Telegram Web
ሩሲያ ጸረ ኑክሌር ኃይሏ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዘች

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዙ፡፡

ፑቲን ከገቡበት የዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከምዕራባዊ ሃገራት ጋር ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ጦሩ በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንዲሆን ያዘዙት፡፡

ዛሬ እሁድ ከከፍተኛ ባለስልጣናቶቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል የሆኑ ሃገራት ጠንከር ያለ መግለጫ እያወጡ መሆኑንና ማዕቀቦችን እየጣሉ በመሆኑ ጸረ ኑክሌር ኃይሉ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዋል፡፡

ፑቲን ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ማዕቀብን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎችን በሚወስዱና ጣልቃ በሚገቡ ሃገራት ላይ ጠንከር ያለ የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስዱ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል፡፡

አል ዐይን

@nidatube
Congratulation 🎉🎉🎉
هنيأ لكم
እንኳን ደስ ያለን ፣ እንኳን ደስ ያለዎ

ሼይኻችን ዶ/ር ሙሐመድ ሐሚዲን አብዱሰመድ በታሪክ ምርምርና ጥናት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ በማጠናቀቃቸው እንኳን ደስ አለዎ ለማለት እወዳለው

ሼይኽ መሐመድ ሀሚዲን ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትልቅ ተስፋ የሚጣልባቸው ታላቅ አሊም ናቸው::

ለሃገራቸውን ሙስሊሞች ኢስላማዊ እውቀት እንዲስፋፋ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን እየተቀዛቀዘ የመጣውን የቂርዓት ክፍተት ለመሙላት የዳዕዋ ቲቪን በመመስረት ለመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም በየቤቱ ኢስላማዊ ትምህርቶችን በቋሚነት እንዲከታተል ማድረግ ችለዋል::

ከዚህ በበለጠም የኡለሞቻችን በሞት እና በተለያዩ ችግሮች መመናመን አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በመረዳት ተተኪ አሊሞችን እና ዱዓቶችን ለማፍራት ትልቅ ኢስላማዊ ተቋም ለመገንባት ታላቅ ፕሮጀክት ነድፈው ወደ ተግባር በመግባት ለኡማው ከሚያስብ ታላቅ አሊም የሚጠበቅ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ::

ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል ታላላቅ ስራዎችን በእድሜያቸው ለመስራት እየለፉ የሚገኙ እኚህን የመሰሉ ታላቅ አሊም በውስጣችን መገኘታቸው ለሁላችንም ትልቅ እድል ሲሆን በእውቀታቸው ከመጠቀም በተጨማሪ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተጨንቀው ለማሳካት እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፕሮጀክቶቻቸውን ማገዝ ከሁላችን ይጠበቃል::

ሼይኻችን ዶ/ር መሐመድ ሀሚዲን የዶክትሬት ድግሪያቸውን በስኬት በማጠናቀቃቸው በድጋሚ እንኳም ደስ አለዎት እያልኩኝ አላህ ረጅም እድሜ ከጤና ጋር እንዲለግሶት ፣ኡማውም ከእርሶ ብዙ የሚጠቀም ያድርገው ዘንድ መልካም ዱዓዬ ነው

@nidatube
በየመን አንድ ዐይን ያለው ህፃን ተወለደ
ህጻኑ በምድር ላይ በህይወት መቆየት የቻለው ለ7 ሰዓታት ብቻ ነው

አለማችን ብዙ ለማመን የሚከብዱ አስደናቂ ነገሮችን እያስተናገደች ሲሆን፤ ከሁለት ቀናት በፊትም በየመን የተፈጠረው አዲስ ክስተት በርካቶችን እያነጋገረ ነው።

ክስተቱ የተፈጠረው በየመኗ አል-በይዳ ግዛት በምግተኘው የራዳአ ከተማ ሲሆን፤ በተከማዋም በሚገኝ ሆስፒታል አንድ ዐይን ያለው ህፃን መወለዱ ተሰምቷል።

በአል-ሂላል እስፔሻላይዝድ ሜዲካል ሆስፒታል የህክምና ምንጮች እንደገለፁት፤ ህጻኑ ከሁለት ቀናት የተወለደ ሲሆን፤ ከተወለደ ብዙም ሳይቆይ ህይወቱ ማለፉን ጠቁመዋል።

ህፃኑ ወደ ማሞቂያ ክፍል ከተወሰደ ከሰባት ሰዓታት በኋላ ህይወቱ ማለፉን የሆስፒታሉ ምንጮች አስታውቀዋል።

አል ዐይን

@nidatube
ዝነኛው አሊ ቢራ ከእንግዲህ ወደ ዘፈን አልመለስም ፊቴን ወደአላህ አዙሪያለሁ አለ። አላህ ይቀበልህ

"ዳግም ሁለተኛ ወደ ዘፈን አልመለስ አላህ ተውበቴን ይቀበለኝ" ብሏል አሊ ቢራ

አልሀምዱሊላህ ፣ዱኣ አድርጉለት

@nidatube
ለመሸፋፈን ብንለፋ አልሸፈን ያለን ነውር ዛሬም ራሱን ገልጧል

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የሞቱትን ለጀነት፣ ለቆሰሉት ፈጣን ፈውስ፣ ንብረታቸውን ላጡ የተሻለ ካሳ ከአላህ እማፀናለሁ

መተባበርና መተዛዘን በሚጠበቅባቸው ግዚያትና ቦታዎች ማጥቃት ቀላል የሆነላቸው ድንገተኛ ክስተት ሆኖ አይደለም

በቀላሉ ሊቆም የሚችልን ችግር እንደሰደድ እሳት ያስፋፉት ከአቅም በላይ ሆኖ አይደለም፣

በመቃብር ስፍራ ላይ ያስጀመሩትን ጥቃት ወደመኖሪያ ቤት፣ የንግድ ማእከላትና መሳጂዶች ያዛመቱት ድንገት ከጃቸው ወጥቶ አይደለም

ትንሽ መስለው ሰፊውን ህዝብ የሚያውኩት ክፋታቸው በቁጥራቸው ብቻ የሚገለፅ ሆኖ አይደለም

ብዙዎቹ ነገሮች ሁሌ ለመስጠት እንደምንሞክረው ቀና መላምት፣ ለህዝቦች አብሮነት እንደምንለፋው አልሳካ ያሉት ለመሸፋፈን የምንጥረው ነውር ራሱን ደግሞ ደጋግሞ እየገለጠ ነው።

ይህንን ነውር የጎንደር ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ሊጠየፈው ይገባል። ከውስጡ የበቀሉ የነውረኛ ሥብስቦችን ነቅሎ ለመጣል የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ቢከፍል ለጎንደር ህዝብ የቆየ ሰላማዊነትና ለነገዋ ጎንደር እፎይታ እጅግ የሚገባ አንገብጋቢ ስራ ነው። የአካባቢው ባለስልጣናትና የክልሉ መንግስት አካባቢውን እና ክልሉን እረፍት የለሽ ሁከት ውስጥ እየከተቱ ክልሉን የነውረኞች መሸሸጊያ እንደሆነ የሚሰሩትን ሳያቃልል እና ምንም ምክንያት ሳይደረድር ሊያስቆምና ሊቀጣ ይገባል። አመራሩ የሚወስደው የማያዳግም እርምጃ ለሰላሙ ብቻ ሳይሆን ነውረኞች በአመራሩ ውስጥ ሰርገው አለመግባታቸውን ማስተማመኛ የሚሰጥ ነው።

ነውረኞች የመጨረሻ ግባቸው የህዝባችን ቋንቋ እና ምግባር በነሱ ደረጃ ወርዶ የነሱ ህግ ገዢ እንዲሆን ነው የሚሹት። ትንሽ ቢሆኑም በነውራቸው ብዙውን ሊበክሉ እንደሚችሉ በማመን ወደሜዳቸው ነው ሊጠሩን የሚመኙት፣ እረፍታቸው የሚመነጨው አለመረጋጋት በመፍጠር ስለሆነ ከሰከነ መንፈሳዊነትና ከተረጋጋ አውድ እንድንወጣ ነው የሚለፉት

ለነርሱ የምንደረድረው የይሆናል ምክንያት አልቆብን ግልፁን መናገር ብንጀምርም ያስነሱትን የነውር መንገድ በጎንደርም ሆነ በተቀረው አካባቢ እንዲሰፍን ግን ፈፅሞ አንፈቅድላቸውም። የተቀረውን አካባቢ ሰላም እንዲጠበቅ እየሰራን እነርሱን ነቅሎ ለመጣል ከጎንደር ህዝብና የሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአካባቢው አመራሮች፣ ከክልሉና ከፌዴራል መንግስት ጋር በትብብር እንሰራለን። እንደምናሸንፋቸውም ሙሉ እምነት አለን!

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ
ሚያዝያ 18/2014
በጎንደር ሙሰሊም ላይ ያነጣጠረ ግደያ የሁለት ሃይማኖቶች ግጭት ለማስመሰል የምትጋጋጡ ሚዲያዎች ተቆጠቡ ፣ ጥቃቱ ሙሰሊም ላይ ብቻ የተደረገ የአንድ ወገን ጥቃት ነው።

share ...share...share
🚩 የጎንደር አሥተዳደር መስጊድ ላይ ድራማ መሥራትን መርጧል!
—————————
.ኢስሀቅ እሸቱ

የጎንደር አሥተዳደር በታጠቁ አሸባሪዎች ደሙ ሲፈስ፣ አጥንቱ ሲከሰከስ የቆየውን የጎንደር ሙስሊም ከለላ በመስጠት ፈንታ ድራማ ይሠራበት ጀምሯል። ጌሾ ሠፈር አቅራቢያ የሚገኘውና በ3 አቅጣጫ በጥይት ሲደበደብ የከረመው መስጊድ ላይ አዲስ ❝ጂሐዳዊ ሐረካት❞ መሰል ድራማ መሥራትን መርጧል።
.
በትናንትናው ዕለት በመስጊዱ ጀርባ ባሉ ቤቶች በኩል ገጀራዎችን እና መሣሪያዎችን ከውጭ በማስገባት ❝መስጊድ ውስጥ ተገኘ❞ በሚል የሐሰት ዶኩመንተሪ ሲቀርጹ መዋላቸውን ማወቅ ተችሏል። ለድማራው ግብዓት እንዲሆንም የሃይማኖት አባቶችን በማምጣት ❝ሙስሊሙ ጥፋቱን አምኖ ቤተ ክርስትያንን ይቅርታ ይጠይቅና ሠላም ይውረድ ይህንን ካደረጋችሁ የዒድ ሶላት እንድትሰግዱ ይፈቀድላችኋል❞ የሚል እጅግ አሳፋሪ ጥያቄ አቅርበዋል።
.
መንግሥት ❝በቁጥጥር ሥር ውለዋል❞ ካላቸው 380 ሰዎች አብዛኛዎቹ ሙስሊሞች መሆናቸውንም ማወቅ የተቻለ ሲሆን ልክ በሞጣው ጥቃት እንዳደረጉት ሙስሊሙን ራሱ ተጠያቂ ለማድረጎ ቆርጠው እየሠሩ ይገኛሉ።
.
ይህንን ተበዳይን በዳይ አስመስሎ የማቅረብ ነውረኛ ፕሮፓጋንዳ መከላከል የምንችለው እኛው ነን! ሁላችንም ኢ-ሰብዓዊውን በደል በማጋለጥ ከተበዳይ ጎን እንቁም! ሐሽታጎቹን ተጠቅመን እንጻፍ! በዝምታ የምናሣልፋት እያንዳንዷ ሰከንድ በጎንደር ሙስሊሞች አንገት ሸምቀቆው እንዲጠብቅ እንደምታደርግ አንዘንጋ! ሼር በማድረግና በራሳችን በመጻፍ እንረባረብ!
.
#የጎንደርጭፍጨፋ #GondarMassacre #ደባርቅ #ሙስሊምጠልነት #ፋኖ
በጎንደርና በደባርቅ ጥቃት አድራሾች በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር በሲያትል ጠየቀ
@nidatube
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ!
ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት፦
👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም ሆኗል።
@nidatube
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ክርሰቲያን ወንድማችን ጥያቄ ያቀርባል
@nidatube
እጅግ በጣም የሚገርመኝ .......

በአቡ ሀይደር

የሆነን ክልል ይጠቅሱና: በክልሉ የተሰራውን ቤተ ክርስቲያን ለማገዝ ከሙስሊሞች በኩል ይህን ያህል ሚሊየን ተለገሰ፣ ለምርቃቱ ደግሞ ይህን ያህል በሬ ተሰጠ! የሚለውን ዜና እንደጉድ ያሰራጩና: በመጨረሻም:– ይህ ነው ኢትዮጲያዊነት! ይህ ነው ጨዋነት! ይህ ነው አንድነት! በማለት መልክቱን ይቋጩታል።

እኔ የምጠይቀው:– የተወራው ነገር እውነት ከሆነና: የኢትዮጲያዊነት ፀባይ አንዱ መገለጫ: የአንዱን የአምልኮ ቦታ ሌላው በእምነት የማይመስለው ወገኑ: ከቻለ በገንዘብ ካልቻለ ደግሞ የምርቃት ቀን የእርድ ከብት ማቅረቡን ከልብ አምናችሁ ከተቀበላችሁት: እናንተስ የሙስሊሙን መስጂድ ከማቃጠልና ከማፍረስ ውጭ ምን ሰርታችሁ ታውቃላችሁ? በመዲናችን አዲስ አበባ እንኳን: በህጋዊ መንገድ ፍቃድ ያገኘንበትን ቦታ በሰላም እንድንገነባ በዝምታ እንኳ መች ተባብራችሁ ታውቃላችሁ? የቱንም ያህል ቢራራቁም: ህዝቡን ለማነሳሳት ከቤ/ክርስቲያን ጎን መስጂድ ሊሰራ ነው ብላችሁ ረብሻ መቀስቀስ፣ ድንጋይ መወርወር፣ ከታቻለም መሳሪያ መተኮስ መገለጫችሁ አይደለምን? ከአንዋር መስጂድ ውጭ የትኛው መስጂድ ነው ደም ሳይፈስ በሰላም የተገነባው? ወይስ ኢትዮጲያዊ ጨዋነትና አንድነት እናንተን አይመለከትም? ወይስ ጨዋነቱና አንድነቱ የሚሰራው ለቤ/ክርስቲያን ግንባታ ሲሆን ብቻ እንጂ ለመስጂድ ግንባታ ግዜ አይሰራም? ኧረ እንደው በራሳችሁ ድርጊት እንድታፍሩ የሚገስጻችሁ የህሊናም ይሁን የሃይማኖት መካሪ የላችሁም? ለቤ/ክ ግንባታ የሙስሊሙን መሳተፍ የኢትዮጲያዊ ጨዋነት መገለጫ መሆኑ እውነት ከታመነበት: እናንተ ምንም ኢትዮጲያዊ ጨዋነት እንደሌላችሁ መስክራችኋል ማለት ነው። ሙስሊሞች ለቤ/ክርስቲያናችን ለግንባታው እና ለምርቃቱ ይህን አደረጉልን እንጂ እኛ ለነሱ መስጂድ ይህን አደረግንላቸው ብላችሁ የምታወሩት ምንም የላችሁም። አድርጋችሁብን እንጂ አድርጋችሁልን አታውቁምና!!

አል–ሐምዱ ሊላህ ዓለሰ ኒዕመቲል ኢስላም
@nidatube @nidatubebot
የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለምትፈልጉ

በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከ ሰኔ 6-12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡

ስለሆነም ይህን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣7፣13፣14፣20፣21፣27፣28 ) ስለምናደርግ በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ እንድትይዙ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም፡፡
.................
ሼር በማደርግ ያሰተላለፉት
@nidatube
በኢስላም ንጉስም ብትሆን ስትሞት ነጭ ከፈን እንጂ ሌላ ለብሰህ አትቀበርም!

ዛሬ በ 73 አመታቸው መሞታቸው የተገለፀው እና በህዝባቸው ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እንደነበሩ የሚነገርላቸው የተባበሩት አረብ ኢምሬትሶች ፕሬዝደንት ሼይኽ ከሊፋ ቢን ዛይድ (አላህ ይዘንላቸው) ሰርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል::

እጅግ የሃብታም ሃገር መሪ ሆነው ቢቆዩም ሲሞቱ ግን እንደማንኛውም ተራ ሰው ባለ ሶስት ነጭ ከፈን ተጠቅልለው ሰላተል ጀናዛ ተሰግዶባቸው አፈር ውስጥ ተቀብረዋል::

በኢስላም ሁሉም ሰው እኩል ነው:: ንጉስም ሁን፣ የሃገር መሪ፣ ባለስልጣን፣ ባለሃብት ፣ምሁር ፣ደሃ፣ጥቁር ሁን ነጭ ስትሞት የአቀባበርህ ሁኔታ ላይ የምትበላለጥበት መንገድ የለም:: ሃብታም ግድግዳ ውስጥ ደሃ አፈር ውስጥ የሚቀበርበት የቀብር ስነ ስርዓት በኢስላም የለም::

በኢስላም ስትሞት ሃብታም ወይንም መሪ ስለሆንክ ዘመናዊ ሙሉ ሱፍ አልያ የተሽቀረቀረ ሙሉ ልብስ ፣እጅግ ውድ እና ዘመናዊ የሬሳ ሳጥን፣እና ሌሎች አጀባዎች ወዘተ.... እንዲኖርህ አይጠበቅም::

የሃገር መሪ ስለሆንክ ታላላቅ የሃገራት መሪዎች እስኪመጡ ፣ ህዝብ አስክሬኑን እስኪሰናበተው፣ የቀብር ስነ ስርዓቱ ለማከናወን የአደባባይ ድግስ እና የሽኝት ፕሮግራም እስኪካሄድ አስክሬኑ ሳይቀበር ይቆይ የሚባል መርህ በኢስላም የለም::

ማንም ሰው ከሞተ ቶሎ አጥቦ፣በነጭ ከፈን ሸፍኖ እና ገንዞ ሰላተል ጀናዛ በመስገድ ወደ ቀብር ወስዶ መቅበር በኢስላም የተደነገገ ነው::

"የሰው ልጆች ሁሉ እንደማበጠሪያ ጥርስ እኩል ናቸው" የሚለው የነብያችን (ሰዓወ) የእኩልነት አስተምህሮ በህይወት እያሉ ብቻ ሳይሆን ሞተንም ቢሆን በቀብር ስርዓታችን ላይ አንዱ ከአንዱ የሚበላለጥበት መንገድ የዘጋ ነው::
ለሞቱት አላህ እዝነቱን ይላክላቸው

abu dawd

@nidatube
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ይቺ ሀገር የሁላችንም ናት፣ ሁላችንም በእኩል የምንኖርባት የጋራ ሀገር ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

ይቺ ሀገር የሁላችንም ናት ፣ ኦርቶዶክሱም ፣አይሁዱም ከመካከለኛው ምሰራቅ ነው የመጡት ግን ይቺ የሁላችንም ሀገር ናት ፣እዚች ሀገር ላይ የበቀሉ ክርሰቲያኖች የአረብ ክርቲያኖች ወይም የግሪክ ክርሰቲያኖች አይደለም የሚባሉት፣እንዲሁም እዚህ ምድር ላይ የበቀሉ ሙሰሊሞች ኢትዮዺያዊ እንጂ የሳኡዲ ፣ የሶሪያ ወይም የኢራቅ ሙሰሊሞች አይደሉም፣ኢትዮዺያዊ ሙሰሊሞች ናቸው።

ሁላችንም በእኩል የምንኖርባት የጋራ ሀገር ናት

ተወዳጁ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

@nidatube
2025/06/26 14:57:13
Back to Top
HTML Embed Code: