Telegram Web
(የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 15)
----------
17፤ ቀይ ልብስም አለበሱት፥ የእሾህ አክሊልም ጎንጉነው ደፉበት፤

18፤ የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ እጅ ይነሱት ጀመር፤

19፤ ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት።

20፤ ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት፥ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።

21፤ አንድ መንገድ አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።

22፤ ትርጓሜውም የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደተባለ ስፍራ ወሰዱት።

@linkortodoxe21
እንካን አደረሳችሁ 😍😍😍
@linkortodoxe21
"ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤አሰሮ ለሰይጣን፤አግዐዞ ለአዳም፤ሠላም እምዕይዜሰ፤ኮነ ፍስሐ ወሠላም።

'ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሣ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍጽም ሰላምና ደስታ ሆነ'

" እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም"
(የማቴዎስ ወንጌል 28:6)

😊እንካን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ😊
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
"እሳትን በእሳት ማጥፋት ይቻላልን??
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
" ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ #የመውጊያውን ብረት #ብትቃወም #ለአንተ #ይብስብሃል #አለው።"
(የሐዋርያት ሥራ 9:5)

@Ortodoxe19
(መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 13)
----------
1፤ አቤቱ፥ እስከ መቼ ፈጽመህ ትረሳኛለህ? እስከ መቼስ ፊትህን ከእኔ ትሰውራለህ?

2፤ እስከ መቼ በነፍሴ እመካከራለሁ? ትካዜስ እስከ መቼ ሁልጊዜ ይሆናል? እስከ መቼ ጠላቴ በላዬ ይጓደዳል?

3፤ አቤቱ አምላኬ፥ እየኝ ስማኝም፤ ጠላቴ። አሸነፍሁት እንዳይል፥

4፤ የሚያስጨንቁኝም እኔ ብናወጥ ደስ እንዳይላቸው፥ ለሞትም እንዳልተኛ ዓይኖቼን አብራ።

5፤ እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ፥ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል።

6፤ የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ።

👉 @linkortodoxe21
Channel name was changed to «መንፈሳዊ ህይወት»
😍እንካን አደረሳችሁ 😍
ግንቦት 21
እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ የታየችበት ቀን በእኛም ህይወት ትታይልን ከክፍ ነገር ሁሉ ትሰውረን

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
⚪️በዓለ ጰራቅሊጦስ⚪️
መንፈስቅዱስ የወረደበት ቀን እንካን አደረሳችሁ /አደረሰን
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@liniortodoxe21
#የቆሎ_ተማሪ_ዘድንግል


በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15

ግጥም፦ዘኪ

🔸 @linkortodoxe21
🔸 @linkortodoxe21
🔸 @linkortodoxe21
ሰው ሆይ! የሚጎዳህ ሀብትህ አይደለም፤ ድኽነትህም አይደለም። ሰውን የሚጎዳው ክፉ ልብ ነው። ክፉ ልብ ደግሞ በሀብትም፣ ሀብት በማጣትም የሚመጣ አይደለም። ክፉ ልብ ሌሎች ክፉ ልቦችን ይወልዳል። እሳት እሳትን እየወለደ ብዙ እንጨቶችን እንደሚበላ ኹሉ ክፉ ልብም እንደዚህ ነው።

አንተ ሰው! ይህን ማወቅ ትወዳለህን? ክፉ ምግባር ወ ይም በጎ ምግባር በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። እነዚህ ኹለቱ ከክፉ ልብ ወይም ከመልካም ልብ የሚገኙ ናቸው።

© ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ አምስቱ የንስሓ መንገዶች፥ ገ. 9

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
🔸እንካን አደረሳችሁ

እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች
አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤
(ትንቢተ ዳንኤል 10:13)

#join or #share
🔹 @Ortodoxe19
🔹 @Ortodoxe19
🔹 @Ortodoxe19
😊እንካን አደረሳችሁ በዛሬ ቀን ቤተክርስቲያናችን በደንብ የምታከብራቸው በዓላት መካከል ይህ አንድ ነው።
ዛሬ ጾም የሚፈሰክበት የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓል በተለየ ሁኔታ የቅዱስ ጳውሎስ ወጴጥሮስ የተሰውበት ቀን ነች እና እንካን አደረሳችሁ አደረሰን

@linkortodoxe21
ውድ ክርስቲያኖች እንኳን አደረሳችሁ
#ሐዋርያነት
ሐምሌ ፭ ቀን ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የተቀበሉበት መታሰቢያ ዕለት ነው። ሐዋርያነት እስከ ሞት ድረስ እውነትን መናገር ነው። ሐዋርያነት ንጉሡ ኔሮንን እንዳይከፋው ተብሎ እውነትን ባለመናገር መተባበር አይደለም። መከራን፣ሞትን ሳይሰቀቁ እውነትን በአደባባይ መናገር ነው። ሐዋርያነት ፍቅርን ትእግስትን፣ ትሕትናን መሠረት አድርጎ እውነትን በአደባባይ መመስከር ነው። እውነትን መናገር ብቻ ሳይሆን ውሸትንም በአደባባይ መቃወም ነው።
።።
ሐዋርያነት ሁሉን ትቶ መከተል ነው። ራሱ ቅዱስ ጴጥሮስ ኀደግነ ኵሎ ወተሎናከ ሁሉን ትተን ተከተልንህ ምንተ እንከ ንረክብ እንግዲህ ምን እናገኛለን ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጠይቆት ነበረ። ቅዱስ ጴጥሮስ ምን ትቶ ተከትሎታል ቢሉ አንድ አህያ ነበረችው እርሷን ትቶ ተከትሎታል። ከምንም በላይ ግን "እከብር ባይ ልቡናን" ትቶ ተከትሎታል ብለው መተርጉማን ይናገራሉ። ሐዋርያ የእግዚአብሔርን ቃል በደስታ የሚናገር ነው። እውነትን በአደባባይ የሚመሰክር ነው። ይህን በማድረጉ ሰዎች ሲጠሉት ሲሰድቡት እና መከራን ሲያደርሱበት በደስታ የሚቀበል ነው።
።።
ሐዋርያ ለክብረ ቤተክርስቲያን የሚኖር፣ ፈጣሪውን የሚፈራ፣ በሰው መወደድን እና መከበርን የሚጠላ፣ ክብርን ሁሉ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ፣ ሁሉን እንደራሱ የሚወድ ፍቅር ያለው፣ ለራሱ ድኅነት እና ለሰዎች መዳን የሚተጋ ነው።

የቅዱሳኑ ሐዋርያት በረከት ይደርብን።

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
1
2025/07/14 18:29:26
Back to Top
HTML Embed Code: