Telegram Web
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
"እሳትን በእሳት ማጥፋት ይቻላልን??
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
" ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ #የመውጊያውን ብረት #ብትቃወም #ለአንተ #ይብስብሃል #አለው።"
(የሐዋርያት ሥራ 9:5)

@Ortodoxe19
(መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 13)
----------
1፤ አቤቱ፥ እስከ መቼ ፈጽመህ ትረሳኛለህ? እስከ መቼስ ፊትህን ከእኔ ትሰውራለህ?

2፤ እስከ መቼ በነፍሴ እመካከራለሁ? ትካዜስ እስከ መቼ ሁልጊዜ ይሆናል? እስከ መቼ ጠላቴ በላዬ ይጓደዳል?

3፤ አቤቱ አምላኬ፥ እየኝ ስማኝም፤ ጠላቴ። አሸነፍሁት እንዳይል፥

4፤ የሚያስጨንቁኝም እኔ ብናወጥ ደስ እንዳይላቸው፥ ለሞትም እንዳልተኛ ዓይኖቼን አብራ።

5፤ እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ፥ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል።

6፤ የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ።

👉 @linkortodoxe21
Channel name was changed to «መንፈሳዊ ህይወት»
😍እንካን አደረሳችሁ 😍
ግንቦት 21
እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ የታየችበት ቀን በእኛም ህይወት ትታይልን ከክፍ ነገር ሁሉ ትሰውረን

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
⚪️በዓለ ጰራቅሊጦስ⚪️
መንፈስቅዱስ የወረደበት ቀን እንካን አደረሳችሁ /አደረሰን
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@liniortodoxe21
#የቆሎ_ተማሪ_ዘድንግል


በዳዊት በገና በያሬድ ዝማሬ
እኔም ላወድስሽ ቃላትን ደርድሬ
የጌታዬ እናት ስምሽ ይጣፍጣል
ባህዛብ መካከል አፌ አንችን ይጠራል
ማርያም ማርያም ስልሽ ጠላት ይሸበራል
አሁንም ጠራሁሽ አውሬው እርር ይበል
አምላኬ ስጥራሽ ሰምቻለሁ በፍቅር
እናቴ ለክብርሽ አልሻም ምስክር
ምልጃና ፀሎትሽ ምርኩዜ ሆኖኝ
አሰፈሪውን ለሊት ስንቱን አለፈኩኝ
ልቤ አይከፈትም ዝግ ነው ለጠላቴ
ዘውትር አይለየኝም ስእልሽ ከደረቴ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

፤እንቺ የገነት ምንጭ ፥ የሕይውት ውኃ ጉድጓድ ፥ከሊበኖስም
የሚፈስስ ወንዘ ነሽ። መኃልየመኃለይ ዘሰሎሞን4 ፡ 15

ግጥም፦ዘኪ

🔸 @linkortodoxe21
🔸 @linkortodoxe21
🔸 @linkortodoxe21
ሰው ሆይ! የሚጎዳህ ሀብትህ አይደለም፤ ድኽነትህም አይደለም። ሰውን የሚጎዳው ክፉ ልብ ነው። ክፉ ልብ ደግሞ በሀብትም፣ ሀብት በማጣትም የሚመጣ አይደለም። ክፉ ልብ ሌሎች ክፉ ልቦችን ይወልዳል። እሳት እሳትን እየወለደ ብዙ እንጨቶችን እንደሚበላ ኹሉ ክፉ ልብም እንደዚህ ነው።

አንተ ሰው! ይህን ማወቅ ትወዳለህን? ክፉ ምግባር ወ ይም በጎ ምግባር በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። እነዚህ ኹለቱ ከክፉ ልብ ወይም ከመልካም ልብ የሚገኙ ናቸው።

© ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ አምስቱ የንስሓ መንገዶች፥ ገ. 9

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
Forwarded from ✟ የተዋህዶ ልጆች ✟ (✟Mentesenhot✟)
🔸እንካን አደረሳችሁ

እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች
አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤
(ትንቢተ ዳንኤል 10:13)

#join or #share
🔹 @Ortodoxe19
🔹 @Ortodoxe19
🔹 @Ortodoxe19
😊እንካን አደረሳችሁ በዛሬ ቀን ቤተክርስቲያናችን በደንብ የምታከብራቸው በዓላት መካከል ይህ አንድ ነው።
ዛሬ ጾም የሚፈሰክበት የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓል በተለየ ሁኔታ የቅዱስ ጳውሎስ ወጴጥሮስ የተሰውበት ቀን ነች እና እንካን አደረሳችሁ አደረሰን

@linkortodoxe21
ውድ ክርስቲያኖች እንኳን አደረሳችሁ
#ሐዋርያነት
ሐምሌ ፭ ቀን ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የተቀበሉበት መታሰቢያ ዕለት ነው። ሐዋርያነት እስከ ሞት ድረስ እውነትን መናገር ነው። ሐዋርያነት ንጉሡ ኔሮንን እንዳይከፋው ተብሎ እውነትን ባለመናገር መተባበር አይደለም። መከራን፣ሞትን ሳይሰቀቁ እውነትን በአደባባይ መናገር ነው። ሐዋርያነት ፍቅርን ትእግስትን፣ ትሕትናን መሠረት አድርጎ እውነትን በአደባባይ መመስከር ነው። እውነትን መናገር ብቻ ሳይሆን ውሸትንም በአደባባይ መቃወም ነው።
።።
ሐዋርያነት ሁሉን ትቶ መከተል ነው። ራሱ ቅዱስ ጴጥሮስ ኀደግነ ኵሎ ወተሎናከ ሁሉን ትተን ተከተልንህ ምንተ እንከ ንረክብ እንግዲህ ምን እናገኛለን ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጠይቆት ነበረ። ቅዱስ ጴጥሮስ ምን ትቶ ተከትሎታል ቢሉ አንድ አህያ ነበረችው እርሷን ትቶ ተከትሎታል። ከምንም በላይ ግን "እከብር ባይ ልቡናን" ትቶ ተከትሎታል ብለው መተርጉማን ይናገራሉ። ሐዋርያ የእግዚአብሔርን ቃል በደስታ የሚናገር ነው። እውነትን በአደባባይ የሚመሰክር ነው። ይህን በማድረጉ ሰዎች ሲጠሉት ሲሰድቡት እና መከራን ሲያደርሱበት በደስታ የሚቀበል ነው።
።።
ሐዋርያ ለክብረ ቤተክርስቲያን የሚኖር፣ ፈጣሪውን የሚፈራ፣ በሰው መወደድን እና መከበርን የሚጠላ፣ ክብርን ሁሉ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ፣ ሁሉን እንደራሱ የሚወድ ፍቅር ያለው፣ ለራሱ ድኅነት እና ለሰዎች መዳን የሚተጋ ነው።

የቅዱሳኑ ሐዋርያት በረከት ይደርብን።

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
1
#እንኳን #ለቅድስት #ሥላሴ #ዓመታዊ #በዓል #በሰላም #አደረሳችሁ
ዓለምን ካለመኖር የፈጠሩ፣ ፈጥረውም የሚያስተዳድሩ ሥላሴ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ አንድ ናቸው።

√ በአካላዊ ግብር ሦስት ናቸው። በአካላዊ ግብር ሥምም ሦስት ናቸው። ይህም ወላዲ አሥራጺ፣ ተወላዲ፣ ሠራጺ መባል ነው።

√ በሥልጣናዊ (በባሕርያዊ) ግብር አንድ ናቸው። በባሕርያዊ ግብር ሥምም አንድ ናቸው። ይህም አምላክ፣ ፈጣሪ፣ እግዚአብሔር ወዘተ የመሳሰለው ነው።

√ በከዊን ሦስት ናቸው። እኒህም ቃል መሆን፣ ልብ መሆን፣ እስትንፋስ መሆን ናቸው። በዚህም ሥላሴ ነባብያን፣ ሕያዋን፣ ለባውያን መሆናቸውን እናውቃለን

√ በባሕርይ አንድ ናቸው። ይህም ማለት የሦስቱ ኩነታት ተገናዝቦ አንድ ሕይወተ አንድ ባሕርይ ይባላል።

√ በአካል ሦስት ናቸው። በአካል ሥምም ሦስት ናቸው። ይህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ መባል ነው።

@linkortodoxe21
@linoortodoxe21
@linkortodoxe21
ጠያቂ:እናንተ ክርስትያኖች ግን ስንት አምላክ ነው ያላቹ

ክርስትያን:አንድም ሶስትም ልዩ አንድ ልዩ ሶስት ነት

ጠያቂ:እንዴት አንድ ነገር ሶስት ይሆናል ሶስት ነገርስ እንዴት አንድ ነገር ይሆናል

ክርስትያን:እኛስ መቼ አንድ ነገር ሶስት ይሆናል አልን አዎ አንድ ነገር ሶስት መሆን አይችልም እግዚአብሔር ግን አንድም ሶስትም መሆን ይችላል ተመልከት አንድ ነገር ሶስት መሆን የማይችለው በእኛ አይምሮ ወይም በአለማዊ ነገር ስለን ስላየነው ነው ይህ ደሞ ለአምላክ አይሆንም እኛ እግዚአብሔርን ልዕል አምላክ የምንለው ስለማይመረመር ስላማይደረስበት ጥልቅ ስለሆነ ነው እና አምላክ በእኛ ጭንቅላት ተሰፍቶ እንዴት ይህ ይሆናል ይህማ አይሆንም ብለን በዝች በጠባብ አዕምሮ ከሰፈነው ምኑን ልዕል ተባለ እንዴትስ አምላክ እንለዋለን በእኛ ጭንቅላት ከለካነው ስለዚ ወዳጄ እግዚአብሔር አንድም ሶስትም ነው አንድ ነገር ሶስት ሶስት ነገር አንድ መሆን አይችልም እግዚአብሔር ግን ይችላል

ጠያቂ:😲😲

#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
👍1
[ለእግዚአብሔር ያላችሁ ፍቅር መቀነስ ነው]

በዓለም መደሰት ወደ እግዚአብሔር ሊመራችሁ አይችልም ከእርሱ ያርቃችኋል እንጂ ። የዓለም ፍቅር ወደ ልባችሁ ከገባም አሳቦቻችሁና አመለካከቶቻችሁ መናጋት ይጀምራሉ ።

በዚህ ጊዜ እናንተ ተስማሚ ነው ብላችሁ ያመናችሁበትን አመለካከት እንዲህ እያላችሁ መጠየቅ ትጀምራላችሁ ፦ ይህንንና ያንን ማድረግ ስሕተቱ ምንድር ነው ? ! እንዲህ ባለው ነገር ብደሰት ኃጢአቱ ወይም ጉዳቱ ምንድር ነው ? ! ከዚህ በኋላ በመመርያዎችና በዋጋቸው የሚደረገው ሰንሰለታማ ክርክር ይጀምራል! ! ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ክርክሮችና ሙግቶች ምክንያት የሚሆነው ለእግዚአብሔር ያላችሁ ፍቅር መቀነስ ነው ።

ስለዚህ ልባችሁን በዓለም ፍላጎቶች ወይም ምኞቶች ውስጥ አታስቀምጡ ደጁ ሰፊ ከሆነ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አትችሉምና [ማቴ 7*13]

[_ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ _]

#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
👍1
2025/07/13 23:09:50
Back to Top
HTML Embed Code: