Telegram Web
ሰኔ ፲፪ /12/


በዚች ዕለት የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ ላሊበላ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ።

ይህንንም ቅዱስ ወላጆቹ በወለዱት ጊዜ እግዚአብሔርን በመፍራትና በበጎ ሥራ ሁሉ አሳደጉት ። አድጎ አካለ መጠን በአደረሰ ጊዜ ታላቅ ወንድሙ ንጉሥ ቀናበት መልእክተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስመጣው ምክንያትም ሽቶ ከሦስት ሰዓት እስከ ሰባት ሰዓት እንዲገርፉት አዘዘ ።

ከዚህም በኋላ በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ በአቆሙትም ጊዜ የደረሰበት ጉዳት እንደሌለ አይተው ንጉሡና መኳንንቶቹ ሁሉ አደነቁ የእግዚአብሔር መልአክ ከግርፋት ሠውሮታልና ። ከዚህ በኋላም ወንድሙ ንጉሥ በአንተ ላይ ስለአደረግሁት ክፉ ሥራ ወንድሜ ሆይ ይቅር በለኝ ብሎ ለመነውና እርስ በርሳቸው ታረቁ ።

ከዚህ በኋላም እግዚአብሔር መንግሥትን አወረሰው ። ክብር ይግባውና ጌታችንም የፍቅሩን ጽናት በአየ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት ወደ እርሱም ወደ ሰማያት አወጣው ዐሥሩን አብያተ ክርስቲያንም እንዴት እንደሚሠራቸው አሳየው እነርሱም ሥራቸው የየራሳቸው የሆነ ልዩ ነው ተመልሶም መንፈስ ቅዱስ እንደአራቀቀው በአስደናቂ ጥበብ አነፃቸው ። እሊህንም አብያተ ክርስቲያናት አንፆ በፈጸመ ጊዜ መንግሥቱን ለወንድሙ ልጅ አወረሰ ።

ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መቶ ብዙ ቃልኪዳን ገባለት ቅዱስ ላሊበላም ጌታችንን እያመሰገነ በምድርላይ ወድቆ ሰገደ ። ጌታችንም ሰላምታ ሰጥቶት በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ። ከዚህም በኋላ ጥቂት ሕማም ታሞ በሰላም አረፈ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

አዘጋጅ:-በለጠከበደ(የጣፈጡልጅ)አላቲኖስ

╔​✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╗
#መልካም_የበረከት_በዓል
╚✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╝ አላቲኖስ
"ሚካኤል እምመላእክት መኑ ከማከ ክቡር ወመኑ ከማከ ልዑል!"
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
🗓⚪️#አንድ_ጥያቄ

●✥ ከመንፈስ ፍሬዎች መካከል ቀዳሚነትን የሚይዘው የትኛው ነው ●✥
አይናፋር ነት ይዟት የቆየችው "ቅዱስ ትውፊት " የሕትመት ጊዜዋን ጨርሳ ለመውጣት ተዘጋጅታለች እናተም በማንበብ በመግዛት አላምዷት Girum G Abebe ከምጽአት በፊት መጥታለች ኃላፊነቱ የእናተ ነው ክቡር

በቅርብ ቀን ይጠብቁን!
ዋና አከፋፋይ ሰርዲኖን መጽሐፍ ቤት

በተለየ ቅናሽ መንፈሳውያት መጻሕፍትን ከስርዲኖን የራስዎ ያድርጉ ፈጥነው ይጎብኙን!!

📍 ማኅበረ ቅዱሳን ፊት ለፊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚገኝበት አዲሱ የቤተክህነት ሕንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን ይጎብኙን።
🤳 0910934578

የሚድያ አማራጮቻችን
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61561651813051

Instagram
https://www.instagram.com/sardinon_books/profilecard/?igsh=MThidjdrc3FnNnpqag==

telegram
https://www.tgoop.com/Sardinon

tiktok
https://www.tiktok.com/@www.serdinon?_t=ZM-8xHzomiNYVc&_r=1

#ሰርዲኖን #መጻሕፍት #ዓውደ_ርዕይ #ቅናሽ
Channel photo updated
╔​✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╗
#ወጥታለች_ደርሳለች_
╚✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╝ አላቲኖስ
╔​✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╗
#አዲስ_መጽሐፍ_በገበያ__ላይ
╚✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╝ አላቲኖስ

#ቅዱስ_ትውፊትን በሰርዲኖስ የመጽሐፍ መደብር ይገኛል
በበለጠ ከበደ (የጣፈጡ ልጅ) አላቲኖስ የተዘጋጀው ❝ቅዱስ ትውፊት ❞ የተሰኘው መጽሐፍ በመደብራችን ይገኛል ይጎብኙን!!

መንፈሳውያት መጻሕፍትን ከሰርዲኖን በቅናሽ የራስዎ ያድርጉ!!

📍 ማኅበረ ቅዱሳን ፊት ለፊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚገኝበት አዲሱ የቤተክህነት ሕንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን ይጎብኙን።
🤳 0910934578

    የሚድያ አማራጮቻችን
  Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61561651813051

  Instagram
https://www.instagram.com/sardinon_books/profilecard/?igsh=MThidjdrc3FnNnpqag==

telegram
https://www.tgoop.com/Sardinon

tiktok
https://www.tiktok.com/@www.serdinon?_t=ZM-8xHzomiNYVc&_r=1

#sardinon #bookstore #orthodoxbooks #ethiopia
እጅግ ድንቅ መንፈሳዊ መጽሐፍ እንሆ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሦስት የሃይማኖት መመሪያዎች አሏት ፤ ምእመኖቿ እምነትን ከምግባር ጋር አስተባብረው እንደ ሕጉና ትእዛዙ እንዲኖሩ በአምልኮተ እግዚአብሔር እንዲጸኑ የምትመራባቸው ሦስት የሃይማኖት መመሪያዎች አሏት፡፡

ዶግማ Dogma (መሠረተ እምነት)
ቀኖና Canon (መሠረተ ሥርዐት)
ትውፊት Tradition (ቅብብል)
ትውፊት “አወፈየ፤ አቀበለ፣ ሰጠ” ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ቅብብል፣ ውርስ ማለት ነው፡፡ ትውፊት
ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ቀጥሎ ስለ ክርስትና የሚነግረን እና ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳን ሐዋርያትና ከአባቶቻችን  የተቀበልነው ትምህርት ነው፡፡ ትውፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተጻፉ ነገር ግን ፈጽሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ ያልሆኑ ትምህርቶችን፣ ታሪኮችን፣ ክርስቲያናዊ ሥርዐት፣ ሥርዐተ አምልኮ ልምምዶችንና ጸሎቶችን የያዘ  ነው።

ቅዱስ ባስልዮስ (ST. BASIL THE GREAT) እንዲህ ይላልለ ምሳሌ
የመጀመሪያውንና አጠቃላይ ምሳሌን ብንወስድ “በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የታመኑትን የመስቀል ምልክት ማድረግን በጽሑፍ ያስተማረን ማን አለ?” በትውፊት አይደል ያገኝነው ።

ስለ ቅዱስ ትውፊት በስፋት የያዘ ጥልቅ መጽሐፍ  ያንብቡ ያስነብቡ መንፈሳዊ በረከት ያገኙበታል ።
2025/07/09 00:09:59
Back to Top
HTML Embed Code: