዳት ንገራት::

አበቦች ሁሉ ሳይረግፉ
ምኡዝ ሽታዎች ሳይጠፉ
ያጸድ በሮች ሳይቆለፉ
በንቦች ጎዳና ላይ፥ተርቦች ሳይሰለፉ
በንፋስ ክንፍ ሳይመታ
ሕይወት የላምባ መብራት
አሁንኑ ዛሬውኑ ፥እንደምትወዳት ንገራት፤

ርቃ ሳትገሰግስ
ገና ስንቋን ስትደግስ
እንዲሁ እንዳማረባት
ቀልብህ እንደቀረባት
መቃብር በመዳፉ
እንደጠጠር ሳይቀልባት
አፈሩን ሳትዛመድ
ወደማትቀባው አመድ
ወደማትስበው አየር
ሳትቀየር
አንትም አንደበት ሳለህ፥ እሷም ጆሮ ሳያጥራት
ዛሬውኑ! አሁኑኑ! እንደምትወዳት ንገራት።

@gGetem
@gGetem
👌1
መናፈቅ ማለት …
ከወትሮው በድንገት
ከከተማ ግፊያ
ከሰፊው ገበያ
ከሰው ትርምስ
ከህይወት ግብስብስ
አረፍ ብለው ባልጋ
ከራስ ጋር ሲወጋ
የአስቴር እና ኤፍሬም
አባባይ ሙዚቃ ...
አንጀትንን ሲገርፍ
ትዝታን ሲያነቃ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት..
በቡሄ አመሻሽ
እርግት ባለ ሰማይ
ልጅነት ሲወያይ
ሲሸት የኩበት ጭስ
የአሪቲ ቃና መንደርን ሲዳብስ
ውብ አደይ አበባ ምድሪቷን ሲያነግስ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት ..
እኔና አንቺ አፍረን
ከዓይን ተሸሽገን
ከመስቀል ዳመራ
ሸሽተን ከጓደኞች
ፈልገን ሰዋራ ...
ተቃቅፈን እየሄድን
ውሎን ስንጋራ
ስትሰጪኝ ፖፖቲን
‘’ፖስት ካርዴስ ?’’ ብለሽ
ኪሴን ስትዳብሽኝ
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
ትምህርት ሊዘጋ ወቅት
ድራማ ተውነን
በሰኔ ሰላሳ  ለመታየት ደምቀን
በድራማው መኃል
ፈልገን ስህተት
ከልብ የሳቅን ዕለት
ከሳቅን በኋላ
ኩሪፊያ ሲከተለን ...
ድፍን ሶስት ወራትን
ያለመገናኘት ፍርሀት ሲውጠን
ስትሰናበችኝ  በጥልቁ ዝምታ
ዓይንሽን እያየሁ
ዓይኖቼን እያየሽ
የቆዘምን ለታ …..
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
የሽፍታ ፍርሀት
ነፍስያን ሳይንጣት
በ አራት እግር ጉዞ
የመኪናን መስኮት
በራስ ተመርኩዞ
የገጠርን መስመር
አንዱን መንገድ ይዞ
ተራራውን ማየት
እሸቱን መጎምዠት
ከገበሬ ቁና
በቆሎ መሸመት
የፀሀይዋን ግባት
አሻግሮ መቃኘት
እንዲህ ይመስለኛል።

መናፈቅ ማለት …

(ሚካኤል አ )


@gGetem
@gGetem
@gGetem
...ቃሌን
ውበት እረጋፊ  አላቂና አብቂ
ስስትን ማልሻ  አፍቃሪህ ናፍቂ
ገደብ የማላውቀው  እኔ ያንተ ጠባቂ
አርጅተን እስክንሔድ በሽበት ተከበን
ቃሌን አላጥፈውም አፈቅራለው አንተን
     

@gGetem
@gGetem
@gGetem
(እርቆ ለተኛ)

አትቀስቅሱት ከእንቅልፍ
አይውጣ ከእልፍኝ አይውረድ ከአልጋ
መሲሕ ካልሆነ
ወጀብ አይገስፅም መርከብ አያረጋ'
;
ተበላይ ተበላይ
ጧ! ብሎ የተኛ ስለምን ይፈራል
ሲቀርቡት ነው እንጂ
ርቆ ላየውማ ማዕበልኮ ያምራል።



@gGetem
@gGetem
.................ዮሐንስ✍️




ተይ አትከተይኝ
ላታስቆሚኝ መንገዴን አትዝጊው
ልቤ መች ፍቅር አዝሎ አሁን መተሽ ምፈልጊው

በቃ ሂጂ አልጠቅምሽም
ውስጤ ወና ድንጋይ ሆኗል የኔን ሀዘን አታብሺም

"ውዴ ሆዴ "አትበይኝ ውብ ቃላቶች አትምረጪ
ለፍቅራችን መለያ ስም አይጠቅምሽም ከቶ'አታውጪ
የልቤን ጉም ጥቁር ጭጋግ እንደ ፀሐይ መክፈት ካልቻሽ
የኔን ህመም በመታመም በኔ መዳን አንቺ ካልዳንሽ
ያንቺ ፍቅር ምን ሊጠቅመኝ ከቃል ውጪ ምን አትርፎ
እንደዚ አይነት የፍቅር ሂወት እስከዛሬስ መች ተፅፎ

አየሽ
ፍቅሬ ስትይኝ ዝም ያልኩሽ
ስትጠሪኝ ያልሰማውሽ

እንዳይመስልሽ ክፉ ሆኜ ከቶ አይደለም የጭካኔ
በኔ እምባ እንዳረጥቢነው የምገፊሽ ከጎኔ
በኔ ጥላ አንቺ ወድቀሽ በወንድ ልጅ ሳትጎጂ
ልብሽ ጠባሳ ሳያርፍበት እኔን ተይኝ አንቺ ሂጂ


@gGetem
@gGetem
💔1
አልሞትም!

(በእውቀቱ ስዩም)


ስሚ!
እኔ በዚህ ዐለም ፤ብዙ ብሰቃይም
አንድ ሀሙስ የቀረው፤ መስየ ብታይም
አምሮቴን ሳላገኝ፤ሱሴን ሳላከትም
በመሬት ከርስ ውስጥ ፤ገላየን አልከትም
አልሞትም!
ማንም ባልደፈረው፤ መንገድ ሳልገሰግስ
እንደ ንጉስ አይዙር፤ግማሽ ቀን ሳልነግስ
በጠገበው ሳልስቅ፤ ለራበው ሳልደግስ
አልሞትም!
ዝማሜን ሳላወልቅ፤ ያንድበቴን ግድብ
ዙፋን ላይ ሳልሸና፤ ጌቶቼን ሳልሰድብ
ከድሃ ሳላብር፤ ከገባር ሳልወግን
ከምድር በረከት፤ ድርሻየን ሳልዘግን
አልሞትም፤
ስሚ!
ልቤ እንደምኞቱ፤ ቢያገኝ እንደምርጫው
ያላማየ ማብቂያ፤ አንቺ ነሽ መቁዋጫው
እና
አገሬን ለቅቄ፤ ልብሽህ ላይ ሳልከትም
በውብ ከንፈርሽ ላይ፤ ከንፈሬን ሳላትም
አልሞትም!

@gGetem
@gGetem

        
ሢቃተ ሆሄ


   ጬኸት....
      ጬኸት
          ጬኸት
የሆሄያት ሲቃ
የሙሾ ድለቃ
ቃል ለዛውን ቢያጣ
ቅኔ ወዙ ቢነጣ
ሆሄያት ታመሙ
ሢቃ ድምጽ አሰሙ
       ያን ጊዜ
ገጣሚ ብእሩን ኣነሳ፤ከሆሄያት ድርድር
ከህመም ከሢቃ፤ስንኙን ሊያዋቅር
    ደራሲ ኣነባ
    የሆሄያት እንባ
ከወረቀቱ ላይ
ከነተበው ልቡ፤ከዘመኑ ሲሳይ
    ደራሲ ኣነባ
    የሆሄያት እንባ
ህይወቱን ሊገርፈው
በቅኔ ሊዘርፈው
ሆሄ ደረደረ
ቃላት ሰበጠረ
ሀረግ ኣዋቀረ
ሆሄያትም ታመሙ
ሢቃ ድምጽ ኣሰሙ
  ስንኙም ቤት መታ
  ግና የ ማታ ማታ
ሚስኪኑ ገጣሚ ቤት ለመታው ግጥሙ
በቆሰሉ ሆሄያት ህመም በሚያዜሙ
ፊደል ኣቀናብሮ በቃል በዘመነ
ቤት ለመታ ግጥሙ
ቤት መድፊያ እሱ ሆነ



@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍2
ሰላምን ፈለጋ
🦗🦗🦗🦗🦗🦗🦗
በሰወች መካከል ትልቅ ክፍተት መጣ
ትንሽ ተወድሶ ትልቅ ክብር አጣ
አገሬ ኢትዮጵያ ሰላም ላንች ይሁን
ፈቅር ይለግሰን ቸሩ አምላካችን
መሪና ተመሪ መገዱ ጠፍቷቸው
ተመሪ አወቀና መገድ ሊነግራቸው
መሪ አልሰማም አለ መች ተቀበላቸው
አተ መሪ ሁነህ ሰላምን ካሳጣህ
በምን ቀመር ሆኖ አተን ልከትልህ
የወድማችን ደም አተን እየጠጣህ
እናት ደስታን ስትል ሀዘን አሸክመህ
በልጆቿ ሀዘን እናት ደም አልቀሳ
በየትኛው መገድ ላተ እጅ ልሳ
አዉቃለው ታውቃለህ መገዱ መች ጠፋህ
አልገባኝም እኔ...
እናት መግደሉ ነው ?
እምነት ማጥፋቱ ነው?
ወይስ አገር መሸጥ..?
ነው ያተ ስልጣንህ?
አልገባኝም እኔ በምን ልጠይቅህ
ተምሪያለው ብለህ ማዕረግ ተሰጠሀል
እመራለው ብለህ ዳኝነት ይዘሀል
ግን እዴት መረሀው እስኪ ልጠይቅህ
ደምን እያፈሰስክ
እናት እያስለቅስክ
ሰላም ስጠን ሲሉህ ጀግናን እየረሸክ
ይህ ነው ሀላፊነት በምን ልጠይቅህ
ሰላምን ፍለጋ ቢመጣ ትልቁ ወድሜ
እረሽን እሚባል ትንሹ ወድሜ
በምን መልኩ ይሆን እርቁ የሚሆነው
ታናሽና ታላቅ እያጋደልክ ነው
ይህ ነዉ ወይ መሪነት?
እስኪ ልጠይቅህ
ተመሪነህ ብለህ አትናቀኝ እባክህ
ለህዝቤ ነጻነት መገዱን ልገርህ
ነፍጠኛነው ብለህ ወድም ከማሰረሸን
አዴ አድምጠኝና ሰላም ይሰፈንልን....

@gGetem
@gGetem
Audio
....አትፍረድ....
በሊዮ-ማክ
※※※※※ ሼር ያድርጉ!! ※※※※※
አዘጋጅ፦ண @gGetem
            ண @gGetem
═══════ ♢.✰.♢ ══════ @yosikeman
<
<< ሳስ ተው ልሽ >>>

...........................................ሴናዬ
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ...
ኤሊያስ የገጠመላት ያቺን እፁብ አስታወሺኝ
በቃል ብቻ የማውቃትን በእውን መተሽ አሳየሺኝ
ባላውቃትም ባላያትም ፍፁም በቁም  ባልኖራትም
ኤሊያስ ግን ያሰባትን ሳይከትባት አልተዋትም
...........................................
ሳስተውልሽ እንዳመልሽ ስበት መልክሽ ወሰወሰኝ
ላንቺ ሲገጥም አንቺን ሲሰኝ ባይኔ መጣ አስታወሰኝ
የኖራትን ያወቃትን አጣጥሞ መቼ ቀረ
ገጠመላት አዜመላት ስሜት ምቱን በብራናው አጠቆረ
...........................................
ደሞ ደሞ..
ሳስተውልሽ ዘውድ አክሊልን ትጠሪያለሽ
ሀያል ስሜት በልብ ላይ ትጭሪያለሽ
ልክ እንደርሱ ሙቀት ውበት እስካርፕም ነሽ
የርሱን ግጥም ትመስያለሽ
.........................................
ሳስተውልሽ ....
የኬቢሻን ጥልቅ ግጥም
እንደ በላይ በቀለ ወያ የምትጥም
እንደ ጋሽ ደበበ ቀለም የሰፋች
እንደ ኤፍሬም ስዩም የረጋች
እንደ  ጋሽ ፀጋዬ ፅሁፍ የጦፈች
በውበት ደምቃ ነብስ ያጠፋች
                              ያለማች
ሁሉም የገጠመላት ሁሉም ያነበነባት
በቃል ቅኔ ግጥም አርጎ የፈጠራት
.......................................
ኤላን የናፈቀችው
አስቱን ያሸፈተችው
ዘውድን የማረከችው
ኬቢን የታመነቺው
በላይን ያሳመመችው
   ጋሽ ደቤን የናፈቀችው
   ጋሽ ፀጋዬን የጠበቀችው
እርሷን ሴት ትመስያለሽ ጠቢቦች የተቀኙላት በደስታ በሂወት ፍሬ
በምኞት በእምባና ናፍቆት ሀያሎች የወደቁልሽ  መሰልሺኝ ተበታኝ ጥሬ
በሀሳብ ቅዠት ነበልባል ታውረው የሚከተሉሽ
ዝም ብዬ ሳስተውልሽ ላንቺ ነው የሚገጥሙልሽ !
አንቺን ነው መሰል የፃፉሽ.....

           

@gGetem
@gGetem
🥰1
ውሸት ነው በይኝ፡፡
እንደሰው ተወድጄ ተከበሬ የኖርኩበት ቀን ትዝ አይለኝም፡፡
ከሰው ጋር ራሴን አላወዳድርም አልልሽም፡፡
ካልተወዳርኩ ደስታዬ ሀዘኔ ከየት ይመነጫል፡፡ ከሰው አነስኩ ይሉ የለ እናቶች እንኳን፡፡ ከሰው እንዳላንስ ተመክሬ ተዘክሬ ነው ከእናቴ ቤት የተሞሸረኩት ለዓለም የተዳርኩት፡፡


ያለንፅፅር ወደድኩህ ስትይኝ የደነገጥኩት ለዛም ነው፡፡ በምን አቅምሽ ቻልሽው፡፡ አለማወዳደርን አለማነፃፀርን፡፡ ወይስ Ego የሚሉትን ጣጣ እንደገላሽ እጣቢ ደፋሽው?
:
:
ውሸት ነው በይኝ፡፡ እኔን እየነካሽ የሰማሽው ሙዚቃ ምንድነው?
ትዝታ?
ገና መቼ ኖሬና፡፡
አንቺሆዬ?
እኔ ሆዬ የደረጃ ምረኮኛ የፉክክር ባርያ ነኝ፡፡
አምባሰል?
መብሰልሰል መቁሰል ....በነገር መብሰል፡፡
ባቲ?
እንደሆንኩ ታውቂያለሽ መዋቲ፡፡
.
.
ታዲያ ምን ሰማሽ ታዲያ ምን ነካሽና ወድሀለሁ አልሽ፡፡
ተይ አታስክሪኝ፡፡ የኖርኩበትን የእሽቅድምድም ሕይወት ፉርሽ አታርጊብኝ፡፡
እያፎካከርሽ ውደጅኝ፡፡
እያወዳደርሽ አልምጅኝ፡፡


አፈቅርሻለሁ
ከሁሉም አስበልጬ
እናፍቅሻለሁ
ከሁሉም መርጬ
እጠራሻለሁ
አንቺን ብቻ ውጬ፡፡


ያለውድድር ያለንፅፅር መውደድም መወደድም ዓለም አይችልበትም፡፡
አንቺ እንዴት

@gGetem
@gGetem
👏1
..............


የተራቡ ነፍሶች፤ፍቅርን የተጠሙ
የደከሙ ጆሮ፤ልብን የሚሰሙ
የታረዙ ኣይኖች፤ከውበት የሸሹ
የጎደፈ ቆዳ፤በኑሮ የቆሸሹ
ደብዛዛ ኮከቦች፤ያደመቁት ሰማይ
ከዚህ ሁሉ መሀል፤ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ውበት ለራበው ዓይን
ሀሴት የምትመግብ
ፍቅር ለጠማው ጆሮ
የነፍስ ጥኡም ዜማ፤የህሊና ምግብ
ለጎደፈ ገላ፤የዘላለም ኣልባስ
ብርሀን እንደ ኮከብ፤ከጨለማው እራስ
     ብቻ ግን ቆንጆ ሴት
ከተመሳቀለ የህይወት ሸራ ላይ
ምንም ቢሸሽጓት፤ጎልታ የምትታይ
ብርሀን ያልሆነች፤ወይንም ጨለማ
ከሁሉም ለሁሉም፤ጋር የምትስማማ
ቆንጆ ሴት ኣማላይ
ጉድፍ ከበዛበት፤የኑሮ ሸራ ላይ
ኣልባስ ሆና ልትኖር
ከጎደፈ ገላው፤ከፈገግታው ሰማይ
.
..
ወደሱ ተጠጋች፤ወደ ግራ ጎኑ
ካለሷ ላለፈው፤ለባከነው ቀኑ
ዋስ እንኳ ባትሆን፤ለሀዘኑ ጠበቃ
ከእቅፋ እንዲደበቅ፤ኣቀፈችው ኣጥብቃ
ምን ኣይነት መክሊት ነው፤እንዴት ያለ ጸጋ
ህመሜ የሚፈወስ፤ከእቅፋ ስጠጋ
የምን ሀዘን ስቃይ
በፍቅር ልንሳፈፍ፤ከደመናው በላይ
ከኑሮ ሸራ ላይ
የምንመኘውን ስእል፤ስሎ ማየት
ከረሀብ
ከሀዘን
ከችግር መለየት
ምን ያለ ሀይል ነው፤እንጃ ግን ኣላቅም
ብቻ ግን እቅፋን፤ይዛለው ኣለቅም
ልክ እንደ ክርስቶስ
እንደ ሀዲስ ኪዳን
እንዴት መታደል ነው
በእቅፎቿ መዳን


      

@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍1
--------አልጋዬ--------

ሆድ ያባውን፣ ብቅል ያወጣዋል፣
እያሉ ፣ስንቱን ዘርጥጠዋል፣
ብሶት ንዴታቸውን፣ አውጥተዋል፣
የብቅሉ ትኩሳት፣ ነግቶ ሲያልፍላቸው፣
በሀፍረት አንገት፣ መድፋታቸው፣

እኔ ግን፣ እንዲ አልኩ
ምሳሌውን፣ ወደራሴ ቀየርኩ

ሆድ ያባውን፣ ዕንባ ያወጣዋል ብዬ
አነባለሁ ተሸሽጌ፣ ገብቼ ጓዳዬ
መከፋቴን ምታውቅ፣ የውስጤን ስብራት
ባዶነቴን ያየች፣ ብሶቴን ማወጋት
አልጋዬ ሚስጥረኛዬ፣ ጩኸቴን አድማጬ
በጣም እወድሻለሁ፣ ከሁሉ አብልጬ።

       
           


@gGetem
@gGetem
@gGetem
👍2
............


ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺኝ በመዳፍሽ
ፊደል አቁስሎኛል፤አትሸንግይኝ ባፍሽ
ነካኪው ገላዬን፤ያካሌን ጉዳንጉድ
ኣፌ ቃላት ይርሳ፤እንጩህ እንደጉድ
ዳሺኝ እና ልንቃ፤በድን ነው ህይወቴ
ኣዝምማ ከብዳለች፤የወረስኳት ቤቴ
ኣላወድስሽም በሽንገላ በቃላት
ሆድሽን ላያባባው፤ነፍሴን ላይደልላት
ሀጥያት ነው ቢሉንም፤ካህንና ቄሱ
ተይ ጽድቁን ለነሱ
ይልቅ ለኔና ኣንቺ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ዳሺው ኣካላቴን
የልቡን ኣያቅም፤ኣትስሚ ኣንድበቴን
ቃሉን እንጠየፍ፤ልናቀው ትዛዙን
በነገና ዛሬ ቀናት ፍቺ የገዙን
ሆነው እስከሚያዩት፤ደርሰው በኛ ቦታ
ሀጥያትን እንውደድ፤ሰው እንሁን ላፍታ
ልዳሰው ገላሽን፤ያካልሽን ጉዳንጉድ
ሳሚኝ እና ልዳን፤ልሳምሽ እንደጉድ
ፍቅር የጸነሰው፤ዝሙት እንደማይወልድ
ተዳሩ ቢሉ እንኳ፤መዳራት ለነሱ
በረከሰ ኣንድበት፤ስምሽን ለሚያረክሱ
ባይገባቸው እንጂ የመሳምሽ ምሱ
ጽድቁን ተይ ለነሱ


   

@gGetem
@gGetem
@gGetem
ልጠብቅሽ?!
ትመጫለሽ ብይ ቆማለው ከመንገድ
በአንቺ ተስፋ ቆርጭ አልሄድ
የፍቅራችንን ትላንት እያሰብኩኝ
በትላንትናችን ነጋችንን እያለምኩኝ
ግን አንቺ ጥለሽኝ ሄድሽ
እጠብቅሻለው እያልኩኝ ትመጫለሽ
እዛው ነኝ ጥለሽኝ የሄድሽበት ቦታ
አለ ልቤ በፍቅርሽ እደተረታ
ትመጫለሽ እያልኩኝ ከዛሬ ነገ
እደምትመለሽ ልቤ ተስፍ እያደረገ 
እዛው ነኝ የቆምንበት ቦታ
ልቤ አንቺንስ በማንም አይተካ
ብያደክመኝም መቆሙ ከመንገድ
ብሉኝም ሄዳለች አንተ ሄድ
እጠብቅሻለው እዛው ቦታ ላይ ሁኝ
እደምትመለሽ መንገዱን አምኝ

    

@gGetem
@gGetem
@gGetem
.......


ተናነስን
ከል ለበስን
ለፍቅርን ብለን
ምኞትን ተከትለን
በደረቅ ቁስል  ነተብን
ነፍሳችን  ከሌላ ነፍስ አተብን
በዕንባ ነጠብጣብ ሆሄያት ከተብን
ፍቅር ሆኖ ጭብጡ  መውደድ ነበር ቅሉ
ሰከርን በድግሱ ጥንስሱ   ማጣት ሆኖ ብቅሉ



@gGetem
@gGetem
@gGetem
ትወደኝና ዋ!

እልህ ነው የያዘኝ ያለመገኘትህ
እኔ አንተን ስልህ ሌላውን ማለትህ
ስትገኝ አይደለም ሳጣህ ነው ምወድህ

ሁሉ ሲፈልገኝ ስላልፈለከኝ ነው
በፍቅር እንዳይመስልህ እንደዚህ ምሆነው
እልህ ነው!
አደራህን ውዴ ከወደድከኝ ጠላሃለው
ከፈለከኝ ርቅሃለው
አውቀዋለው እኔ አመሌን
ሲፈልጉኝ መጀነኔን
ፍቅር እንዳይመስልህ እንዲህ ሚያደርገኝ
እልህ ነው ካለህበት ሁሉ ሚያሽከረክረኝ
ልንገርህ አንተ ሰው ከቶ እንዳትወደኝ
እኔ አመል አለብኝ
ስለዚህ አደራ ወደህ አታስጠላኝ!


@gGetem
@gGetem
👍2
ተቁነጥንጣ ቀረበችኝ
ተቻኮለች እንዳፈቅራት ፣
ተጨነቀች ወዲያው ደሞ
ተቻኩየ ስላቀፍኳት ፣

ትፈጥናለች ለማግኜት
ልቤን አርጋው የቀበሌ  ፣
ታምር አርጋ ቆጠረችው
በእሷ ፍቅር መቸኮሌ ፣

መቸኮልን አስለምዳኝ
ተጣድፎ ዝግታየን
አቻኩላ አገባችኝ
እይ ስትል እድሜየን ፣


ተቻኩላ አስለምዳኝ
ረጋ ያለ አረማመድ  ፣
ተቻኩየ ጥያት ሄድኩኝ
ቀድማ ከእኔ እንዳትራመድ

@gGetem
@gGetem
@gGetem
2025/07/14 08:38:26
Back to Top
HTML Embed Code: