Warning: Undefined array key 0 in /var/www/tgoop/function.php on line 65

Warning: Trying to access array offset on value of type null in /var/www/tgoop/function.php on line 65
- Telegram Web
Telegram Web
በዱባይ በተደረገው የፖሊስ SWAT ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 101ኛ መውጣቱ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ላለፉት ጥቂት ቀናት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ዱባይ ከተማ በተካሄደው እና የ103 ሀገራት የSWAT ፖሊስ ቡድን አባላት በተሳተፉበት ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 101ኛ መውጣቱ ታውቋል።

ይህ Special Weapons And Tactics (የልዩ መሳርያዎች እና ታክቲኮች) የቡድን ውድድር ላይ የቻይና B ቡድን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፣ የካዛክስታኑ ሱንካር ፖሊስ ሁለተኛ እንዲሁም የቻይና C ቡድን ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል (ሊንክ: https://uaeswatchallenge.com/?page_id=11727)

በ SWAT ውድድሩ ላይ ሲወዳደር የቆየው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ቡድን ከሁለት ቀን በፊት በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮች አቀባበል ተደርጎለታል።

በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፤ እንደ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ የፖሊስ ተቋም በተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች SWAT ውድድር ላይ መሳተፉ ለሀገራችን ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ከማስገኘቱም ባሻገር ዓለም አቀፍ የፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነትን ለማዳበር ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የፖሊስ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ውድድር ላይ መሳተፍ መቻላችን ልምድና ተሞክሮ እንድናገኝ ያስቻለን ነው ሲሉም ጠቁመዋል፡፡

በቀጣይም እ.ኤ.አ 2026 በሚካሄደው ውድድር ላይ አስፈላጊውን ስልጠና በመውሰድ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትጋት እንሠራለን ሲሉም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲጓዝ እና ውድድሩን አጠናቆ ወደ ሀገር ሲመለስ በስፋት በመንግስት ሚድያዎች ቢበገብም ያስመዘገበው አነስተኛ ውጤት ግን ለህዝብ አልተገለፀም።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
"ጠበቃዎችን እያነጋገርኩ ነው፣ በአቪዬሽን ህግ ሊከለክሉኝ እንደማይችሉ ተነግሮኛል"- አቶ ልደቱ አያሌው ለመሠረት ሚድያ

(መሠረት ሚድያ)- ዛሬ ጠዋት ከአሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ለመጓዝ በአትላንታ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ቢገኙም እንዳይሳፈሩ የተደረጉት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው ጉዳዩን በህግ ሊይዙት እንደሚችሉ ተናገሩ።

"አየር ማረፊያው ስገኝ ሰራተኞቹ የ boarding pass ማውጣት እምቢ አላቸው፣ የአየር መንገዱ ሰራተኞች ያሉኝ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮጵያ መጓዝ እንደማልችል ነው" ብለው ለመሠረት ሚድያ የተናገሩት አቶ ልደቱ ዋሽንግተን ወደሚገኘው ኤምባሲ ስልክ ቢደውሉም ጥሪ የሚያነሳ ማሽን እንጂ የኤምባሲው ሰራተኖችን ማነጋገር እንዳልቻሉ ጠቅሰዋል።

"ወደ ሀገሬ መሄድ ማንም ሊከለክለኝ አይችልም፣ ሀገሬ ከሄድኩ በኋላ ግን ማሰር ይችላሉ። በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል" ያሉት ፖለቲከኛው ከአመታት በፊት ለህክምና ከሀገር ሲወጡ ከልክሏቸው እንደነበር፣ አሁን ደግሞ ሊመለሱ ሲፈልጉ መከልከሉ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ጨምረው ተናግረዋል።

"መሄድ አለብኝ፣ በመብቴ ጉዳይ አልደራደርም። ጠበቆችም እያነጋገሩኝ ነው፣ በአቪዬሽን ህግ ሊከለክሉኝ እንደማይችሉ ተነግሮኛል" በማለት ወደ ሀገር ቤት በመመለስ በሀገራቸው የፖለቲካ ምህዳር ላይ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ቁርጠኛ አቋም እንዳላቸው ለሚድያችን ተናገረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአርማውን ቀለም የመቀየር ፍላጎትና እቅድ እንደሌለው ለመሠረት ሚድያ አሳወቀ

- የድርጅቱ አዲስ አጥር ላይ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ የሰፈረው አርማ መልሶ ሊቀባ መሆኑ ታውቋል

(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ በቪ አይ ፒ መግቢያ አካባቢ ባሰራው አጥር ላይ የሚታወቅበት አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለም ቀርቶ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ አርማው (ሎጎው) ተቀብቶ በመመልከታቸው የተለያየ አስተያየት ሲሰነዝሩ ተስተውሏል።

አንዳንዶች አየር መንገዱ ቀስ በቀስ የአርማውን ቀለም እየቀየረ እንደሆነ የገመቱ ሲሆን ድርጊቱን በተለያየ መልኩ ሲገልፁት ታይቷል።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ አየር መንገዱን ያነጋገረ ሲሆን ተቋሙ አርማውን የመቀየር ፍላጎትና እቅድ እንደሌለው አሳውቋል።

"ይሄ የእኛ እቅድም፣ ፍላጎትም አይደለም" ያሉን አንድ የአየር መንገዱ ሀላፊ አዲሱ አጥር በአረንጓዴ ብቻ የተቀባው ገፅታውን 'ቀለል ያለ' እንዲሆን ለማድረግ ነው ብለዋል።

"በዚህ ዙርያ ተወያይተንበታል፣ ብዙ ግርታም እንደፈጠረ አስተውለናል። ወደቀደመው እና ወደ ኦፊሴላዊው የአርማ ቀለሞች መልሶ በቅርቡ ይቀባል" በማለት አስተያየት ሰጥተዋል።

አንድ ሌላ የዘርፉ ባለሙያ በሰጠን አስተያየትም አንዳንድ ግዜ ባለ ቀለም ሎጎዎች ቀለል ያለ መልክ እንዲኖራቸው ሲፈለግ ቅርፃቸውን ጠብቀው ቀለማቸው ሊቀየር እንደሚችል ጠቁሟል።

"ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በታላቁ ሩጫ ቲሸርቶች ላይ ያለውን ሎጎ ብናይ ወይ ነጭ ወይ ሌላ ቀለም ነው፣ አላማው ዲዛይኑ የማይረብሽ እና ቀለል ያለ እንዲሆን ነው። ይህ አሰራር እንደ አሜሪካ ባሉ ሀገራት በጣም የተለመደ አሰራር ነው" በማለት ሙያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መቃረቡን ተከትሎ አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑ ታወቀ

- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል

(መሠረት ሚድያ)- በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።

ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።

ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።

"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።

"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
በአየር መንገድ ግቢ ውስጥ ከአመራሮች እውቅና ውጪ ተነሳ የተባለው ፎቶ በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ

(መሠረት ሚድያ)- ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።

የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።

ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ  27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።

የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።

በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም። 

ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።

በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
ከ890 በላይ እስረኞች በምግብ እና ውሀ ብክለት ታመሙ፣ ሟቾችም እንዳሉ ተሰምቷል

(መሠረት ሚድያ)- በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ 'ጮሬሳ' ተብሎ በሚጠራው ካምፕ ውስጥ ከ890 በላይ የፖለቲካ እስረኞች በምግብ እና በውሃ ብክለት ምክንያት መታመማቸው ታውቋል።

መሠረት ሚድያ ከእስረኞች ቤተሰቦች የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ እስረኞች መሞታቸውም ተረጋግጧል።

በሽታው የተቀሰቀሰው በዚህ ሳምንት የካቲት 6/2017 ዓ/ም መሆኑን የተናገሩት የታሳሪ ቤተሰቦች ለእስረኞቹ የሚቀርበው ውሃ ከወንዝ እየተቀዳ በመሆኑ ለበሽታው ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ብለዋል።

ወደ እስረኞች ካምፕ ከፌደራል ፖሊስ እና ከመከላከያ ሰራዊት አባላት ውጭ መግባት የተከለከለ በመሆኑ  የሕክምና አገልግሎት ማገኘት እንዳልቻሉም ቤተሰቦቻቸው ጨምረው ተናግረዋል።

እስረኞቹ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውን የፋኖን ኃይል ትደግፋላችሁ በሚል ከመስከረም ወር ጀምሮ ከተለያዩ የአማራ ክልል ወረዳዎች በማሰባሰብ ከኮምቦልቻ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኛው ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

ከእስረኞቹ ውስጥ 220ዎቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ዋስትና የተፈቀደላቸው ቢሆንም ታሳሪዎቹን የተረከበው የፌደራል ፖሊስ እስረኞቹን መልቀቅ የሚችለው መከላከያ እንጂ ፍርድ ቤት አይደለም በሚል ሊለቃቸው ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል ተብሏል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
አንዳንድ እድሜያቸው የገፋ መኪናዎች ወደ ቦሌ አቅጣጫ እንዳይንቀሳቀሱ እየተደረጉ እንደሆነ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ከአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ጋር በተያያዘ አንዳንድ እድሜ ጠገብ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ቦሌ አቅጣጫ የመንቀሳቀስ እገዳ እየተደረገባቸው እንደሆነ ታውቋል።

ከባለፈው አርብ እለት ጀምሮ በርካታ የእነዚህ ተሽከርካሪዎች ባለቤቶች ለመሠረት ሚድያ ባደረሱት ጥቆማ ከቦሌ ብስራስ፣ ቦሌ አትላስ፣ ከአራት ኪሎ እና ከኡራኤል አቅጣጫዎች በመነሳት ወደ ዋናው የቦሌ መንገድ (በኦፊሴላዊ አጠራሩ የአፍሪካ ጎዳና) ሲጓዙ በትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እንዲመለሱ መታዘዛቸውን አስረድተዋል።

"ዝርዝር የማስፈፀሚያ ህግ ባልወጣበት እንዲህ አይነት እገዳ መጣሉ የህግ የበላይነት አለመኖሩን ማሳያ ነው" ያሉ አንድ እገዳው ያጋጠማቸው አሽከርካሪ ድርጊቱን ኮንነዋል።

ሌላ አሽከርካሪ ደግሞ "አላማው ምንድነው? ዜጎቻችን በሙሉ የሚነዱት ዘመናዊ ተሽከርካሪ ነው የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ይሆን?" በማለት ጥያቄያቸውን ሰንዝረዋል።

እገዳውን እየጣሉ ያሉት የትራፊክ ፖሊሶች ዝርዝር ማስፈፀምያ ደርሷቸው ይሆን ወይስ በራሳቸው ተነሳሽነት የፈፀሙት ነው የሚለውን ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

በአዲስ አበባ አሮጌ መኪናዎች በተለይ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው እንደሚችል በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ አመት ገደማ ነበር።

በወቅቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ የአሮጌ መኪና ባለቤቶች መኪናቸውን መቀየር ካልቻሉ በለሙ የኮሊደር መንገዶች ላይ እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው ይችላል ብለው ለሚድያዎች ተናግረው ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
መንግስት ንብረታቸውን ሊወስድ እየተዘጋጀ መሆኑን አቶ ልደቱ አያሌው አስታወቁ

(መሠረት ሚድያ)- ባሳለፍነው ሰኞ ጠዋት ከአሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ለመጓዝ በአትላንታ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ቢገኙም እንዳይሳፈሩ የተደረጉት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው መንግስት ንብረታቸውን ሊወስድ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቁ። 

ፖለቲከኛው ለበርካታ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ተቋሟት ዛሬ በፃፉት እና ለመሠረት ሚድያ በቀጥታ ባጋሩት ደብዳቤያቸው ላይ "ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ሀገር መመለስ እንደማልችል በአንድ ስብሰባ ላይ በይፋ ተናግረዋል" ብለዋል።

አቶ ልደቱ አክለውም ወደ ሀገር ቤት እንዳይመለሱ የታገዱት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ወደ ኢትዮጵያ በሚበሩ አየር መንገዶች ጭምር መሆኑን ጠቁመዋል።

"ይህ ድርጊት የሚያሳየው የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም ተፃራሪ ድምፆች ለማፈን ቁርጠኛ መሆኑን ነው። እነዚህ ድርጊቶች እየተፈፀሙ ያሉት ካለ ምንም የህግ አግባብ ስለሆነ በግዜው ካልተስተካከለ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ ጭምር ሊፈፀም ይችላል" በማለት በደብዳቤያቸው ላይ አስፍረዋል።

አቶ ልደቱ ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ ዜግነት እንደሌላቸው አፅንኦት ሰጥተው በደብዳቤያቸው ላይ ያስረዱ ሲሆን የኢትዮጵያ ህገ-መንግስትም ሆነ ሌሎች የሀገሪቱ ህጎች ዜጎች ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደማይችሉ የሚገልፅ ድንጋጌ እንደሌላቸው አንስተዋል።

የአቶ ልደቱ ደብዳቤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን፣ የአፍሪካ ህብረትን፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን፣ ሂውማን ራይትስ ዋችን እና የአሜሪካ ኤምባሲን ጨምሮ ለ32 ድርጅቶች የተፃፈ ነው።

"ወደ ሀገሬ መሄድ ማንም ሊከለክለኝ አይችልም፣ ሀገሬ ከሄድኩ በኋላ ግን ማሰር ይችላሉ" የሚሉት ፖለቲከኛው ከአመታት በፊት ለህክምና ከሀገር ሲወጡ መንግስት ከልክሏቸው እንደነበር፣ አሁን ደግሞ ሊመለሱ ሲፈልጉ መከልከሉ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ባሳለፍነው ሰኞ ለመሠረት ሚድያ ተናግረው ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
ባሳለፍነው ሳምንት ሸራተን ሆቴል አቅራቢያ ከፍተኛ የፍንዳታ አቅም ያለው ፈንጂ ተገኝቶ እንደነበር ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተማ ሸራተን ሆቴል አቅራቢያ ከፍተኛ የፍንዳታ አቅም ያለው ፈንጂ በአሰሳ ወቅት ተገኝቶ እንደነበር ታውቋል።

እሮብ እለት፣ ማለትም የካቲት 6/2017 ዓ/ም ምሽት አምስት ሰአት ላይ ከቤተመንግስት አቅጣጫ ወደ ሸራተን መውረጃ ጠመዝማዛው መንገድ አቅራቢያ TNT የተባለ ፈንጂ መገኘቱን የፀጥታ ምንጮች ለመሠረት ሚድያ አረጋግጠዋል።

የፈንጂው መገኘት አሁን ላይ ከተጠናቀቀው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ጋር የተገናኘ ይሁን አይሁን እስካሁን ይፋ አልተደረገም።

ሚድያችን በዚህ ዙርያ ተጨማሪ መረጃ ከፌደራል ፖሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ የጠየቀ ቢሆንም "መረጃው የለንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

ይሁንና የፌደራል ፖሊስ ባሳለፍነው ሀሙስ፣ ወይም ፈንጂው ከተገኘበት ከአንድ ቀን በኋላ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት ባቀረበው ክስ 13 ሰዎችን የአፍሪካ ህብረት የሚታደሙ ሰዎችን ለማጥቃት በማሴር ክስ መስርቷል።

ክሱ በግልፅ ድርጊቱ ይህ ሸራተን አካባቢ ጋር ከተገኘው ፈንጂ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ባይጠቅስም "የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ አባል ሀገራት እና ከተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ስብሰባው ላይ ለመታደም በሚመጡ አመራሮች እና ጋዜጠኞች ላይ የሽብር ጥቃት እንዲፈፅሙ" ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ይገልፃል።

በዚህ ዙርያ የመንግስት አካላት መግለጫ ሊሰጡ እየተዘጋጁ እንደሆኑ የደረሰን ተጨማሪ መረጃ ይጠቁማል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት በጅምላ የታሰሩ ወጣቶች እስከ 20 ሺህ ብር ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- እሁድ እለት የተጠናቀቀው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ባሉት ቀናት አዲስ አበባ ውስጥ የታሰሩ ወጣቶች ገንዘብ ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታውቋል።

እነዚህ ልደታ አካባቢ በአፈሳ መልክ የታሰሩ ወጣቶች ጦር ሀይሎች አካባቢ ታስረው የቆዩ ሲሆን አሁን ላይ እስከ 20 ሺህ ብር እየከፈሉ፣ ሌሎቹ ደግሞ ለህዳሴ ግድብ የ2 ሺህ ብር ቦንድ እንዲገዙ እየተደረጉ መለቀቃቸውን መሠረት ሚድያ ከታሳሪዎቹ እና ቤተሰቦቻቸው ሰምቷል።

"በስብሰባው ምክንያት ተሰብስባቹ ተቀመጣችሁ ተብለው ቁጭ ብለው ከሚበሉበት በረንዳ የታፈሱት ባለፈው እሮብ ነበር" የሚለው አንድ የመረጃ ምንጫችን ከትናንት ጀምሮ የተወሰኑት እየተፈቱ መሆኑን ተናግሯል።

"ቦንድ ያልገዙት ተቀምጠው እኛ ወጣን" ያለን ደግሞ ለቦንድ 2 ሺህ ከፍሎ ነፃ የወጣ ግለሰብ ነው።

ከሰሞኑ እንደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያሉ ተቋማት ከእስር ተፈቺዎችን እና ተገልጋዮችን ለማገልገል ወይም ከእስር ለመልቀቅ የ 500 ብር የህዳሴ ግድብ ቦንድ በግዴታ እያስገዙ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
በምሥራቅ ጎጃም በድሮን ጥቃት ሕፃናትን ጨምሮ 16 ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች እና ቤተሰቦች ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ም. ተያይዘው በተሠሩ አራት ቤቶች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቤተሰቦች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቱ በዞኑ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ (ሐሙስ ገበያ) በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሐሙስ ረፋድ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በሦስት ሱቆች እና ሻይ ቤት ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

"[ድሮን] ስትዞረን ነበር" ያሉ አንድ የዓይን እማኝ ጥቃቱ ከደረሰበት ስፍራ በግምት 100 ሜትር ርቀት ላይ እንደነበሩ ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች መንገድ ላይ ሲጫወቱ የነበሩ ህፃናት፣ ገበያተኞች እና ሻይ እየጠጡ የነበሩ ሰዎች ናቸው ብለዋል።

ከፍተኛ ፍንዳታ መፈጠሩን የሚናገሩት እማኙ፤ ወዲያው "አካባቢውን አቧራው፤ የቤቱ ፍርስራሽ በጭስ" እንዳፈነው እና ድንጋጤ እና ግርግር እንደተፈጠረ ገልፀዋል።
ሌላ የዓይን እማኝም በፍንዳታው አካባቢው በአቧራ ጭስ መሸፈኑን ጠቅሰው፤ በስፍራው ለመተያትም አስቸጋሪ እንደነበር ተናግረዋል።

በደቂቃዎች ውስጥ ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው ቤቶች ደርሰው የቆሰሉ ሰዎችን እንዳወጡ እና አስከሬን እንዳነሱ የተናገሩት ሌላ የዓይን እማኝ "የሚጫወቱ ህፃናት እና ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለዋል።

Via BBC News Amharic

@MeseretMedia
ኮምቦልቻ አቅራቢያ በእስር ላይ የነበሩ ከ890 በላይ እስረኞች በዛሬው እለት ተለቀቁ

(መሠረት ሚድያ)- በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ 'ጮሬሳ' ተብሎ በሚጠራው ካምፕ ውስጥ ከ890 በላይ የፖለቲካ እስረኞች በምግብ እና በውሃ ብክለት ምክንያት ታመው እንደነበር መሠረት ሚድያ የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ መዘገቡ ይታወሳል።

ሚድያችን ከእስረኞች ቤተሰቦች በወቅቱ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ እስረኞች ህይወታቸው አልፏል።

አሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በዚህ ካምፕ ውስጥ ታስረው የነበሩ ሁሉም እስረኞች በዛሬው እለት ተለቀዋል፣ የተለቀቁበት ምክንያትም ግን እንዳልተነገራቸው ታውቋል።

በሽታው በካምፑ ውስጥ የተቀሰቀሰው የካቲት 6/2017 ዓ/ም መሆኑን የተናገሩት የታሳሪ ቤተሰቦች ለእስረኞቹ የሚቀርበው ውሃ ከወንዝ እየተቀዳ በመሆኑ ለበሽታው ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ብለው ነበር።

አሁን ነፃ የሆኑት ግለሰቦቹ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውን የፋኖን ኃይል ትደግፋላችሁ በሚል ከመስከረም ወር ጀምሮ ከተለያዩ የአማራ ክልል ወረዳዎች በማሰባሰብ ከኮምቦልቻ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኛው ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታስረው እንደነበር ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

ከእስረኞቹ ውስጥ 220ዎቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ዋስትና የተፈቀደላቸው ቢሆንም ታሳሪዎቹን የተረከበው የፌደራል ፖሊስ እስረኞቹን መልቀቅ የሚችለው መከላከያ እንጂ ፍርድ ቤት አይደለም በሚል ሊለቃቸው ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል እንደነበር ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች ከነገ ጀምሮ የብልፅግና ፓርቲ ማስታወቂያን በግዴታ እንዲያሳዩ ሊደረጉ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች እና ህንፃዎቻቸው ላይ የማስታወቂያ ስክሪን የገጠሙ ባለሀብቶች ከነገ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ መልእክት የሆኑ ምስሎችን እና ጽሁፎችን በአስገዳጅነት እንዲያሰራጩ ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ታውቋል።

በራሳቸው ወጪ አውጥተው የሰሩትን የዲጂታል ስክሪን ለፖለቲካ ፓርቲ መልዕክት ማስተላለፊያ መደረጉ በህዝብ ዘንድ ለአንድ ወገን ያደሉ ወይም የፓርቲ አባል እንደሆኑ እንዳይወሰድባቸው የሰጉት ግለሰቦቹ አማራጭ እንዳጡ እና አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ ተናግረዋል።

የብልጽግና ሹሞች ቁጣ በተቀላቀለበት መልዕክት በአስገዳጅነት ማስታወቂያውን ከነገ ጀምሮ ለማሰራጨት እንዳስገደዷቸው ጨምረው ተናግረዋል።

"ከሳምንት በፊት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መሪዎች ሲመጡ 'እንኳን ደህና መጣችሁ' የሚልና ስለ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ተመሳሳይ ትዕዛዝ ተላልፎ  ያስተላለፍነው የፖለቲካ ይዘት የሌለው በመሆኑ ነበር" የሚሉት የማስታወቂያ ድርጅቶቹ "አሁን የታዘዝነው የፖለቲካ ፓርቲ  መልእክት ገበያው በተዳከመበት መሀል ከህዝቡ ጋር እንዳያቃቅረን ስጋት አለን" ብለዋል።

በሌላ በኩል በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ወቅት በርካታ የመኪና ኪራይ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን በነፃ ለስብሰባው አገልግሎት እንዲሰጡ ተገደው እንደነበር ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

"ቢዝነስ በተዳከመበት በዚህ ወቅትም ይሁን ድሮ በአመት አንዴ ጥሩ ስራ የምንሰራው እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲመጡ ነበር" የሚሉት የመኪና አከራዮቹ አሁን ግን እሱንም በግዴታ እንደተነጠቁ እና መኪናዎቻቸው የተመለሱላቸው ስብሰባው ካለቀ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia
2025/02/25 07:32:49
Back to Top
HTML Embed Code: