HUSSEYN_Y_ABDERY_WEDAJ Telegram 4007
[ስሟ መስጅድ ላይ የተፃፈው የአሮጊት ሴትዮ ታሪክ]

በድሮ ጊዜ ከነግስታት መካከል አንድ ንጉስ በከተማው ላይ መስጂድ ለመስራት ፈልጎ  በዚህም መስጅድ ስራ በገንዘብም ሆነ በሌላ ነገር ማንም ሰው እንዳይሳተፍ አዘዘ።

በእርግጥም ንጉሱ በፈለገው መልኩ ያለምንም የሌላላ ሰው እገዛ የመስጅዱ ግንባታ ተጠናቆ በበሩ ላይም ስሙ እንዲፃፍ አዘዘ።

አንድ ቀን ሌሊት ንጉሱ በህልሙ ከሰማይ መላኢካ ወርዶ የሱን ስም ከመስጂዱ ደጃፍ ላይ ሰርዞ በስፍራው ላይም የሴት ስም ሲጽፍ ተመለከተ።

ታዲያ ንጉሱ ከእንቅልፉ በፍርሐት በመንቃት በመስጂዱ በር ላይ ስሙ መኖሩን  ለማረጋገጥ ወታደሮቹን ላከ፤ ወታደሮቹ ተመልሰው ስሙ  እንዳለ ነገሩት።

በሁለተኛው ሌሊት ንጉሱ ያንኑ ህልም አይቶ ከእንቅልፉ በተነሳ ጊዜ ስሙ  መኖሩን ለማረጋገጥ ወታደሮቹን ለሁለተኛ ጊዜ ላካቸው፤  እነርሱም ሄደው ተመልሰው  ስሙ እንዳለ ነገሩት፤ ንጉሡም በጣም ተገረመ።

በሦስተኛው ሌሊትም ያንኑ ህልም ተደጋገመበት..... ንጉሡ  ከእንቅልፉ በነቃ በሕልሙ መስጅዱ ላይ ስሟ የተጻፈላትን ሴትዮ ሥሟን ሸምድዶ ስለ ነበር ወታደሮቹ እሷን ፈልገው ወደሱ እንዲያመጧት አዘዘ።

ወታደሮቹም እስኪያገኟት ድረስ ተበታተነው  ፈልገው  ወደ ንጉሡም አቀረቧት ፤ ሴትዮዋ ሚስኪን አሮጊት ነበረች፤ ወደ ንጉሱ ስትቀርብ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች።

በመቀጠልም ንጉሱም «እኔ በሰራሁት መስጅድ ላይ ረድተሻል?» በማለት ጠየቃት። እሷም፡- «ንጉሥ ሆይ! እኔ ምስኪን አሮጊት ነኝ፣ በምትሰራው መስጅድ ላይ  ማንም በምንም ነገር  እንዳይረዳህ ስትከለክል ሰምቻለሁ» አለች።

እሱም፦ «በአሏህ እጠይቅሻለሁ ይህን መስጅድ ለመስራት ምን አስተዋፅኦ አድርገሻል?» አላት።

እሷም፦«ከዕለታት አንድ ቀን በመስጅዱ ጎን ሳልፍ ለመስጅ ስራ የሚውል እንጨትና የግንባታ መሳሪያ የተሸከመች እንስሳ ውሃ ተጠምታ ተመለከትኩ፤ የታሰረችበት ገመድ አጭር በመሆኑ ምክንያት በአቀራቢያዋ ከነበረ የውሃ ባልዲ  ደርሳ መጠጣት  አልቻለችም። በዚህ ሰኣት ለአሏህ ብዬ ውሃው ወደሷ አስጠግቸላት እስክትጠግ ጠጥታ ከሞት ተረፈች፤ እኔ ያደረኩት ይህ ብቻ ነው አለች።

ንጉሱም በመገረም «ሱብሐን አሏህ! አንቺ ለአሏህ ብለሽ በመስራት ተቀባይነት አገኘሽ፣ እኔ ግን  የሰራሁት የንጉሱ መስጊድ ተብሎ እንዲጠራ ስለነበር አሏህም ሳይቀበለው ቀረ»አለ።

በመቀጠልም ንጉሱ ተውባ አደረገ፤ የአሮጊቷ ስምም በመስጅዱ በር ላይ እንዲፃፍ ካደረገ በኃላ እስከ መጨረሻው እድሜዋ በድሎት ምትኖርበትን ገንዘብ ሰጦ ሸኛት።

<ማንኛውም መልካም ስራ ከአሏህ ዘንድ ተቀባይነት ሚያገኘው በኒያ ልክ ነው>

አሏህ መልካም ስራቸው ለሱ  ከሆኑ ባሮች ያድርገን!

:¨·.·¨: ❀
 `·. ሑሰይን የዐብደሪይ ወዳጅ
T.me/husseyn_y_abdery_wedaj



tgoop.com/husseyn_y_abdery_wedaj/4007
Create:
Last Update:

[ስሟ መስጅድ ላይ የተፃፈው የአሮጊት ሴትዮ ታሪክ]

በድሮ ጊዜ ከነግስታት መካከል አንድ ንጉስ በከተማው ላይ መስጂድ ለመስራት ፈልጎ  በዚህም መስጅድ ስራ በገንዘብም ሆነ በሌላ ነገር ማንም ሰው እንዳይሳተፍ አዘዘ።

በእርግጥም ንጉሱ በፈለገው መልኩ ያለምንም የሌላላ ሰው እገዛ የመስጅዱ ግንባታ ተጠናቆ በበሩ ላይም ስሙ እንዲፃፍ አዘዘ።

አንድ ቀን ሌሊት ንጉሱ በህልሙ ከሰማይ መላኢካ ወርዶ የሱን ስም ከመስጂዱ ደጃፍ ላይ ሰርዞ በስፍራው ላይም የሴት ስም ሲጽፍ ተመለከተ።

ታዲያ ንጉሱ ከእንቅልፉ በፍርሐት በመንቃት በመስጂዱ በር ላይ ስሙ መኖሩን  ለማረጋገጥ ወታደሮቹን ላከ፤ ወታደሮቹ ተመልሰው ስሙ  እንዳለ ነገሩት።

በሁለተኛው ሌሊት ንጉሱ ያንኑ ህልም አይቶ ከእንቅልፉ በተነሳ ጊዜ ስሙ  መኖሩን ለማረጋገጥ ወታደሮቹን ለሁለተኛ ጊዜ ላካቸው፤  እነርሱም ሄደው ተመልሰው  ስሙ እንዳለ ነገሩት፤ ንጉሡም በጣም ተገረመ።

በሦስተኛው ሌሊትም ያንኑ ህልም ተደጋገመበት..... ንጉሡ  ከእንቅልፉ በነቃ በሕልሙ መስጅዱ ላይ ስሟ የተጻፈላትን ሴትዮ ሥሟን ሸምድዶ ስለ ነበር ወታደሮቹ እሷን ፈልገው ወደሱ እንዲያመጧት አዘዘ።

ወታደሮቹም እስኪያገኟት ድረስ ተበታተነው  ፈልገው  ወደ ንጉሡም አቀረቧት ፤ ሴትዮዋ ሚስኪን አሮጊት ነበረች፤ ወደ ንጉሱ ስትቀርብ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች።

በመቀጠልም ንጉሱም «እኔ በሰራሁት መስጅድ ላይ ረድተሻል?» በማለት ጠየቃት። እሷም፡- «ንጉሥ ሆይ! እኔ ምስኪን አሮጊት ነኝ፣ በምትሰራው መስጅድ ላይ  ማንም በምንም ነገር  እንዳይረዳህ ስትከለክል ሰምቻለሁ» አለች።

እሱም፦ «በአሏህ እጠይቅሻለሁ ይህን መስጅድ ለመስራት ምን አስተዋፅኦ አድርገሻል?» አላት።

እሷም፦«ከዕለታት አንድ ቀን በመስጅዱ ጎን ሳልፍ ለመስጅ ስራ የሚውል እንጨትና የግንባታ መሳሪያ የተሸከመች እንስሳ ውሃ ተጠምታ ተመለከትኩ፤ የታሰረችበት ገመድ አጭር በመሆኑ ምክንያት በአቀራቢያዋ ከነበረ የውሃ ባልዲ  ደርሳ መጠጣት  አልቻለችም። በዚህ ሰኣት ለአሏህ ብዬ ውሃው ወደሷ አስጠግቸላት እስክትጠግ ጠጥታ ከሞት ተረፈች፤ እኔ ያደረኩት ይህ ብቻ ነው አለች።

ንጉሱም በመገረም «ሱብሐን አሏህ! አንቺ ለአሏህ ብለሽ በመስራት ተቀባይነት አገኘሽ፣ እኔ ግን  የሰራሁት የንጉሱ መስጊድ ተብሎ እንዲጠራ ስለነበር አሏህም ሳይቀበለው ቀረ»አለ።

በመቀጠልም ንጉሱ ተውባ አደረገ፤ የአሮጊቷ ስምም በመስጅዱ በር ላይ እንዲፃፍ ካደረገ በኃላ እስከ መጨረሻው እድሜዋ በድሎት ምትኖርበትን ገንዘብ ሰጦ ሸኛት።

<ማንኛውም መልካም ስራ ከአሏህ ዘንድ ተቀባይነት ሚያገኘው በኒያ ልክ ነው>

አሏህ መልካም ስራቸው ለሱ  ከሆኑ ባሮች ያድርገን!

:¨·.·¨: ❀
 `·. ሑሰይን የዐብደሪይ ወዳጅ
T.me/husseyn_y_abdery_wedaj

BY ሑሰይን የዐብደሪይ ወዳጅ - official


Share with your friend now:
tgoop.com/husseyn_y_abdery_wedaj/4007

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) 5Telegram Channel avatar size/dimensions The group also hosted discussions on committing arson, Judge Hui said, including setting roadblocks on fire, hurling petrol bombs at police stations and teaching people to make such weapons. The conversation linked to arson went on for two to three months, Hui said. ZDNET RECOMMENDS To upload a logo, click the Menu icon and select “Manage Channel.” In a new window, hit the Camera icon.
from us


Telegram ሑሰይን የዐብደሪይ ወዳጅ - official
FROM American