ጠጥቻለሁ ... መራር ኃጥያት
በልቻለሁ ... እርጉም ክፋት
ወጥቻለሁ ... ከሰው ተራ
ተስያለሁ ... እንደ ካራ
ማረድ ... የጽድቅ አንገት
መቁረጥ ... የጾም አንጀት
መበጠስ ... የጸሎት ክር
መጉረድ ... የምጽዋት ስር
ግብሬ ሆኖ የተጣባኝ
የቁም ሞትን መኖር ቀባኝ
ድንግል ማርያም የለሁም በእውነት
ካንች ተለይቶ መች አለ ህይወት
አጥቢኝ የጾም ወተት ኃጥያትን ማርከሻ
ልጉረስ ከ'ጅሽ ፍቅር ክፋት መደምሰሻ
እናቴ እያልኩኝ ልጥራሽ እንደ ሰው
ውለጅኝ በምልጃሽ ሞቴን ልደምስሰው
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
በልቻለሁ ... እርጉም ክፋት
ወጥቻለሁ ... ከሰው ተራ
ተስያለሁ ... እንደ ካራ
ማረድ ... የጽድቅ አንገት
መቁረጥ ... የጾም አንጀት
መበጠስ ... የጸሎት ክር
መጉረድ ... የምጽዋት ስር
ግብሬ ሆኖ የተጣባኝ
የቁም ሞትን መኖር ቀባኝ
ድንግል ማርያም የለሁም በእውነት
ካንች ተለይቶ መች አለ ህይወት
አጥቢኝ የጾም ወተት ኃጥያትን ማርከሻ
ልጉረስ ከ'ጅሽ ፍቅር ክፋት መደምሰሻ
እናቴ እያልኩኝ ልጥራሽ እንደ ሰው
ውለጅኝ በምልጃሽ ሞቴን ልደምስሰው
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
ምሽት በረንዳ ላይ
(በእውቀቱ ስዩም)
አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ
በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤
“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”
እያልሁ አስባለሁ፥
ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ
በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤
በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::
@getem
@getem
@getem
(በእውቀቱ ስዩም)
አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ
በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤
“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”
እያልሁ አስባለሁ፥
ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ
በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤
በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::
@getem
@getem
@getem
[የጅራፍ ጠበቃ]
_
እነ ተረት አዋቂ ...
(እነ ጸጉር ሰንጣቂ....)
«ጅራፍ እራሱ ገርፎ ፥ እራሱ ይጮኻል»
(ይሉሃል....፤)
እንዲህ ሲነግሩህ — ምን ይሰማኻል?
አይተህ አይደል ወይ....!?
(ምስኪኑን ጅራፍ....)
ቁልቁል ከመሬት እያላተመው
— እረኛው ጠልፎ ፤
እንዴት ይባላል...!?
«እራሱ ጮኸ — እራሱ ገርፎ » ?
²
(ጅራፉ ጥፋት የለበት....)
ሀሰት ነው —·· ውንጀላ ክሱ ፤
(ገራፊ ካልሰነዘረው....)
መች ያውቃል —·· ገርፎ በራሱ!?
³
ሳትፈቅድ ተገፈህ
(ሳትወድ ተጠልፈህ...)
"ጅራፍ ሁነኝ" መባል....
(ለዱላ መታጨት....፤)
መግረፍ ነው? – መጋጨት?
⁴
(ግርፊያ በሚል ሰበብ..)
ጎርባጣ ጀርባ ላይ— ሄዶ በማረፉ ፤
ከበሬው ገላ እኩል — ያመዋል ጅራፉ ።
(ቢጮኽ አልፈርድበት......)
___
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
_
እነ ተረት አዋቂ ...
(እነ ጸጉር ሰንጣቂ....)
«ጅራፍ እራሱ ገርፎ ፥ እራሱ ይጮኻል»
(ይሉሃል....፤)
እንዲህ ሲነግሩህ — ምን ይሰማኻል?
አይተህ አይደል ወይ....!?
(ምስኪኑን ጅራፍ....)
ቁልቁል ከመሬት እያላተመው
— እረኛው ጠልፎ ፤
እንዴት ይባላል...!?
«እራሱ ጮኸ — እራሱ ገርፎ » ?
²
(ጅራፉ ጥፋት የለበት....)
ሀሰት ነው —·· ውንጀላ ክሱ ፤
(ገራፊ ካልሰነዘረው....)
መች ያውቃል —·· ገርፎ በራሱ!?
³
ሳትፈቅድ ተገፈህ
(ሳትወድ ተጠልፈህ...)
"ጅራፍ ሁነኝ" መባል....
(ለዱላ መታጨት....፤)
መግረፍ ነው? – መጋጨት?
⁴
(ግርፊያ በሚል ሰበብ..)
ጎርባጣ ጀርባ ላይ— ሄዶ በማረፉ ፤
ከበሬው ገላ እኩል — ያመዋል ጅራፉ ።
(ቢጮኽ አልፈርድበት......)
___
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
እስኪ ምን ላርግልሽ
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
[ለሻማ ሕይወቶች....]
🕯️
፩.
ሻማዬ ...ሞቆሻል አይደል?!
ላብሽ — ይንጠፈጠፋል ፤
እንዳላበርድሽ (ጨነቀኝ)
የቤቴ ብርሃን — ይጠፋል ።
["ይነጋል" ግን — አልልሽም...
አጉል ተስፋን— አልሰጥሽም ።]
አውቃለሁ በደጄ በራፍ·· —
የጠዋት ጮራ ይሰለፋል ፤
ያኔ ግን ከጨለማው ጋር —
ሕይወትሽም አብሮ ያልፋል ።
🕯️
፪.
(አንተም አንተም የኔ ወዳጅ....)
የሠው ልጅም በጨለማ....
ቢለኮስ – ቢቀልጥ – ቢቃጠል ፤
(እንባ ላቡ ቢንጠለጠል...)
"ይነጋል " አትበለው — እረፍ !
(ጀንበር 'በራሁ' — እስክትል...)
ማለቁ አይቀርም ሲሸረፍ ።
[ሰም ለበስ ነውና — ሠውም እንደ ሻማ እስከ ንጋት ድረስ — ያልቃል በጨለማ ።]
ከቻልክ "እፍ" በለው....
`ሳቱን አብርድለት ፤
ላንተ ብርሃን ተብሎ...
— ማለቅ አይወድለት ።
🕯️|
___
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
🕯️
፩.
ሻማዬ ...ሞቆሻል አይደል?!
ላብሽ — ይንጠፈጠፋል ፤
እንዳላበርድሽ (ጨነቀኝ)
የቤቴ ብርሃን — ይጠፋል ።
["ይነጋል" ግን — አልልሽም...
አጉል ተስፋን— አልሰጥሽም ።]
አውቃለሁ በደጄ በራፍ·· —
የጠዋት ጮራ ይሰለፋል ፤
ያኔ ግን ከጨለማው ጋር —
ሕይወትሽም አብሮ ያልፋል ።
🕯️
፪.
(አንተም አንተም የኔ ወዳጅ....)
የሠው ልጅም በጨለማ....
ቢለኮስ – ቢቀልጥ – ቢቃጠል ፤
(እንባ ላቡ ቢንጠለጠል...)
"ይነጋል " አትበለው — እረፍ !
(ጀንበር 'በራሁ' — እስክትል...)
ማለቁ አይቀርም ሲሸረፍ ።
[ሰም ለበስ ነውና — ሠውም እንደ ሻማ እስከ ንጋት ድረስ — ያልቃል በጨለማ ።]
ከቻልክ "እፍ" በለው....
`ሳቱን አብርድለት ፤
ላንተ ብርሃን ተብሎ...
— ማለቅ አይወድለት ።
🕯️|
___
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ጠብም
አምላክ ሊታረቀ
ባንቺ ሊባርከኝ
ሊያመጣሽ ነው መሰል
ሰማዩ ዳመነ
ጨለማው ገነነ
ልክ አንደረተቱ
አይቀርም መንጋቱ
ቀኑ ሲጨላለልም
ብርሀን ሲጠልም
ሰማይ ሲደማምን
አላህን ልለምን
በስግደት በዱዓ
በፆም በጁምዓ
መሬት ተንበረከኩ
እናም አንቺን ለመንኩ
ለመንኩት ለመንኩት
ባንቺ አከበርኩት
አንቺን እንድሰጠኝ
አንድ አንቺን እንዲመፀወተኝ
ተረቱስ ተለለ
ጠብም ያለ የለ
ደመናው ለዝናብ
ጨለማው ለብርሀን
ቦታውን ለቀቀ
ተረቱም አለቀ
መስገዴ በከንቱ
ጠብም ያለ የለ
ካላህ በማውራቱ
አላህም እንዳንቺ
አላህም አንደሰው
ጨካኝነት ባሰው
ጨለማን ሲያነግስ ጭካኔ
በግርማሽ ሲፈራረስ ወኔ
እኔም ጠፋሁ ከኔ ።
by kerim
@getem
@getem
@getem
አምላክ ሊታረቀ
ባንቺ ሊባርከኝ
ሊያመጣሽ ነው መሰል
ሰማዩ ዳመነ
ጨለማው ገነነ
ልክ አንደረተቱ
አይቀርም መንጋቱ
ቀኑ ሲጨላለልም
ብርሀን ሲጠልም
ሰማይ ሲደማምን
አላህን ልለምን
በስግደት በዱዓ
በፆም በጁምዓ
መሬት ተንበረከኩ
እናም አንቺን ለመንኩ
ለመንኩት ለመንኩት
ባንቺ አከበርኩት
አንቺን እንድሰጠኝ
አንድ አንቺን እንዲመፀወተኝ
ተረቱስ ተለለ
ጠብም ያለ የለ
ደመናው ለዝናብ
ጨለማው ለብርሀን
ቦታውን ለቀቀ
ተረቱም አለቀ
መስገዴ በከንቱ
ጠብም ያለ የለ
ካላህ በማውራቱ
አላህም እንዳንቺ
አላህም አንደሰው
ጨካኝነት ባሰው
ጨለማን ሲያነግስ ጭካኔ
በግርማሽ ሲፈራረስ ወኔ
እኔም ጠፋሁ ከኔ ።
by kerim
@getem
@getem
@getem
እስኪ ምን ላርግልሽ
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
ካንቺ የተፀናወተኝ ማፍቀሬ እንዲገባሽ
ከአይኖችሽ የያዘኝ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ የኔ ዓለም እስኪ ምን ላርግልሽ
ከምድር እስከ ሰማይ ወጥቼ ወርጄ ስልጣን ተበድሬ
በዓለም ሚኖሩትን ሕዝቡን ሚገዙትን ነገስታትን ሽሬ
ለዘውድሽ እንድትሆን ከሰማየ ሰማይ ፀሐይን አውርጄ
ግርማሽ እንዲያስፈራ መጎናፀፍያሽን በእሳት ጋርጄ
ከሰው ሁሉ እንድትልቂ ተከብረሽ ተነግሰሽ
ዉበትሽ እንዲታይ እንዲጎላ መልክሽ
ጨረቃን አውርጄ ልሰራት ካንገትሽ
ኮከብ አዋቅሬ ልብስሽን ልስራልሽ
ከእሳት እና ከዉሃ ዙፋን ልገንባልሽ
ስምሽ እንዳይረሳ ዓለም እንዲያስታውስ ትውልድ ሁሉ እንዲያውቀው
ቃላት እየመረጥኩ ግጥም እየፃፍኩኝ መልክሽ ልሳለው
ማፍቀሬ እንዲገባሽ መውደዴ እንዲታይሽ
ንገሪኝ ፍቅሬ ሆይ እስኪ ምን ላርግልሽ ?
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
አህያ
ጀርባው ይዞ ትልቅ ጭነት
አንገት ደፍቶ ሁሉ ሰው ፊት
አገልግሎት እንዳልሰጠ
በውጭ ገንዘብ ተለወጠ።
አንገቱ ላይ አርፎ ቢላ
ለእርድ ቀርቧል ነው እንዲበላ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
ጀርባው ይዞ ትልቅ ጭነት
አንገት ደፍቶ ሁሉ ሰው ፊት
አገልግሎት እንዳልሰጠ
በውጭ ገንዘብ ተለወጠ።
አንገቱ ላይ አርፎ ቢላ
ለእርድ ቀርቧል ነው እንዲበላ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
🤔
.
.
ግራ መጋባቴ እንደዉ ግራ ገብቶኝ፤
ስቋጥር ስፈታ እጅጉን አሳስቦኝ፤
ባስብ ባሰላስል ከልቤ አጣሀት፤
ግራ የገባኝን ግራ ገብቶኝ ተዉኩት።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ግራ መጋባቴ እንደዉ ግራ ገብቶኝ፤
ስቋጥር ስፈታ እጅጉን አሳስቦኝ፤
ባስብ ባሰላስል ከልቤ አጣሀት፤
ግራ የገባኝን ግራ ገብቶኝ ተዉኩት።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem