😥ገዳም እንሂድ...ይለኛል ወንድሜ።ዘማነቴን አያውቀውም። ሴሰኝነቴ አይገባውም።እኔ በምናብ ከፈጠርኳት ሴት ጋ ቀን ከሌት በራሴ አለም ስዳራ የኖርኩ መሆኔን ቢያቅብኝ እንኳን ገዳም አብሮኝም ቆሞ ለመታየት ያፍርብኝ ነበር አንተ ያሬድ ተነስ ሰአቱ እረፈደ ነው። ውጣ እንጂ...አለ።(ዛሬ የቁርጥ ቀን ነው።ገዳም ከመሄዱ በላይ የሚፈታተነኝን ግለ ወሲብ የት ጥዬው እንደምሔድ ጨንቆኝ ስገላበጥ ነው ያደርኩት እ....እሺ ይኸው ወጣሁ(ቦርሳዬን ሸክፌ ተከተልኩት።ለአመታት ልወጣበት ካልቻልኩት ድብቁ ሱስ የሚገላግለኝ ሀይል እንደሌለ አምኛለሁ። ተውኩት ስል እየመጣ፤ የሀጥያት ሀፍረት ሲያከናንበኝ ለአመታት ቆይቶብኛል።አንዳንዴ ግልግል ማለትም ያምረኛል.... ሰውዬ ውረድ እንጂ ምነው ዛሬ ፈዘካል....ከረጅም የፒስታ መንገድ በኋላ በጫካ የተከበበች መሀሪት ማርያም ቤተክርስትያን ደረስን።ጫማ ማድረግ የለም።ምግብ የለም። ስልክ አይገባም።ንሰሐ ሳይገቡ መውጣት...(ገና ከበሩ የግቢው ዘብ ህጉን ሲዘረዝረው ልቤ እንደ ሰም ቀለጠች።ስልኬ ላይ በድፍረት የተሸከምኳቸው የነውር ምስሎሽ በአይኔ እየዞሩ ስልኬን አስረክቤ ወንድሜን ተከትዬ ገባሁ...... "አረ አለም በምን ጣዕሟ" እያልኩ እያማረርኩ ነበር የመሸልኝ።ከተማ ጥዬው የመጣሁት ዝሙት ገዳም ስገባ ጭራሽ ያቅበዘብዘኝ ይዟል።ከፀሎቱ ይልቅ ዝሙት አእምሮዬን ወጥሮት የአንድ ሰአቱን ፀሎት እንደጨረስን ስሮጥ ወደ ጫካው ወረድኩ።ሱሴን ላስታግስ...በዝሙት ልወድቅ....እንደገና ደጁ ልበድል...... ሱሪህን ፍታው....!! አረ ተው ፈጣሪን ፍራ!! እዚህ ጨለማ ማን እንዳያይህ ነው!? ከውስጤ ጋ ትግል እየገጠምኩ ከተራራው ቅጠል እያንኮሻኮሸ የሚወርድ የአውሬ ድምፅ ስሰማ ሱሪዬን እየጎተትኩ ወደ ማደሪያው አመለጥኩ...... ጎረምሳው ና እስቲ እቺን ውሀ አድርስልኝ...(ከኪዳን ስንመለስ ጎልመስ ያሉ መለኩሴ ከሰው መሀል ጠሩኝ እሺ አባቴ ችግር የለም..... ባዶ እግሬን ሸንከል እያልኩ ለመለኩሴው ውሀውን በሩ ላይ አድርሼላቸው እንደዞርኩ ሳትገባማ አትሄድም።ና ግድ የለም ጦም ቢሆንም ትንሽ እረፍት አድርግ..... ኦና የሆነ።ጨለማ የወረሰው ቤት ተከትያቸው ገባሁ።እጣን እጣን ይሸታል።በቆርቆሮው ቀዳዳ የሚገባው ጨረር ቀይ ረጅም መጋረጃቸው ላይ ስላረፈ የሚታየው እሱ ብቻ ነው።የተደገፍኩበት ግድግዳ በምርጊት የቀረ የጭቃ ቤት መሆኑ ያስታውቃል።መሬቱም አባጣ ጎርባጣ አቧራማ መሆኑ እግሬ በዳበሳ ሰልሎታል.... ልጅ ያሬድ ተጫወት (አሉ ከጨለማ ውስጥ ለስለስ ያለ ድምፅ አውጥተው በስመአብ ወወልድ።አማተብኩ።ፈራሁ።ስሜን ማን ነገራቸው...??? አይዞህ እንግዲህ የመለኩሴ ቤት።እስቲ እቺን ገመድ ያዛት ልጄ አሉ ጨረሩ እጃቸው ላይ ሲያርፍ አረንጓዴ ገመድ አይቼ ተቀበልኳቸው ምን ላድርገው አባ??? አንገትህ ውስጥ አጥልቀው አልገባኝም።ለምን??ልላቸው ብዬ ገዳም መሆኑ ትዝ ብሎኝ እጄ እየተንቀጠቀጠ አንገቴ ውስጥ ከተትኩት።የሆነ ነገር ነብሴን እየጨነቃት ገመዱ እየተሳበ እየጠበቀ ሲመጣ ይታወቀኛል..... አ....አባ ም...ምንድነው??አልኳቸው የሞት ሞቴን ትንፋሽ እያጠረኝ ።እሳቸው ጋ ግን ከማጥበቅ ውጪ መልስ የለም አባ እያነቁኝ ነው።ገመዱን አስለቅቁኝ አባቴ.....(መልስ የለም አባ ልሞት ነው...(ትንፋሼ እየተቆራረጠ በግድ አወራሁ።ገመዱ እየገዘገዘኝ ደምስሬ እየተወጠረ የጣሬን ገመዱን ይዤ በመጨረሻ አቅሜ... አ....አባ (ስል ገመዱ ድንገት ሲረግብ እኩል ሆነና ትንፋሼን እየለቀቅኩ ተነስቼ ለማምለጥ ቃጣኝ ቁጭበል!! እንዴ ምንድነው ከኔ ሚፈልጉት?? ምን አድርግ ነው ሚሉኝ ቆይ.... ምንም አላልኩህም።ሞት እንዴት እንደሆን በትንሹ ላሳይህ ብዬ ነው።ልጅ ያሬድ ከመጣህ ቀን ጀምሮ አውቅሀለሁ ወንድምህ አንተን እዚህ ሲያመጣህ ተማክረን ነው።አየህ በመጀመርያ ቀን ንሰሐ ግባ ሲልህ አሻፈረኝ ብለካል ነገሩ በግድ ስለማይሆን ተውንክ።አንተ ግን ሌላ በደል.... ሌላ በደል!??? አዎ እንግዲህ እዚ ድረስ መጥተህ ከምትጠፋ ብነግርህ ይቀላል።ያንተን ችግር እኔም ወንድምክም እናቀዋለን።ባለፈው በለሊት ጫካ ውስጥ ከራስህ ስትታገል እንደ አውሬ ጩኼ ያባረርኩህ እኔ ነኝ።አስተውል ያሬድ ቅድም ገመዱን ስሰጥህ ቀለል አርጌ ነበር ሸምቀቆው እየጠበበ ሲመጣ ግን መተንፈስ አቃተህ።ግለ ወሲብም እንዲህ ነው።በተዘዋዋሪ በቀላሉ ትገባበትና እየጠበቀ ሲመጣ ግለ ሞት እራስን በፈቃደኝነት በነብስም በስጋም ማጥፋት ይሆናል።እራስህን ብቸኛው ሀጥያተኛ አድርገህ አታስብ ከመድሀኒቱ ቀድመህ ስለበሽታው ካላወቅክ አትድንም።መተፋፈሩ ይበቃል ከዚህ በላይ ሰይጣን እንዲያዋርድህ አትፍቀድ።ለመንፃት ሳትሰለች ተጠመቅ ንሰሐ ግባ ሰይጣን የደበቅክለትን ነውሩን በእግዜር ፊት ስትገልጥበት እግዚአብሔር ደሞ ከሰይጣን የዘማዊነት አሰራር ይከልልካል።አሁንስ ልጅ ያሬድ ምን ትለኛለህ አባ ለንሰሐ መች ልምጣ...እንዲ መሞት አልፈልግም።(ሲሰንፍ የነበረው ልቤ ያዋረደኝን ሰይጣን ለመጣል ሲነሳሳ ለእግዜር ደሞ ሲብረከረክ ተሰማኝ የመዳን ቀን ዛሬ ነው ልጄ ከመጣህ አሁኑኑ ሀጥያትህን ተናዘህ ሂድ...
ለብዙ ሰው ይጠቅማል #ሼር
https://www.tgoop.com/meazasenay
ለብዙ ሰው ይጠቅማል #ሼር
https://www.tgoop.com/meazasenay
Telegram
መዓዛ ሠናይ
☞ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖታችን እንወቅ
☞እንረዳ
☞እንማማር
♥♥♥♥♥♥
ለበለጠ መረጃ @Tadi16 ላይ ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት እንቀበላለን፡፡
☞እንረዳ
☞እንማማር
♥♥♥♥♥♥
ለበለጠ መረጃ @Tadi16 ላይ ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት እንቀበላለን፡፡
“ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት።” /ማር 5÷34/
"እምነት" በኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ እግዚአብሔር ከፅንሰቱ እስከ እርገቱ ድረስ በምድር ላይ ሰው ሆኖ በፈቃዱቨ ያደረገውን ሁሉ ማመን መቀበል ሳያጎድሉ በምልዐት መቀበል ነው (ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መድልተ ጽድቅ ቅጽ 1) የሰው ልጅ ውድቀቱ መነሳቱ በእምነት ማጣት እና ማግኘት ነው።
አስቀድሞ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሲፈጥረው እንደራሱ አድሮጎ በተፈጠረለት ማንነቱ በንፅሕናው ተፈጥሮ መልካምና ክፍውን ይለይ ዘንድ ነፃ ፍቃድ ሰጥቶ ፈጠው ከእርሱ በፈት የተፈጠሩት ፍጥረታት ሁሉ አዳም የእግዚአብሔር ስራ አይቶ በመድነቅ ከእግዚአብሔር ጋር በእምነት በታማኝነት አንድላይ ይኖሩ ዘንድ ፍጥረታት ተፈጠሩለት እግዚአብሔር ከዚህ ከተፈጠረለት ማንነት እንዳይወጣ አሰቀድሞ " ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካም እና ክፍውን ከሚያሳውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ በማለት አዞት " ግን ከእግዚአብሔር ይልቅ የሴጣንን ምክር ሰምቶ አምኖ ሞትን በራሱ ላይ አመጣ የቀደመችው ሔዋን ሴጣንን አምና ሞትን በእራሷና ከአብራኩ ካስገኛት አዳም ሞትን አመጣች።
ዳግማዊቷ ሔዋን ድንግል ማርያም ግን መጀመርያ ሞት በመጣበት መንገድ የእምነት ማጣት ትሞላ ዘንድ ቀድማ የሴጣንን ምክር በተቀበለችው ሔዋን ፍንታ የመላኩን ቃል በእምነት በመቀበል ለፈጣሪ ያለንን እምነት መለሰችልን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእምነት በመኖራቸው የእምነታቸውን ፍሬ ያፈሩ እና በሕይወታቸው ሁሉን የእግዚአብሔር ቻይነት የመሰከሩ እሩስም ታማኝነታቸውን በበረከት የመሰከረላቸው አሉ ከእንዚህም ውስጥ የመጥምቁ እናት ቅድስት ኤልሳቤጥ ናት እስከ እርጅናዋ ዘመን ድረስ እግዚአብሔር ስታገለግል የኖረች የካህኑ ዘካርያስ ሚስት ኤልሳቤት ታሪኳ በሉቃ 1÷5 ተፅፎ እናገኛለች ኤልሳቤጥ በዘመኗ ሁሉ እግዚአብሔር ባይሰጣትም ልጅ እንደሚሰጣት አንድ ቀን አምና የእግዚአብሔር ሁሉ ቻይነት እመሰከረች ኖረች።
እግዚአብሔር የኤልሳቤጥን እሱን አምና ለዘመናት ሳታማርር መኖሯን አይቶ ጌታን የሚያጠምቀውን መጥምቁ ዮሐንስን ሰጥቷት እምነቷን መሰከረላት ይህ ሁሉ የሆነው በኤልሳቤጥ በእምነት መኖር ነው። ሰማዕታት የእግዚአብሔርን ክብር እየመሰከሩ በርሃብ እርሱን ምግብ አርገው ሁሉን እንደማያሳጣቸው እየመሰከሩ ኖሩ እግዚአብሔር በገባላቸው ቃልኪዳን ዘወትር ፍጥረታትን በስማቸው እየመገበ እምነታቸውን መሰከረላቸው።
(ማቴ 20÷22) ተፅፎ የምናገኘው አንድ ታሪክ አለ ከአስራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም ይፈሳት የነበረች ሴት ብዙ ባለመዳኒቶች ጋር ገንዘቧን የጨረሰች ግን የገንዘቧ ማለቅ ደሟ መፍሰሱን ያላስለቀቀላት" ያልቆመላት ሴት። ይች ሴት ክርስቶስን ልብሱን የነካው እንደሆነ እፈወሳለሁ ብላ በእምነት አምና ቀረበች ዳሰሰችውም ዳነች። ክርስቶስ ልጄ ሆይ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል ብሎ መሰከረላት። ይህች ሴት የክርስቶስን በስጋ ውስጥ ሳይታይ ያለውን ሁሉን ቻይነት አምና ሊፈውሳት እንደሚችል አምላክነቱን በእምነት መሰከረች። ክርስቶስ በማይታየው እምነቷ የሚታየውን በሽታዋን በመፈወስ እምነቷን መሰከረላት።
ወዳጆቼ ብዙ የሚታይ በሽታ ይዞን ይሆናል እንደ ዘመኑ ሰው የመግደል በሽታ አልቅሶ እስካለየነው ደስታ የማይሰማን የመሆን በሽታ ፍቅርን በመግፍት አንጂ በተጠላን ልክ የማይገኝ ሲመሰለን በትውልድ ውስጥ ጥላቻ እየጫሩ የመኖር ይህ ሁሉ የሚታይ የግፍ ውጤት ሊቆም ያልቻለው የማይታየው እምነት ስለሌለን ፈጣሪ ሳይሆን ሴጣን እየመሰከረልን እየኖርን እንገኛል። ስለዚህ ፈጣሪ እንዲመሰክርልን ወደ እርሱ እንመለስ።
"እምነት" በኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ እግዚአብሔር ከፅንሰቱ እስከ እርገቱ ድረስ በምድር ላይ ሰው ሆኖ በፈቃዱቨ ያደረገውን ሁሉ ማመን መቀበል ሳያጎድሉ በምልዐት መቀበል ነው (ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መድልተ ጽድቅ ቅጽ 1) የሰው ልጅ ውድቀቱ መነሳቱ በእምነት ማጣት እና ማግኘት ነው።
አስቀድሞ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሲፈጥረው እንደራሱ አድሮጎ በተፈጠረለት ማንነቱ በንፅሕናው ተፈጥሮ መልካምና ክፍውን ይለይ ዘንድ ነፃ ፍቃድ ሰጥቶ ፈጠው ከእርሱ በፈት የተፈጠሩት ፍጥረታት ሁሉ አዳም የእግዚአብሔር ስራ አይቶ በመድነቅ ከእግዚአብሔር ጋር በእምነት በታማኝነት አንድላይ ይኖሩ ዘንድ ፍጥረታት ተፈጠሩለት እግዚአብሔር ከዚህ ከተፈጠረለት ማንነት እንዳይወጣ አሰቀድሞ " ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካም እና ክፍውን ከሚያሳውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ በማለት አዞት " ግን ከእግዚአብሔር ይልቅ የሴጣንን ምክር ሰምቶ አምኖ ሞትን በራሱ ላይ አመጣ የቀደመችው ሔዋን ሴጣንን አምና ሞትን በእራሷና ከአብራኩ ካስገኛት አዳም ሞትን አመጣች።
ዳግማዊቷ ሔዋን ድንግል ማርያም ግን መጀመርያ ሞት በመጣበት መንገድ የእምነት ማጣት ትሞላ ዘንድ ቀድማ የሴጣንን ምክር በተቀበለችው ሔዋን ፍንታ የመላኩን ቃል በእምነት በመቀበል ለፈጣሪ ያለንን እምነት መለሰችልን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእምነት በመኖራቸው የእምነታቸውን ፍሬ ያፈሩ እና በሕይወታቸው ሁሉን የእግዚአብሔር ቻይነት የመሰከሩ እሩስም ታማኝነታቸውን በበረከት የመሰከረላቸው አሉ ከእንዚህም ውስጥ የመጥምቁ እናት ቅድስት ኤልሳቤጥ ናት እስከ እርጅናዋ ዘመን ድረስ እግዚአብሔር ስታገለግል የኖረች የካህኑ ዘካርያስ ሚስት ኤልሳቤት ታሪኳ በሉቃ 1÷5 ተፅፎ እናገኛለች ኤልሳቤጥ በዘመኗ ሁሉ እግዚአብሔር ባይሰጣትም ልጅ እንደሚሰጣት አንድ ቀን አምና የእግዚአብሔር ሁሉ ቻይነት እመሰከረች ኖረች።
እግዚአብሔር የኤልሳቤጥን እሱን አምና ለዘመናት ሳታማርር መኖሯን አይቶ ጌታን የሚያጠምቀውን መጥምቁ ዮሐንስን ሰጥቷት እምነቷን መሰከረላት ይህ ሁሉ የሆነው በኤልሳቤጥ በእምነት መኖር ነው። ሰማዕታት የእግዚአብሔርን ክብር እየመሰከሩ በርሃብ እርሱን ምግብ አርገው ሁሉን እንደማያሳጣቸው እየመሰከሩ ኖሩ እግዚአብሔር በገባላቸው ቃልኪዳን ዘወትር ፍጥረታትን በስማቸው እየመገበ እምነታቸውን መሰከረላቸው።
(ማቴ 20÷22) ተፅፎ የምናገኘው አንድ ታሪክ አለ ከአስራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም ይፈሳት የነበረች ሴት ብዙ ባለመዳኒቶች ጋር ገንዘቧን የጨረሰች ግን የገንዘቧ ማለቅ ደሟ መፍሰሱን ያላስለቀቀላት" ያልቆመላት ሴት። ይች ሴት ክርስቶስን ልብሱን የነካው እንደሆነ እፈወሳለሁ ብላ በእምነት አምና ቀረበች ዳሰሰችውም ዳነች። ክርስቶስ ልጄ ሆይ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል ብሎ መሰከረላት። ይህች ሴት የክርስቶስን በስጋ ውስጥ ሳይታይ ያለውን ሁሉን ቻይነት አምና ሊፈውሳት እንደሚችል አምላክነቱን በእምነት መሰከረች። ክርስቶስ በማይታየው እምነቷ የሚታየውን በሽታዋን በመፈወስ እምነቷን መሰከረላት።
ወዳጆቼ ብዙ የሚታይ በሽታ ይዞን ይሆናል እንደ ዘመኑ ሰው የመግደል በሽታ አልቅሶ እስካለየነው ደስታ የማይሰማን የመሆን በሽታ ፍቅርን በመግፍት አንጂ በተጠላን ልክ የማይገኝ ሲመሰለን በትውልድ ውስጥ ጥላቻ እየጫሩ የመኖር ይህ ሁሉ የሚታይ የግፍ ውጤት ሊቆም ያልቻለው የማይታየው እምነት ስለሌለን ፈጣሪ ሳይሆን ሴጣን እየመሰከረልን እየኖርን እንገኛል። ስለዚህ ፈጣሪ እንዲመሰክርልን ወደ እርሱ እንመለስ።
#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል (#ታኅሣሥ_19)
ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡
ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡
በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡
የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡
መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ)
ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡
ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡
በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡
የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡
መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ)
"ልጆቼ! የሚያሳፍር ነገር፣ የስንፍና ንግግር ወይም ዋዛ ፈዛዛ የማይገቡ ናቸውና በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ ከቶ አይሰሙ፡፡ እስኪ ንገሩኝ! የዋዛ ፈዛዛ ንግግር ጥቅሙ ምንድን ነው? እስኪ ንገሩኝ፤ አንድ ጫማ ሰፊ፣ ጫማ እየሰፋ በአንድ ጊዜ ሌላ ሥራ መሥራት ይችላልን? አይችልም፡፡ ከዋዛ ፈዛዛ የሚያሳፍር ንግግር ይወለዳል፡፡ የአሁኑ ጊዜ ደግሞ ለእኛ ለክርስቲያኖች ዋዛ ፈዛዛ የምንናገርበት ሳይኾን የንስሐችን ጊዜ ነው፡፡ እስኪ አሁንም ልጠይቃችሁና እናንተም መልሱልኝ! አንድ ቦክስ የሚጫወት ሰው ውድድሩን ችላ ብሎ ዋዛ ፈዛዛን ይናገራልን? እንዲህ የሚያደርግ ከኾነስ በተጋጣሚው በቀላሉ የሚሸነፍ አይደለምን? ታዲያ ባለጋራችን ዲያብሎስ‘ኮ የሚውጠውን ፈልጐ እንደሚያገሣ አንበሳ በዙርያችን ቁሟል፡፡ ጥርሱን እያንቀጫቀጨብን ነው፡፡ እኛን የሚጥልበት ወጥመድ በማዘጋጀት ላይ ነው፡፡ የደኅንነታችን መንገድ ላይ እሳት እየተነፈሰ ነው፡፡ ታዲያ ዲያብሎስ እንዲህ እኛን ለመጣል ሲተጋ እኛ ዋዛ ፈዛዛን፣ የሚያሳፍር ነገርን፣ የስንፍናንም ንግግር ስንናገር ቁጭ ልንል ይገባናልን?
የምወዳችሁ ልጆቼ! ጊዜው የምንተኛበት ጊዜ አይደለም፡፡ የተጋድሎ ጊዜ ነው እንጂ፡፡ ቅዱሳን ጊዜያቸውን እንደ ምን እንደሚያሳልፉት ማወቅ ትፈልጋላችሁን? እስኪ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን አብረን እንስማው፤ እንዲህ ያለውን፡- “ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሠጽ እዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ”፤ … “በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችኋለሁ…”፡፡ … “የሚደክም ማን ነው፤ እኔ አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፤ እኔም አልናደድምን?”፤ “… በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን”፡፡ ታዲያ እነ ቅዱስ ጳውሎስ ጊዜያቸውን እንዲህ ካሳለፉ፣ ኃጥአን የምንኾን እኛ ጊዜያችንን በሳቅና ስላቅ ልናጠፋ ይገባናልን? በክርስቶስ ፍቅር የማፈቅራችሁ ልጆቼ! በንግግሬ አትማረሩ፡፡
ጊዜው የተጋድሎ ጊዜ ነው፤ ታዲያ ስለ ምንድን ነው የዘፋኞችን መሣርያ አንሥተን ከዓለም ጋር የምንዘፍነው? በጦር ግንባር ያለ ወታደር ከጠላት ሊመጣ የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል ከመዘጋጀት ይልቅ ጊዜውን በዋዛ ፈዛዛ ያጠፋልን? አያጠፋም፡፡ ታዲያ እኛም‘ኮ የክርስቶስ በጎ ወታደሮች ነን፡፡ ..."
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የምወዳችሁ ልጆቼ! ጊዜው የምንተኛበት ጊዜ አይደለም፡፡ የተጋድሎ ጊዜ ነው እንጂ፡፡ ቅዱሳን ጊዜያቸውን እንደ ምን እንደሚያሳልፉት ማወቅ ትፈልጋላችሁን? እስኪ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን አብረን እንስማው፤ እንዲህ ያለውን፡- “ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሠጽ እዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ”፤ … “በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችኋለሁ…”፡፡ … “የሚደክም ማን ነው፤ እኔ አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፤ እኔም አልናደድምን?”፤ “… በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን”፡፡ ታዲያ እነ ቅዱስ ጳውሎስ ጊዜያቸውን እንዲህ ካሳለፉ፣ ኃጥአን የምንኾን እኛ ጊዜያችንን በሳቅና ስላቅ ልናጠፋ ይገባናልን? በክርስቶስ ፍቅር የማፈቅራችሁ ልጆቼ! በንግግሬ አትማረሩ፡፡
ጊዜው የተጋድሎ ጊዜ ነው፤ ታዲያ ስለ ምንድን ነው የዘፋኞችን መሣርያ አንሥተን ከዓለም ጋር የምንዘፍነው? በጦር ግንባር ያለ ወታደር ከጠላት ሊመጣ የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል ከመዘጋጀት ይልቅ ጊዜውን በዋዛ ፈዛዛ ያጠፋልን? አያጠፋም፡፡ ታዲያ እኛም‘ኮ የክርስቶስ በጎ ወታደሮች ነን፡፡ ..."
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
ጌታችን ስለተወለደባት ምሽት ቅዱስ ኤፍሬም አንዲህ አለ....
.
‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡ ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ!
ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት! ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት!
ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡ ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ!
የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!››
እንኳን ለአምላካችን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
.
‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡ ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ!
ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት! ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት!
ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡ ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ!
የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!››
እንኳን ለአምላካችን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
ሰብአ ሰገል ይዘው የመጡት ወርቅ ዕጣንና
ከርቤ ከየት መጣ?
በቅድምያ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ልደት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሁንልን።
ጌታችን በተወለደ ጊዜ ሰብአ ሰገል የገበሩተለት ወርቅ ፣ ዕጣንና ከርቤ መገኛቸው ከገነት እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ ጥንት አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በገነት ውስጥ በሰላምና በተድላ ይኖሩ ነበር። ታዲያ ዲያቢሎስ አትብሉ የተባሉትን እንዲበሉ ሐሳብ አቅርቦ ካሳታቸው በኋላ ያን አትብሉ የተባሉትን በመብላታቸው ትዕዛዝ በመተላለፋቸው ሰባት ዓመት ከ47 ቀን በተድላ ከኖሩበት ገነት ተባረሩ። ከገነት ከወጡ በሁላ አዳምና ሔዋን በዚህ ምድር ላይ ኑሮአቸውን ሀ ብለው ጀመሩ።
አንድ ቀን አዳም እናታችን ሔዋንን በባል ልማድ ሊጨዋወታት (ሊገናኛት) ወዶ በመንገድ ጠብቆ አስደነገጣት ታዲያ ይህን ጊዜ ሥላሴ ተገልጠው "ምነው ማጫውን ሳትሰጠን ልጃችን ትነካለህን?" ቢሉት አዳምም "ጌታዩ የአንተ ያልሆነ የኔ የሆነ ምን አለኝና እሰጥሀለው!" ቢሊ "አይ ለኋልኛው ዘመን ሥርዓት ነውና ይህን ለእርሷ ስጣት እንኳ" ብለው ቅዱስ ሚካኤል ወርቁን ፣ ቅዱስ ገብርኤል ዕጣኑን ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ደግሞ ከርቤውን ለአዳም ሰጥተውታል። አዳምም ተቀብሎ ለሔዋን ሰጣት ፣ ሔዋን ለሴት ሰጠችው ፤ ከሴት ሲወርድ ሰዋረድ ከኖህ ደረሰ፡ ኖህ በጥፋት ውኅ ዘመን ወደ መርከብ ሲገባ የአዳምን አጥንትና ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአንድነት ይዞ ገባ።
ኋላ የጥፋት ውኀው ጎደለና ከመርከብ ይዞትጰወጣ በሁላ ለሴም ሰጠው ፤ ሴምም መልከጼዴቅን ተገናኘውና የአዳምን አጥንት በጎለጎታ ቀበሩት። ለዚህም ነው የጌታችን የሥነ ስቅለቱ ስዕል ሲሳል ከሥር የራስ ቅል አጥንት የሚደረገው ያም የአዳም አጥንት ምሳሌ ነው። ከዚያም ሴም ለመልከጼዴቅ ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአደራ አስጠበቀው፡ መልከጼዴቅ ለአብርሃም ሰጠው።
ከአብርሃም ሲወርድ ሲወረድ በዳዊት በሰለሞን አድርጎ ከአካዝ ደረሰ፡ በአካዝ ዘመን ቴልጌልፌልሶር ማርኮ ወስዶ ከቤተ መዛግብት አኑሮታል፡ አባታቸው ዥረደሸት ፈላስፋ ነበር፡ አንድ ቀን በቀትር ከውኃ ዳር ሆኖ ሲፈላሰፍ በሰሌዳ ኮከብ ድንግል ሕፃን ታቅፋ አየ ያየውን በሰሌዳ ቀርጾ አሰቀመጠው ከመሞቱ በፊትም እንዲህ ያለ ኮከብ ሲወጣ ባያችሁ ግዜ ሰማያዊ ንጉስ ይወለዳልና ወስዳቹ ይህን ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤ ስጡት ብሎ ለልጆቹ ተናዞ ሞተ። በዚህ መልኩ ከእነዚህ ነገሥታት እጅ ደርሷል። በእርግጥ ታሪኩን ለመተረክ አንድ መጽሐፍ የሚበቃውም አይደለም ከረጅም በአጭሩ ግን ይህን ይመስላል።
ታዲያ ኮከቡም በታየ ግዜ የታዘዙትን ለመፈፀም 12
ነገስታት ፍርሻኩር የተባለ ንጉሥ እየመራቸው ከሀገራቸው ተነሱ እያንዳንዱ ነገሰታት 10 ሺህ የሚሆን ሠራዊት ይዘው በጉዞ ላይ እያሉ ኤፍራጥስ ወንዝ ሲደርሱ ፍርሻኩር የተባለው መሪያቸው ዘጠኙን ነገስታት ከነሰራዊታቸው ይዟቸው ተመለሰ ከተመለሱበት ምክንያት ውስጥ ግማሹ ስንቅ አልቆባቸው ሌሎቹ ደግሞ በሀገራቸው ጠላት ተነስቶባችዋል የሚል ወሬ ሰምተው ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ኢየሩሳሌም ለሰላሳ ሺ ሠራዊት አትበቃም ጠባብ ናት ብለው የተመለሱም አሉ። ምስጢሩ ግን ከበረከተ ልደቱ እንዲሳተፋ የተመረጡት ሦስቱ ብቻ መሆናቸውን የጠይቃል የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ጥቂቶች ናቸው እንደተባለ።
ከርቤ ከየት መጣ?
በቅድምያ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ልደት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሁንልን።
ጌታችን በተወለደ ጊዜ ሰብአ ሰገል የገበሩተለት ወርቅ ፣ ዕጣንና ከርቤ መገኛቸው ከገነት እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ ጥንት አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በገነት ውስጥ በሰላምና በተድላ ይኖሩ ነበር። ታዲያ ዲያቢሎስ አትብሉ የተባሉትን እንዲበሉ ሐሳብ አቅርቦ ካሳታቸው በኋላ ያን አትብሉ የተባሉትን በመብላታቸው ትዕዛዝ በመተላለፋቸው ሰባት ዓመት ከ47 ቀን በተድላ ከኖሩበት ገነት ተባረሩ። ከገነት ከወጡ በሁላ አዳምና ሔዋን በዚህ ምድር ላይ ኑሮአቸውን ሀ ብለው ጀመሩ።
አንድ ቀን አዳም እናታችን ሔዋንን በባል ልማድ ሊጨዋወታት (ሊገናኛት) ወዶ በመንገድ ጠብቆ አስደነገጣት ታዲያ ይህን ጊዜ ሥላሴ ተገልጠው "ምነው ማጫውን ሳትሰጠን ልጃችን ትነካለህን?" ቢሉት አዳምም "ጌታዩ የአንተ ያልሆነ የኔ የሆነ ምን አለኝና እሰጥሀለው!" ቢሊ "አይ ለኋልኛው ዘመን ሥርዓት ነውና ይህን ለእርሷ ስጣት እንኳ" ብለው ቅዱስ ሚካኤል ወርቁን ፣ ቅዱስ ገብርኤል ዕጣኑን ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ደግሞ ከርቤውን ለአዳም ሰጥተውታል። አዳምም ተቀብሎ ለሔዋን ሰጣት ፣ ሔዋን ለሴት ሰጠችው ፤ ከሴት ሲወርድ ሰዋረድ ከኖህ ደረሰ፡ ኖህ በጥፋት ውኅ ዘመን ወደ መርከብ ሲገባ የአዳምን አጥንትና ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአንድነት ይዞ ገባ።
ኋላ የጥፋት ውኀው ጎደለና ከመርከብ ይዞትጰወጣ በሁላ ለሴም ሰጠው ፤ ሴምም መልከጼዴቅን ተገናኘውና የአዳምን አጥንት በጎለጎታ ቀበሩት። ለዚህም ነው የጌታችን የሥነ ስቅለቱ ስዕል ሲሳል ከሥር የራስ ቅል አጥንት የሚደረገው ያም የአዳም አጥንት ምሳሌ ነው። ከዚያም ሴም ለመልከጼዴቅ ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአደራ አስጠበቀው፡ መልከጼዴቅ ለአብርሃም ሰጠው።
ከአብርሃም ሲወርድ ሲወረድ በዳዊት በሰለሞን አድርጎ ከአካዝ ደረሰ፡ በአካዝ ዘመን ቴልጌልፌልሶር ማርኮ ወስዶ ከቤተ መዛግብት አኑሮታል፡ አባታቸው ዥረደሸት ፈላስፋ ነበር፡ አንድ ቀን በቀትር ከውኃ ዳር ሆኖ ሲፈላሰፍ በሰሌዳ ኮከብ ድንግል ሕፃን ታቅፋ አየ ያየውን በሰሌዳ ቀርጾ አሰቀመጠው ከመሞቱ በፊትም እንዲህ ያለ ኮከብ ሲወጣ ባያችሁ ግዜ ሰማያዊ ንጉስ ይወለዳልና ወስዳቹ ይህን ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤ ስጡት ብሎ ለልጆቹ ተናዞ ሞተ። በዚህ መልኩ ከእነዚህ ነገሥታት እጅ ደርሷል። በእርግጥ ታሪኩን ለመተረክ አንድ መጽሐፍ የሚበቃውም አይደለም ከረጅም በአጭሩ ግን ይህን ይመስላል።
ታዲያ ኮከቡም በታየ ግዜ የታዘዙትን ለመፈፀም 12
ነገስታት ፍርሻኩር የተባለ ንጉሥ እየመራቸው ከሀገራቸው ተነሱ እያንዳንዱ ነገሰታት 10 ሺህ የሚሆን ሠራዊት ይዘው በጉዞ ላይ እያሉ ኤፍራጥስ ወንዝ ሲደርሱ ፍርሻኩር የተባለው መሪያቸው ዘጠኙን ነገስታት ከነሰራዊታቸው ይዟቸው ተመለሰ ከተመለሱበት ምክንያት ውስጥ ግማሹ ስንቅ አልቆባቸው ሌሎቹ ደግሞ በሀገራቸው ጠላት ተነስቶባችዋል የሚል ወሬ ሰምተው ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ኢየሩሳሌም ለሰላሳ ሺ ሠራዊት አትበቃም ጠባብ ናት ብለው የተመለሱም አሉ። ምስጢሩ ግን ከበረከተ ልደቱ እንዲሳተፋ የተመረጡት ሦስቱ ብቻ መሆናቸውን የጠይቃል የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ጥቂቶች ናቸው እንደተባለ።
የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
Telegram
ማኅቶት ፕሮሞሽን💓
You’ve been invited to add the folder “ማኅቶት ፕሮሞሽን💓”, which includes 99 chats.
የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
Telegram
ማኅቶት ፕሮሞሽን💓
You’ve been invited to add the folder “ማኅቶት ፕሮሞሽን💓”, which includes 99 chats.
የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡
🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞
🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧
🎶 ዘወይን ዘወይን ✞
🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡
🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞
🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ
🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡
🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡
🎶 እንዘስውር ✧
እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
join join join
Join join join
Telegram
ማኅቶት ፕሮሞሽን💓
You’ve been invited to add the folder “ማኅቶት ፕሮሞሽን💓”, which includes 99 chats.
"...ክርስቲያኖች ግን ክርስቲያኖች ለመኾናቸው መታወቅ የሚገባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ምሥጢራትን ሲቀበሉ ብቻ ሳይኾን የትም ቦታ በሚኖሩት የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በአፍአ የከበሩ ሰዎች በአፍአ ከሚያሳዩት ምልክት እንደሚታወቁ ኹሉ፥ እኛም ልንታወቅ የሚገባን በነፍሳችን ክብር ነው፡፡ በሌላ አገላለጥ አንድ ክርስቲያን መታወቅ ያለበት በተሰጠው ልጅነት ብቻ ሳይኾን ለልጅነቱ እንደሚገባ በሚያሳየው አዲስ ሕይወትም ጭምር ሊኾን ይገባል፡፡ ይህ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃንና ጨው ሊኾን ይገባዋል፡፡ ለዓለም ብርሃን መኾንህስ ይቅርና ለራስህ እንኳን ብርሃን መኾን ካልተቻለህ፣ የሚሰፋ ቁስልህን በዘይት ማሰርም ካቃተህ፥ ክርስቲያን መኾንህን የምናውቀው እንዴት ነው? ወደ ተቀደሰው ውኃ ገብተህ በመጠመቅህ ነውን? በዚህስ አይደለም ! ይህስ እንዲያውም ዕዳ ፍዳ ይኾንብሃል [እንጂ ክርስቲያን መኾንህን እንድናውቅህ አያደርገንም]፡፡ ይህ ሀብት (ልጅነት) ታላቅ ነውና ለዚህ ሀብት እንደሚገባ ለማይኖሩት ሰዎች ዕዳ ፍዳ መጨመሪያ ነው፡፡ አዎን፥ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃኑን ማብራት ያለበት ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ ብቻ ሳይኾን እርሱ ራሱም ድርሻውን በመወጣት ነውና፡፡ ክርስቲያን ካልኾኑት ይልቅ በኹለንተናው በአረማመዱ፣ በአተያዩ፣ በአለባበሱ፣ በአነጋገሩ ብልጫ ሲኖረው ነውና፡፡ ይህንም የምለው ልጅነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች ልጅነትን ተቀበሉ በመባል ብቻ ሳይኾን የሌሎች ሰዎች ረብ ጥቅም ይኾን ዘንድ ለተቀበሉት ልጅነት የሚገባና ሥርዓት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ ስለምሻ ነው፡፡
አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡
ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ [በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡] ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?"
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ድርሳን 4፥14-15 ገጽ 80-82 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡
ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ [በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡] ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?"
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ድርሳን 4፥14-15 ገጽ 80-82 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም - #ጥር_21
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሀዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
አበው ስለ #እመቤታችን_ዕረፍት እንዲህ አሉ፦
"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ
(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)
"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ
(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)
🎬 ምን አይነት የኦርቶዶክስ መንፈሳዊ ፊልም መመልከት ይፈልጋሉ❓️
🎬 JOIN አዳምና ሔዋን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የኢየሱስ ክርስቶስ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN አቡነ ተክለሃይማኖት ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ጠቢቡ ሰለሞን ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የሃያል ሳምሶን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የአባ ጳውሊ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ቅድስት አርሴማ ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የነብዩ ቅዱስ ሙሴ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN አባ ኖብ ሙሉ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ
✅ እንደ ምርጫው መርጠው ይ🀄️ላ🀄️ሉ ✅
ማኅቶት Wave ለመቀላቀል
www.tgoop.com/Makda25
🎬 JOIN አዳምና ሔዋን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የኢየሱስ ክርስቶስ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN አቡነ ተክለሃይማኖት ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ጠቢቡ ሰለሞን ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የሃያል ሳምሶን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የአባ ጳውሊ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ቅድስት አርሴማ ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN የነብዩ ቅዱስ ሙሴ ፊልም 👈 ይንኩ
🎬 JOIN አባ ኖብ ሙሉ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ
✅ እንደ ምርጫው መርጠው ይ🀄️ላ🀄️ሉ ✅
ማኅቶት Wave ለመቀላቀል
www.tgoop.com/Makda25
Telegram
ማኅቶት ፕሮሞሽን💓
You’ve been invited to add the folder “ማኅቶት ፕሮሞሽን💓”, which includes 100 chats.