ዕንቁጣጣሽ በወርኃ መስከረም ስለመከበሩ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕይታ፡-
የዕንቁጣጣሽ በዓል በመስከረም ወር ላይ ለምን እንደሚከበር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚከተለው ያብራራሉ፡፡ ብርሃናት (ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት) የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜን ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ይጀምራሉ፤ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል ዐሥራ ሁለት ሰዓት ይሆናል፡፡ ለዘመን መታወቂያ ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ፈጠረ እንዳለ፤ (መጽሐፈ ሄኖክ ፳፩፥፵፱)፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ዓለምን ውኃ አጥለቅልቋት ከቆየ በኋላ ዳግመኛ ከነበረው ውኃ የተገለጠችበት ወር «በመጀመሪያም ወር በምድር ታየች የንፍር ውኃው ከምድር ደረቀ» የሚለውን መሠረት አድርገው የአቡሻኽር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስረዳሉ፡፡ (መጽሐፈ ኩፋሌ ፯፥፩)
ዘመን ሲለወጥ የሰው ልጆች ሕይወት ሊለወጥ ይገባል፡፡ ተማሪው ተምሮ ወደ ቀጣዩ ክፍል ያልፋል፤ በዚህ መልኩም ከኬጂ እስከ ዩኒቨርስቲ ደረጃ ይደረሳል፡፡ ገበሬውም የክረምትን ወራት በሚገባ ተጠቅሞ የሚቀጥለውን የበጋ ወራት የልፋቱን ዋጋ የምድርን በረከት የሚያገኝበት፣ ሠራተኛው የክረምቱን ዝናብ ታግሦ ከፀሐይ ወራት ይደርሳል፤ ክርስቲያንም ዓመት ሲለውጥ በኃጢአት የነበረ ሰው ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከክፋት ወደ በጎነት፣ ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ ከመጀመሪያው የክርስትና ደረጃ እስከ ዐሥረኛው ማዕረግ የሚደረስብትን እያቀደ መኖር ይገባዋል፡፡ ምን ጊዜም ዘመን በተለወጠ ጊዜ የዓመታት እና የወራት ለውጥ ብቻ ሳይሆን የክርስቲኖችም የሕይወት ለውጥ የሚገባ መሆኑን ከተፈጥሮ ክስተት መረዳት ይቻላል፡፡ መጪውን አዲሱ ዓመት ዘመነ ዮሐንስን የቤተ ክርስቲያን ከፍታ የምናይበት፣ በክርስትናችን የሕይወት ለውጥ የሚያድግበት፣ ሰላም፣ አንድነት፣ የምናይበት እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንልን፤ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
የዕንቁጣጣሽ በዓል በመስከረም ወር ላይ ለምን እንደሚከበር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚከተለው ያብራራሉ፡፡ ብርሃናት (ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት) የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜን ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ይጀምራሉ፤ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል ዐሥራ ሁለት ሰዓት ይሆናል፡፡ ለዘመን መታወቂያ ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ፈጠረ እንዳለ፤ (መጽሐፈ ሄኖክ ፳፩፥፵፱)፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ዓለምን ውኃ አጥለቅልቋት ከቆየ በኋላ ዳግመኛ ከነበረው ውኃ የተገለጠችበት ወር «በመጀመሪያም ወር በምድር ታየች የንፍር ውኃው ከምድር ደረቀ» የሚለውን መሠረት አድርገው የአቡሻኽር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስረዳሉ፡፡ (መጽሐፈ ኩፋሌ ፯፥፩)
ዘመን ሲለወጥ የሰው ልጆች ሕይወት ሊለወጥ ይገባል፡፡ ተማሪው ተምሮ ወደ ቀጣዩ ክፍል ያልፋል፤ በዚህ መልኩም ከኬጂ እስከ ዩኒቨርስቲ ደረጃ ይደረሳል፡፡ ገበሬውም የክረምትን ወራት በሚገባ ተጠቅሞ የሚቀጥለውን የበጋ ወራት የልፋቱን ዋጋ የምድርን በረከት የሚያገኝበት፣ ሠራተኛው የክረምቱን ዝናብ ታግሦ ከፀሐይ ወራት ይደርሳል፤ ክርስቲያንም ዓመት ሲለውጥ በኃጢአት የነበረ ሰው ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከክፋት ወደ በጎነት፣ ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ ከመጀመሪያው የክርስትና ደረጃ እስከ ዐሥረኛው ማዕረግ የሚደረስብትን እያቀደ መኖር ይገባዋል፡፡ ምን ጊዜም ዘመን በተለወጠ ጊዜ የዓመታት እና የወራት ለውጥ ብቻ ሳይሆን የክርስቲኖችም የሕይወት ለውጥ የሚገባ መሆኑን ከተፈጥሮ ክስተት መረዳት ይቻላል፡፡ መጪውን አዲሱ ዓመት ዘመነ ዮሐንስን የቤተ ክርስቲያን ከፍታ የምናይበት፣ በክርስትናችን የሕይወት ለውጥ የሚያድግበት፣ ሰላም፣ አንድነት፣ የምናይበት እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንልን፤ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
ርእሰ ዐውደ ዓመት
ዐውደ ዓመት መነሻው ዖደ ከሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ዖደ ዞረ፤ዐውድ ዙርያ፣ ማለት ነው፤ ዐውደ ዓመት የፀሐይ ዐውደ ዓመት ፫፻፷፭ ዕለት ከሩብ ይላል፡፡ (ምንጭ፡ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋሰወ ወግስ ወመዘግበ ቃላት ገጽ ፮፻፹፯)፡፡ ወበዐውዱ ለወእቱ መንበር፡፡ ይቀውሙ ዐውዶ፡፡ ዐውደ ጸሓይ፣ ዐውደ ወርኅ፣ ዐውደ ዓመት (ራእ.፬፡፬፤ አቡሻህር ፳፫)
ዐውደ ዓመት በግእዝ ሲሆን በአማርኛ የዘመን መለወጫ ይባላል፡፡ ርእሰ ዐውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ መፅምቅን ያወሳናል፤ የቅዱስ ዮሐንስ ዕረፍት (ምትረተ ርእሱ) የሚታሰበው መስከረም ሁለት ቀን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስን በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ መካከል የነበረ መሸጋገሪያ ነው፡፡ መታሰቢያ በዓሉም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ከሆነው ካለፈው ዓመት የሐዲስ ኪዳን ምሳሌ ወደሚሆነው አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ በሆነው በመስከረም አንድ ቀን ይከበራል፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በነቢያት መጨረሻ በሐዋርያት መጀመሪያ ተገኝቶ ዘመነ ሐዲስን እንደሰበከና ከዘመነ ብሉይ ወደ ዘመነ ሐዲስ መሸጋገሪያ ጊዜ ላይ ስለነበረ ያለፈውን ዘመን የምንሸጋገርበት የዘመን መለወጫ ቀን የቅዱስ ዮሐንስ መታሰቢያ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ (ማር.፩፥፪-፭)
የዘመን ቆጠራ ከጌታችን ልደት በፊት የነበረው አገልግሎት የሰው ልጆች ሁሉ በተለይ አበው ነቢያት/ በተስፋ ይጠብቁት የነበረውን የጌታችንን መምጣት የቀረውን ጊዜ እንዲሁም በብሉይ ኪዳን አጽዋማትና በዓላት ለማወቅ ነበር፡፡ ተስፋው ከተፈፀመ በኋላ ደግሞ የዘመን ቆጠራ ዋና አገልግሎቱ በዓላትና አጽዋማት በዓመቱ የሚወሉበትን ዕለት ለማወቅ ነው፡፡ እነዚህ በዓላት እግዚአብሔር በተለያዩ ዘመናት ለሰው ልጆች ያደረጋቸው ድንቅ ነገሮችና ውለታዎች የፈጸመባቸው ስቅለት፣ ትንሣኤ እና ሌሎችም በዓላት የሚታሰቡባቸው ናቸው፡፡
ዐውደ ዓመት መነሻው ዖደ ከሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ዖደ ዞረ፤ዐውድ ዙርያ፣ ማለት ነው፤ ዐውደ ዓመት የፀሐይ ዐውደ ዓመት ፫፻፷፭ ዕለት ከሩብ ይላል፡፡ (ምንጭ፡ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋሰወ ወግስ ወመዘግበ ቃላት ገጽ ፮፻፹፯)፡፡ ወበዐውዱ ለወእቱ መንበር፡፡ ይቀውሙ ዐውዶ፡፡ ዐውደ ጸሓይ፣ ዐውደ ወርኅ፣ ዐውደ ዓመት (ራእ.፬፡፬፤ አቡሻህር ፳፫)
ዐውደ ዓመት በግእዝ ሲሆን በአማርኛ የዘመን መለወጫ ይባላል፡፡ ርእሰ ዐውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ መፅምቅን ያወሳናል፤ የቅዱስ ዮሐንስ ዕረፍት (ምትረተ ርእሱ) የሚታሰበው መስከረም ሁለት ቀን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስን በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ መካከል የነበረ መሸጋገሪያ ነው፡፡ መታሰቢያ በዓሉም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ከሆነው ካለፈው ዓመት የሐዲስ ኪዳን ምሳሌ ወደሚሆነው አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ በሆነው በመስከረም አንድ ቀን ይከበራል፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በነቢያት መጨረሻ በሐዋርያት መጀመሪያ ተገኝቶ ዘመነ ሐዲስን እንደሰበከና ከዘመነ ብሉይ ወደ ዘመነ ሐዲስ መሸጋገሪያ ጊዜ ላይ ስለነበረ ያለፈውን ዘመን የምንሸጋገርበት የዘመን መለወጫ ቀን የቅዱስ ዮሐንስ መታሰቢያ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ (ማር.፩፥፪-፭)
የዘመን ቆጠራ ከጌታችን ልደት በፊት የነበረው አገልግሎት የሰው ልጆች ሁሉ በተለይ አበው ነቢያት/ በተስፋ ይጠብቁት የነበረውን የጌታችንን መምጣት የቀረውን ጊዜ እንዲሁም በብሉይ ኪዳን አጽዋማትና በዓላት ለማወቅ ነበር፡፡ ተስፋው ከተፈፀመ በኋላ ደግሞ የዘመን ቆጠራ ዋና አገልግሎቱ በዓላትና አጽዋማት በዓመቱ የሚወሉበትን ዕለት ለማወቅ ነው፡፡ እነዚህ በዓላት እግዚአብሔር በተለያዩ ዘመናት ለሰው ልጆች ያደረጋቸው ድንቅ ነገሮችና ውለታዎች የፈጸመባቸው ስቅለት፣ ትንሣኤ እና ሌሎችም በዓላት የሚታሰቡባቸው ናቸው፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሥርዓቱ መሠረት የበዓላቱና የአጽዋማቱ መደብ የሚታወቅበትና የዘመናቱ ሂደት ተቀምሮ የሚታወጅበት ዕለት መስከረም አንድ ቀን ርእሰ ዐውደ ዓመትን ታከብራለች፡፡ የኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያ መስከረም ነው፡፡ በዚህ ወር የመጀመሪያው ቀን የተለያዩ መጠሪያዎች አሉት፡፡ እነርሱም ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡
አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን ለምን ይከበራል?
በኢትዮጵያ (ርእሰ ዐውደ ዓመት) ዘመን መለወጫ በመስከረም ወር የሆነበትን ምክንያት ሊቃውንቱ ሲያትቱ ብርሃናት ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ክዋክብት የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ አጠናቀው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል ፲፪ ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ ፫፻፰፬ ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና (ሄኖክ. ፳፩፥፵፱)፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር ነው፡፡ (ኩፋሌ. ፯፥፩)፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥን አብራርተው አስቀምጠዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያንን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በጽሑፋቸው ዘመኑን በአራቱ ወንጌላውያን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ የጌታን መጠመቅ፣መሰቀልን፣ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ ማውጣትን አራቱ ወንጌላውያን እያወሱ ዘመናትን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ፡፡ ወንጌላዊውን ወይም ዘመኑን ለማወቅ ዓመተ ፍዳ(ኩነኔ) አምስት ሺህ አምስት መቶ እና ዓመተ ምሕረት (አሁን ያለንበትን ዓመት) በመደመር ውጤቱ ለአራቱ ወንጌላውያን ማለትም ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ በማካፈል የምናገኘው ነው፡፡ ይህም የአንዱ ወንጌላዊ ድርሻ ማለት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ቀሪው አንድ ከሆነ ዘመኑ ማቴዎስ፣ ሁለት ከሆነ ዘመነ ማርቆስ፣ ሦስት ከሆነ ዘመነ ሉቃስ ምንም ቀሪ ባይኖር ደግሞ ዘመነ ዮሐንስ ነው፡፡ ስሌቱም ከዚህ በታች የተቀመጠውን ምሳሌ መነሻ አድርጎ ወንጌላዊውን ማን እንደሆነ ማወቅ ይቻላል፡፡ስለ አዲስ ዓመት በተለያየ ስም የመጠራቱ ታሪካዊ አመጣጥና ስያሜ መነሻ አሳቡ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
አዲስ ዓመት ለምን ቅዱስ ዮሐንስ ይባላል...?
የቅዱስ ዮሐንስ ተግባር በቕዱስ ዮሐንስ አወርቅ የተጠቀሰ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ዐውደ ዓመት መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር አባቶች ወስነዋል፡፡ (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ ፩-፫)፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር “የመስከረም ወር የተባረከ ነው፡፡ እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው፡፡ የዚህ ወር ቀኑና ሌሊቱ እኩል ፲፪ ሰዓት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጎደለ ይሄዳል” እንዲል፡፡ በአጠቃላይ ዘመን መለወጫ ከላይ ባየናቸው የተለያየ ስያሜ ይጠራ እንጂ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች ሥርዓት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውነታችሁን አታርክሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነውና እያለ በመዋዕለ ሥጋዌው ያስተምር ነበር፡፡ አዲስ ዓመት ሲመጣ በኃጢኣት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ልናደርገው ይገባናል፡፡
ዘመነ ማቴዎስም፣ ዘመነ ማርቆስም፣ ዘመነ ሉቃስም ሆነ ዘመነ ዮሐንስ፤ በአራቱም ዘመናት አስቀድሞ ርእሰ ዐውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ ይዘከራል፡፡ ዮሐንስ የስሙ ትርጉም «ጸጋ እግዚአብሔር» ማለት ነው፡፡ ዘመናት ዘመናትን እየወለዱ፣ ሰዓታት ደቂቃን ቅጽበትን (ሰኮንድን) ሳይቀር እየሰፈሩ(እየቆጠሩ) ዕለታት ሳምንታትን፣ ሳምንታት ወራትን፣ ወራት ዓመታትን አሁን ላለንበት ዘመን ደርሰናል፡፡
ዕንቁጣጣሽ
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስረዱት ዕንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይም ጥንተ ታሪክ በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪቃ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪቃ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በሀገረ ኢትዮጵያ በወርኀ መስከረም ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኃ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት «ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ» ይህችን ወቅት ዕንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ በመቀጠል የሀገራችን ንግሥት ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ዜና ጥበብ በጆሮዋ የሰማችውን በዓይኗ ዓይታ ለመረዳት ስለፈለገች ወደ ኢየሩሳሌም ገባች፡፡ ንግሥተ ሳባም ከንጉሡ ሰሎሞንም ተገናኝተው ቤተ መንግሥቱንም አስጎበውኝቶ ሲያበቃ «ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንልሽ» ሲል እጅግ በጣም የከበረ ዕንቁ አበረከተላት/ሰጣት/፡፡ ወሩም ወረኃ መስከረም ነበር፡፡
ንግሥቷ ጠቢቡ ሰሎሞንን ለመጎብኘት በሔደችበት ወቅት ፀንሳ ቀዳማዊ ምኒልክን በወለደች ጊዜ ሕዝቡ ንጉሥ ተወለደ እልል እያሉ «አበባ ዕንቁ (አብረቅራቂ ድንጋይ) ጣጣሽ (ገጸ በረከት)» እያለ ገጸ በረከት ለንግሥቲቱ አበረከቱ፡፡ ያ የዘመን መለወጫ በዓልም ልጃገረዶች የአበባ ገጸ በረከት የሚያቀርቡበት ስለሆነ ዕንቁጣጣሽ ተባለ፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው መጥቷል፡፡ አሁን ከሚፈጸመው ሥነ ሥርዓት ደርሶ በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ የሚከበረውም መስከረም አንድ ቀን ነው፡፡ አንድም «ዕንቁ ዕፅ አወጣሸ»ብሎ የአበባውን መፈንዳትን ያስረዳናል፡፡ የዘመን መለወጫ (ርእሰ ዐውደ ዓመት) ዕንቁጣጣሽ ተብሎም እንደሚጠራ ታሪክ ያወሳናል፡፡ ስያሜውም ለበዓሉ የተሰጠው በንግሥተ ሳባ ዘመነ መንግሥት ነበር፡፡
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የአንድነትና የመተሳሳብ ዘመን እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት የቅደስት ደንግል ማርያም አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንልን አሜን፡፡
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን ለምን ይከበራል?
በኢትዮጵያ (ርእሰ ዐውደ ዓመት) ዘመን መለወጫ በመስከረም ወር የሆነበትን ምክንያት ሊቃውንቱ ሲያትቱ ብርሃናት ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ክዋክብት የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ አጠናቀው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል ፲፪ ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ ፫፻፰፬ ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና (ሄኖክ. ፳፩፥፵፱)፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር ነው፡፡ (ኩፋሌ. ፯፥፩)፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥን አብራርተው አስቀምጠዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያንን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በጽሑፋቸው ዘመኑን በአራቱ ወንጌላውያን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ የጌታን መጠመቅ፣መሰቀልን፣ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ ማውጣትን አራቱ ወንጌላውያን እያወሱ ዘመናትን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ፡፡ ወንጌላዊውን ወይም ዘመኑን ለማወቅ ዓመተ ፍዳ(ኩነኔ) አምስት ሺህ አምስት መቶ እና ዓመተ ምሕረት (አሁን ያለንበትን ዓመት) በመደመር ውጤቱ ለአራቱ ወንጌላውያን ማለትም ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ በማካፈል የምናገኘው ነው፡፡ ይህም የአንዱ ወንጌላዊ ድርሻ ማለት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ቀሪው አንድ ከሆነ ዘመኑ ማቴዎስ፣ ሁለት ከሆነ ዘመነ ማርቆስ፣ ሦስት ከሆነ ዘመነ ሉቃስ ምንም ቀሪ ባይኖር ደግሞ ዘመነ ዮሐንስ ነው፡፡ ስሌቱም ከዚህ በታች የተቀመጠውን ምሳሌ መነሻ አድርጎ ወንጌላዊውን ማን እንደሆነ ማወቅ ይቻላል፡፡ስለ አዲስ ዓመት በተለያየ ስም የመጠራቱ ታሪካዊ አመጣጥና ስያሜ መነሻ አሳቡ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
አዲስ ዓመት ለምን ቅዱስ ዮሐንስ ይባላል...?
የቅዱስ ዮሐንስ ተግባር በቕዱስ ዮሐንስ አወርቅ የተጠቀሰ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ዐውደ ዓመት መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር አባቶች ወስነዋል፡፡ (ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ ፩-፫)፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር “የመስከረም ወር የተባረከ ነው፡፡ እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው፡፡ የዚህ ወር ቀኑና ሌሊቱ እኩል ፲፪ ሰዓት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጎደለ ይሄዳል” እንዲል፡፡ በአጠቃላይ ዘመን መለወጫ ከላይ ባየናቸው የተለያየ ስያሜ ይጠራ እንጂ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች ሥርዓት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውነታችሁን አታርክሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነውና እያለ በመዋዕለ ሥጋዌው ያስተምር ነበር፡፡ አዲስ ዓመት ሲመጣ በኃጢኣት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ልናደርገው ይገባናል፡፡
ዘመነ ማቴዎስም፣ ዘመነ ማርቆስም፣ ዘመነ ሉቃስም ሆነ ዘመነ ዮሐንስ፤ በአራቱም ዘመናት አስቀድሞ ርእሰ ዐውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ ይዘከራል፡፡ ዮሐንስ የስሙ ትርጉም «ጸጋ እግዚአብሔር» ማለት ነው፡፡ ዘመናት ዘመናትን እየወለዱ፣ ሰዓታት ደቂቃን ቅጽበትን (ሰኮንድን) ሳይቀር እየሰፈሩ(እየቆጠሩ) ዕለታት ሳምንታትን፣ ሳምንታት ወራትን፣ ወራት ዓመታትን አሁን ላለንበት ዘመን ደርሰናል፡፡
ዕንቁጣጣሽ
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስረዱት ዕንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይም ጥንተ ታሪክ በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪቃ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪቃ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በሀገረ ኢትዮጵያ በወርኀ መስከረም ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኃ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት «ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ» ይህችን ወቅት ዕንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ በመቀጠል የሀገራችን ንግሥት ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ዜና ጥበብ በጆሮዋ የሰማችውን በዓይኗ ዓይታ ለመረዳት ስለፈለገች ወደ ኢየሩሳሌም ገባች፡፡ ንግሥተ ሳባም ከንጉሡ ሰሎሞንም ተገናኝተው ቤተ መንግሥቱንም አስጎበውኝቶ ሲያበቃ «ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንልሽ» ሲል እጅግ በጣም የከበረ ዕንቁ አበረከተላት/ሰጣት/፡፡ ወሩም ወረኃ መስከረም ነበር፡፡
ንግሥቷ ጠቢቡ ሰሎሞንን ለመጎብኘት በሔደችበት ወቅት ፀንሳ ቀዳማዊ ምኒልክን በወለደች ጊዜ ሕዝቡ ንጉሥ ተወለደ እልል እያሉ «አበባ ዕንቁ (አብረቅራቂ ድንጋይ) ጣጣሽ (ገጸ በረከት)» እያለ ገጸ በረከት ለንግሥቲቱ አበረከቱ፡፡ ያ የዘመን መለወጫ በዓልም ልጃገረዶች የአበባ ገጸ በረከት የሚያቀርቡበት ስለሆነ ዕንቁጣጣሽ ተባለ፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው መጥቷል፡፡ አሁን ከሚፈጸመው ሥነ ሥርዓት ደርሶ በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ የሚከበረውም መስከረም አንድ ቀን ነው፡፡ አንድም «ዕንቁ ዕፅ አወጣሸ»ብሎ የአበባውን መፈንዳትን ያስረዳናል፡፡ የዘመን መለወጫ (ርእሰ ዐውደ ዓመት) ዕንቁጣጣሽ ተብሎም እንደሚጠራ ታሪክ ያወሳናል፡፡ ስያሜውም ለበዓሉ የተሰጠው በንግሥተ ሳባ ዘመነ መንግሥት ነበር፡፡
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የአንድነትና የመተሳሳብ ዘመን እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት የቅደስት ደንግል ማርያም አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁንልን አሜን፡፡
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
🟢 🟡 🔴
መስከረም 2 | የካህኑ የዘካርያስ ልጅ የከበረ #አጥማቂው_ዮሐንስ ሕግን አፍራሽ በሆነ በንጉሥ ሄሮድስ እጅ ሰማዕት ሆነ።
ይህም እንዲህ ነው፦
ቅዱስ ዮሐንስ ሄሮድስን የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን ስለማግባቱና ሌላም ያደርገው ስለነበረ ክፉ ሥራ ሁሉ ይገሥጸው ነበር። ደግሞም በተግሣጽ ላይ ተግሣጽን ጨመረ። ስለዚህም ዮሐንስን ተቀየመውና በግዞት ቤት አኖረው።
ሄሮድስም ዮሐንስን ይፈራው ነበር። ጻድቅ ቅዱስ ሰው እንደሆነ ያውቅ ነበርና ብዙ ይጠባበቀውም ነበር። ሄሮድስ የተወለደባትን ቀን በዓል የሚያከብርባት ዕለት ነበረች። መኳንንቱን አለቆቹን መሣፍንቱን ሹሞቹን በገሊላ አገር ያሉትን ታላላቅ ሰዎች ግብር አገባ።
የሄሮድያዳ ልጅም ወደ አዳራሹ ገብታ ዘፈነች። ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው ከእርሱ ጋር በማዕድ የነበሩትንም ንጉሡም ያቺን ብላቴና የምትሺውን ለምኚኝ እሰጥሻለሁ አላት። እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ሊሰጣት ማለላት።
ወጥታም እናቷን ምን ልለምነው አለቻት። እናቷም የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ አለቻት። ያን ጊዜም እየሮጠች ወደ ንጉሡ ገብታ የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን እንድትሰጠኝ እሻለሁ ብላ ለመነችው። ንጉሡም ስለ መሐላው አብረውት ስለ ነበሩትም ሰዎች አዘነ፤ እምቢ ሊላት ግን አልወደደም።
ያን ጊዜም ባለወጎችን ላከ በእሥር ቤትም ሳለ የዮሐንስን ራስ ቆረጡ። ራሱንም በወጭት አምጥተው ለዚያች ብላቴና ሰጧት። እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች። በዚያችም ቀን የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ከሄሮድያዳ ከእጆቿ ላይ ወደ አየር ስለ በረረች ታላቅ ድንጋፄ ሆነ።
ደግሞም ሄሮድስ ሆይ የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም አለች። ደቀ መዛሙርቱም በሰሙ ጊዜ መጥተው በድኑን ወስደው ቀበሩት።
#እንኳን_አደረሳችሁ
◦🌿◦🌿◦🌿◦
መስከረም 2 | የካህኑ የዘካርያስ ልጅ የከበረ #አጥማቂው_ዮሐንስ ሕግን አፍራሽ በሆነ በንጉሥ ሄሮድስ እጅ ሰማዕት ሆነ።
ይህም እንዲህ ነው፦
ቅዱስ ዮሐንስ ሄሮድስን የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን ስለማግባቱና ሌላም ያደርገው ስለነበረ ክፉ ሥራ ሁሉ ይገሥጸው ነበር። ደግሞም በተግሣጽ ላይ ተግሣጽን ጨመረ። ስለዚህም ዮሐንስን ተቀየመውና በግዞት ቤት አኖረው።
ሄሮድስም ዮሐንስን ይፈራው ነበር። ጻድቅ ቅዱስ ሰው እንደሆነ ያውቅ ነበርና ብዙ ይጠባበቀውም ነበር። ሄሮድስ የተወለደባትን ቀን በዓል የሚያከብርባት ዕለት ነበረች። መኳንንቱን አለቆቹን መሣፍንቱን ሹሞቹን በገሊላ አገር ያሉትን ታላላቅ ሰዎች ግብር አገባ።
የሄሮድያዳ ልጅም ወደ አዳራሹ ገብታ ዘፈነች። ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው ከእርሱ ጋር በማዕድ የነበሩትንም ንጉሡም ያቺን ብላቴና የምትሺውን ለምኚኝ እሰጥሻለሁ አላት። እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ሊሰጣት ማለላት።
ወጥታም እናቷን ምን ልለምነው አለቻት። እናቷም የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ አለቻት። ያን ጊዜም እየሮጠች ወደ ንጉሡ ገብታ የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን እንድትሰጠኝ እሻለሁ ብላ ለመነችው። ንጉሡም ስለ መሐላው አብረውት ስለ ነበሩትም ሰዎች አዘነ፤ እምቢ ሊላት ግን አልወደደም።
ያን ጊዜም ባለወጎችን ላከ በእሥር ቤትም ሳለ የዮሐንስን ራስ ቆረጡ። ራሱንም በወጭት አምጥተው ለዚያች ብላቴና ሰጧት። እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች። በዚያችም ቀን የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ከሄሮድያዳ ከእጆቿ ላይ ወደ አየር ስለ በረረች ታላቅ ድንጋፄ ሆነ።
ደግሞም ሄሮድስ ሆይ የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም አለች። ደቀ መዛሙርቱም በሰሙ ጊዜ መጥተው በድኑን ወስደው ቀበሩት።
#እንኳን_አደረሳችሁ
◦🌿◦🌿◦🌿◦
"እንደቀድሞ ጊዜ ቢሆን ቤተ ክርስቲያን እያለች ሰላም ከሀገር አይርቅም ነበር፤ ዛሬ በእኛ በአገልጋዮቿ ምክንያት ያን ሚናዋን አጥታለች"
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
በማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ተገኝተው ቡራኬና ቃለ ምእዳን የሰጡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወቅታዊ የሀገራችን የሰላም ሁኔታ ላይ ለተሳታፊዎቹ መልእክት አስተላልፈዋል።
"ቤተ ክርስቲያን አንድ ሁኑ ብላ ታስተምራለች፤ ጥላቻን መገዳደልን ታወግዛለች፤በንግግር በውይይት ፍቱ ትላለች" ያሉት ብፁዕነታቸው "ይህንን አቋሟን በበጎ የማይመለከቱ ግን ይኖራሉ" ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመልእክታቸውም "እንደቀድሞ ጊዜ ቢሆን ቤተ ክርስቲያን እያለች ሰላም ከሀገር አይርቅም ነበር፤ ዛሬ በእኛ በአገልጋዮቿ ምክንያት ያን ሚናዋን አጥታለች" በማለት "ወላዋይና አድርባዮች ስለሆንን፣ ምን አገባኝ ብለን መስለን ስላለን ሀገሪቱን ዋጋ እያስከፈልን ነው፤ የወገን ደምም ሲፈስ ማየት ተለምዷል ሲሉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም " ያለፈው ዘመን ይበቃ ዘንድ ስለሰላም ልንጸልይ ይገባል" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
በማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ተገኝተው ቡራኬና ቃለ ምእዳን የሰጡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወቅታዊ የሀገራችን የሰላም ሁኔታ ላይ ለተሳታፊዎቹ መልእክት አስተላልፈዋል።
"ቤተ ክርስቲያን አንድ ሁኑ ብላ ታስተምራለች፤ ጥላቻን መገዳደልን ታወግዛለች፤በንግግር በውይይት ፍቱ ትላለች" ያሉት ብፁዕነታቸው "ይህንን አቋሟን በበጎ የማይመለከቱ ግን ይኖራሉ" ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመልእክታቸውም "እንደቀድሞ ጊዜ ቢሆን ቤተ ክርስቲያን እያለች ሰላም ከሀገር አይርቅም ነበር፤ ዛሬ በእኛ በአገልጋዮቿ ምክንያት ያን ሚናዋን አጥታለች" በማለት "ወላዋይና አድርባዮች ስለሆንን፣ ምን አገባኝ ብለን መስለን ስላለን ሀገሪቱን ዋጋ እያስከፈልን ነው፤ የወገን ደምም ሲፈስ ማየት ተለምዷል ሲሉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም " ያለፈው ዘመን ይበቃ ዘንድ ስለሰላም ልንጸልይ ይገባል" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
"ዓለም በሚቀማበት ወቅት ጊዜውን፣ እውቀቱን፣ ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጥ እንደእናንተ አይነት ልጆች ስላሉን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን"
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በማኅበረ ቅዱሳን የ2016 ዓ.ም የ6 ወራት የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ቡራኬና ቃለ ምእዳን ሰጥተዋል።
በዚህ አስፈሪ ጊዜ እግዚአብሔር ሥራ እንድንሠራ ፈቅዷል ያሉት ብፁዕነታቸው በርካታ ችግሮችን አልፋችሁ መጥታችኋል። ዓለም በሚቀማበት ወቅት ጊዜውን፣ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጥ እንደእናንተ አይነት ልጆች ስላሉን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን ብለዋል።
ብፁዕነታቸው በመልእክታቸው "የቤተ ክርስቲያን ጥቅም እንጂ ቤተ ክርስቲያን በአእምሯችን የሌለች ሁነናል። እግዚአብሔር ግን በተለያዩ መከራዎች ውስጥ ሁነው ስለሚያለቅሱት ሲል ያሻግረናል፤ራሳቸውን ለመስጠት በተዘጋጁ ምእመናን እናልፈዋለን፤ እነዚህን ከደገፍናቸው ቤተ ክርስቲያን ጸንታ ትኖራለች። እናንተም እነሱን ነው ምታግዙት"ሲሉ ገልፀዋል ።
ከእኛ የሚጠበቀውን በመንፈሳዊነት ከሠራን ሀገር ትለወጣለች፤ ግን አንድ ሁነን፣ በእግዚአብሔር አምነን በጸሎት ሲሆን ነው በማለት አጽዕኖት የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ተደማምጠንና ተናበን መሥራት ከቻልን እናልፈዋለን ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል።
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ በማሳለፍና አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በማኅበረ ቅዱሳን የ2016 ዓ.ም የ6 ወራት የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ቡራኬና ቃለ ምእዳን ሰጥተዋል።
በዚህ አስፈሪ ጊዜ እግዚአብሔር ሥራ እንድንሠራ ፈቅዷል ያሉት ብፁዕነታቸው በርካታ ችግሮችን አልፋችሁ መጥታችኋል። ዓለም በሚቀማበት ወቅት ጊዜውን፣ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጥ እንደእናንተ አይነት ልጆች ስላሉን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን ብለዋል።
ብፁዕነታቸው በመልእክታቸው "የቤተ ክርስቲያን ጥቅም እንጂ ቤተ ክርስቲያን በአእምሯችን የሌለች ሁነናል። እግዚአብሔር ግን በተለያዩ መከራዎች ውስጥ ሁነው ስለሚያለቅሱት ሲል ያሻግረናል፤ራሳቸውን ለመስጠት በተዘጋጁ ምእመናን እናልፈዋለን፤ እነዚህን ከደገፍናቸው ቤተ ክርስቲያን ጸንታ ትኖራለች። እናንተም እነሱን ነው ምታግዙት"ሲሉ ገልፀዋል ።
ከእኛ የሚጠበቀውን በመንፈሳዊነት ከሠራን ሀገር ትለወጣለች፤ ግን አንድ ሁነን፣ በእግዚአብሔር አምነን በጸሎት ሲሆን ነው በማለት አጽዕኖት የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ተደማምጠንና ተናበን መሥራት ከቻልን እናልፈዋለን ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል።
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ በማሳለፍና አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
ንስጥሮሳውያን ማናቸው
ንስጥሮሳውያንን ለመረዳት በመጀመሪያ ስለ ንስጥሮስ እንመልከት። ንስጥሮስ በ5ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ሲሆን በአንጾኪያ ቤተክርስቲያን የተማረና ከ 428 እስከ 431 የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የነበረ ነው። ነገር ግን በ431 ዓ.ም በተካሄደው ሶስተኛው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ተወግዞ ከጵጵስናው የተሻረ ነው።
ንስጥሮስ የተወዘገው በኤፌሶን ጉባኤ በ431 ሲሆን ይህም የሆነው የቤተ ክርሰቲያን መከፋፈል ሳይመጣ ነው። ማለትም ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ፣ ምስራቅ ኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ የሚባሉት መከፋፈሎች ሳይመጡ በፊት፣ የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያን (early church) በሚባለው ዘመን ነው።
የንስጥሮስ አስተምህሮ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና እመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ እመቤታችን ድንግል ማርያም የአምላክ እናት አይደለችም የሚል ነበር። እንዲሁም ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ ነው የሚል ነበር።
ይህም ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ አምላክ ሆኖ አልተወለደም የሚልን ሀሳብ የሚፈጥር ነው። ጌታችን አምላክነቱ እና ሰውነቱ አንድ ሳይሆኑ የተነጣጠሉ ናቸው የሚል ነው። ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች የከፈለውን ዋጋ የሚያሳንስ (እሱ ስላለ ጌታችን የከፈለልን ዋጋ አይቀንስም)፣ እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ክብሯን የሚቀንስ ነው (እሱ ስለተናገረ ክብሯ አይቀንስም)።
በዚህም ምክንያት በፈረንጆች አቆጣጠር በ431 ዓ.ም በኤፌሶን ከተማ ሶስተኛው የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ተደረገ። ከ200 በላይ አባቶች ጳጳሳት፣ ከሮም፣ ከእስክንድርያ፣ ከአንጾኪያ ከሁሉም ቦታ የመጡ አባቶች በተኙበት ጉባኤ ንስጥሮስ ተወገዘ። የጵጵስና ማዕረጉም ተሻረ። የሱን አስተምህሮ የሚከተሉ ሁሉም ተወገዙ።
በዚህም ንስጥሮስና ተከታዮቹ ጠፉ። ነገር ግን አስተምህሮው አልጠፋም ነበር። በ451 በተካሄደ ጉባኤ የግሪክና የላቲን ቤተ ክርስቲያናት የሱን አስተምህሮ በተዘዋዋሪ ተቀበሉ። በአፋቸው ንስጥሮስ የተወገዘ ነው ቢሉም ግን የተቀበሉትን በተዘዋዋሪ የንስጥሮስን ሁለት ባህርይ አስተምህሮ ነው። ይህን የተቃወሙትም የኦሪየንታል ቤተክርስቲያናት ከነሱ ተለዩ።
ሌሎችም የንስጥሮስ ተከታዮች ነበሩ። ይህም በምዕራብ ሶርያና ምስራቅ ኢራቅ አከባቢ የምትገኘው የ"ምስራቅ" ቤተክርስቲያን ተከታዮች ነበሩ። ይህ ቤተክርስቲያን ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬም የቆየ ሲሆን የንስጥሮስን አስተምህሮ በቀጥታ የሚቀበሉ እና ንስጥሮስንም እንደ ቅዱስ የሚቆጥሩ ናቸው።
ታዲያ ይህ ከላይ ያየነው አባት የዚህ ቤተክርስቲያን አባል ነው። ከልደቱም ጀምሮ በዚህች ንስጥሮሳዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበረ ሲሆን በዚያም ዲቁና እና ክህነት ያገኘ ነበር። በኋላ ላይ ግን ከዚያም በመለየት የራሱን ቸርች የከፈተ ሰው ነው።
እንደ ቻናሌ የዚህን ሰው የኋላ ታሪክ ሳልመረምር መልክቱን በመልቀቄ ይቅርታ እጠይቃለሁ።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
ንስጥሮሳውያንን ለመረዳት በመጀመሪያ ስለ ንስጥሮስ እንመልከት። ንስጥሮስ በ5ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ሲሆን በአንጾኪያ ቤተክርስቲያን የተማረና ከ 428 እስከ 431 የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የነበረ ነው። ነገር ግን በ431 ዓ.ም በተካሄደው ሶስተኛው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ተወግዞ ከጵጵስናው የተሻረ ነው።
ንስጥሮስ የተወዘገው በኤፌሶን ጉባኤ በ431 ሲሆን ይህም የሆነው የቤተ ክርሰቲያን መከፋፈል ሳይመጣ ነው። ማለትም ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ፣ ምስራቅ ኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ የሚባሉት መከፋፈሎች ሳይመጡ በፊት፣ የቀድሞዋ ቤተ ክርስቲያን (early church) በሚባለው ዘመን ነው።
የንስጥሮስ አስተምህሮ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና እመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ እመቤታችን ድንግል ማርያም የአምላክ እናት አይደለችም የሚል ነበር። እንዲሁም ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ ነው የሚል ነበር።
ይህም ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ አምላክ ሆኖ አልተወለደም የሚልን ሀሳብ የሚፈጥር ነው። ጌታችን አምላክነቱ እና ሰውነቱ አንድ ሳይሆኑ የተነጣጠሉ ናቸው የሚል ነው። ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች የከፈለውን ዋጋ የሚያሳንስ (እሱ ስላለ ጌታችን የከፈለልን ዋጋ አይቀንስም)፣ እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ክብሯን የሚቀንስ ነው (እሱ ስለተናገረ ክብሯ አይቀንስም)።
በዚህም ምክንያት በፈረንጆች አቆጣጠር በ431 ዓ.ም በኤፌሶን ከተማ ሶስተኛው የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ተደረገ። ከ200 በላይ አባቶች ጳጳሳት፣ ከሮም፣ ከእስክንድርያ፣ ከአንጾኪያ ከሁሉም ቦታ የመጡ አባቶች በተኙበት ጉባኤ ንስጥሮስ ተወገዘ። የጵጵስና ማዕረጉም ተሻረ። የሱን አስተምህሮ የሚከተሉ ሁሉም ተወገዙ።
በዚህም ንስጥሮስና ተከታዮቹ ጠፉ። ነገር ግን አስተምህሮው አልጠፋም ነበር። በ451 በተካሄደ ጉባኤ የግሪክና የላቲን ቤተ ክርስቲያናት የሱን አስተምህሮ በተዘዋዋሪ ተቀበሉ። በአፋቸው ንስጥሮስ የተወገዘ ነው ቢሉም ግን የተቀበሉትን በተዘዋዋሪ የንስጥሮስን ሁለት ባህርይ አስተምህሮ ነው። ይህን የተቃወሙትም የኦሪየንታል ቤተክርስቲያናት ከነሱ ተለዩ።
ሌሎችም የንስጥሮስ ተከታዮች ነበሩ። ይህም በምዕራብ ሶርያና ምስራቅ ኢራቅ አከባቢ የምትገኘው የ"ምስራቅ" ቤተክርስቲያን ተከታዮች ነበሩ። ይህ ቤተክርስቲያን ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬም የቆየ ሲሆን የንስጥሮስን አስተምህሮ በቀጥታ የሚቀበሉ እና ንስጥሮስንም እንደ ቅዱስ የሚቆጥሩ ናቸው።
ታዲያ ይህ ከላይ ያየነው አባት የዚህ ቤተክርስቲያን አባል ነው። ከልደቱም ጀምሮ በዚህች ንስጥሮሳዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበረ ሲሆን በዚያም ዲቁና እና ክህነት ያገኘ ነበር። በኋላ ላይ ግን ከዚያም በመለየት የራሱን ቸርች የከፈተ ሰው ነው።
እንደ ቻናሌ የዚህን ሰው የኋላ ታሪክ ሳልመረምር መልክቱን በመልቀቄ ይቅርታ እጠይቃለሁ።
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
በእንተ ቅዱስ መስቀል (#በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
የጌታችን የክርስቶስ መስቀል ለእንደ ምን ያለ ታላቅ በረከት ምክንያት እንደ ኾነልን እናስበው፡፡ ምንም እንኳን ከአፍአ ሲታይ የጌታችን መስቀል አሳዛኝና አሰቃቂ ቢመስልም፥ እንደ እውነቱ ግን ደስታንና ሐሴትን የተሞላ ነው፡፡ መስቀል የቤተ ክርስቲያን መድኃኒት ነውና፤ መስቀል ተስፋ ለሚያደርጉት መመኪያቸው ነውና፤ መስቀል ጠላቶች [ደቂቀ አዳም] ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቁበት [የታረቁበት]፥ ኃጥአንም ወደ ክርስቶስ የተመለሱበት [አሁንም የሚመለሱበት] ነውና፡፡
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ከግብርናተ ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ኾኖ ተገኘ፡፡ የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም [መንፈሳዊ] ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ እውነትም [ወንጌልም] ወደ ዓለም ኹሉ ደርሷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም [ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው] ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በኹሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ [በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና] ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት [የረባት፣ የጠቀማት] ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
ክርስቶስ በቅዱስ መስቀል ላይ ተሰቀለ፤ ዲያብሎስም በድን ኾነ፡፡ ክርስቶስ በቅዱስ መስቀል ላይ እጆቹን ዘረጋ፤ ለዓለምም የመዳን መንገድ ተሰጠ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተቸነከረ፤ ነፍሳትም ኹሉ ከእስራታቸው ተፈቱ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ዋለ፤ ፍጥረታትም ኹሉ ከጥፋት ባርነት ነፃ ወጡ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ፤ እንግዳ ነገርም ለዓለም ኹሉ ታየ ፀሐይ ብርሃኗን ከለከለች ንዑድ ክቡር የሚኾን ነቢዩ አሰምቶ እንደ ተናገረው - እንዲህ ሲል፡- “በዚያን ቀን ፀሐይ በቀትር ይገባል፤ ብርሃንም በምድር ላይ በቀን ይጨልማል” (አሞ.8፡9)፡፡ ተወዳጆች ሆይ! የነቢዩ ቃል እንደ ምን ያለ ግሩም ምሥጢር በውስጡ ቋጥሮ እንደ ያዘ ታያላችሁን? እዚህ ላይ የኹላቸውም -የእስራኤላውያንም የአሕዛብም - ግብር ተገልጧል፤ ኹላቸውም በአንድነት በድለዋልና፡፡
እንደ ኦሪቱ ሕግ በዓላትን የሚያከብሩት ያዝናሉ፤ በመዝሙር ፈንታም በኢየሩሳሌም ላይ.ያለቅሳሉ፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ኢየሩሳሌም የተቀደሱትን ሥርዓተ አምልኮዎችን ይዛ አትቀጥልምና፤ ከእንግዲህ ወዲህም በእርሷ ዘንድ በዓላት አይከበሩምና፡፡ የአሕዛብ አገራትም እንደዚሁ ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ ያዝናሉ፤ መጽሐፍ “የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው” እንዳለ ኀዘን የበረከት ምንጭ ነውና ይተክዛሉ (ማቴ.5፡4)፡፡ አዎ! ትርጉም ለሌላቸው በዓላቶቻቸውና ሥርዓት ለሌላቸው ዘፈኖቻቸው ለርኵሳት መናፍስት ይቀርብ እንደ ነበረ ዐውቀው ያዝናሉ፤ ይተክዛሉም፡፡ ዛሬ አሕዛብ ያከናውኑአቸው ለነበሩት ክፉ ክፉ ነገሮች እንዴት እንደሚጸጸቱባቸው አስተውሉ፤ ከነቢዩ ጋር በአንድነት እንዲህ ይላሉና፡- “በድለናል፤ በሐፍረታችንም ጠፍተናል፤ በዓመፃ ተሞልተናልና ኃጢአታችን ሸፍናናለች፡፡ እንደ አባቶቻችን በድለናል፡፡”
እንግዲያውስ እኛም ስለ ሠራናቸው ኃጣውእ እናልቅስ፤ እንዘንም፡፡ ተስፋችንን በእርሱ ላይ.አኑረን ወደ ቅዱስ መስቀሉ እንጠጋ፡፡ እኛ ሥራ ሠርተን አንበቃምና ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብሩና ጌትነቱ አንድ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነትና ሰውን መውደድ የመንግሥቱ ወራሾች እንኾን ዘንድ በመስቀሉ [ቃል] ተምረን አሳባችንን በሰማያት እናኑር፤ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ለዓለም ወለዓለም፥ አሜን!!!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
የጌታችን የክርስቶስ መስቀል ለእንደ ምን ያለ ታላቅ በረከት ምክንያት እንደ ኾነልን እናስበው፡፡ ምንም እንኳን ከአፍአ ሲታይ የጌታችን መስቀል አሳዛኝና አሰቃቂ ቢመስልም፥ እንደ እውነቱ ግን ደስታንና ሐሴትን የተሞላ ነው፡፡ መስቀል የቤተ ክርስቲያን መድኃኒት ነውና፤ መስቀል ተስፋ ለሚያደርጉት መመኪያቸው ነውና፤ መስቀል ጠላቶች [ደቂቀ አዳም] ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቁበት [የታረቁበት]፥ ኃጥአንም ወደ ክርስቶስ የተመለሱበት [አሁንም የሚመለሱበት] ነውና፡፡
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ከግብርናተ ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ኾኖ ተገኘ፡፡ የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም [መንፈሳዊ] ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ እውነትም [ወንጌልም] ወደ ዓለም ኹሉ ደርሷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም [ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው] ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በኹሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ [በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና] ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት [የረባት፣ የጠቀማት] ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
ክርስቶስ በቅዱስ መስቀል ላይ ተሰቀለ፤ ዲያብሎስም በድን ኾነ፡፡ ክርስቶስ በቅዱስ መስቀል ላይ እጆቹን ዘረጋ፤ ለዓለምም የመዳን መንገድ ተሰጠ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተቸነከረ፤ ነፍሳትም ኹሉ ከእስራታቸው ተፈቱ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ዋለ፤ ፍጥረታትም ኹሉ ከጥፋት ባርነት ነፃ ወጡ፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ፤ እንግዳ ነገርም ለዓለም ኹሉ ታየ ፀሐይ ብርሃኗን ከለከለች ንዑድ ክቡር የሚኾን ነቢዩ አሰምቶ እንደ ተናገረው - እንዲህ ሲል፡- “በዚያን ቀን ፀሐይ በቀትር ይገባል፤ ብርሃንም በምድር ላይ በቀን ይጨልማል” (አሞ.8፡9)፡፡ ተወዳጆች ሆይ! የነቢዩ ቃል እንደ ምን ያለ ግሩም ምሥጢር በውስጡ ቋጥሮ እንደ ያዘ ታያላችሁን? እዚህ ላይ የኹላቸውም -የእስራኤላውያንም የአሕዛብም - ግብር ተገልጧል፤ ኹላቸውም በአንድነት በድለዋልና፡፡
እንደ ኦሪቱ ሕግ በዓላትን የሚያከብሩት ያዝናሉ፤ በመዝሙር ፈንታም በኢየሩሳሌም ላይ.ያለቅሳሉ፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ኢየሩሳሌም የተቀደሱትን ሥርዓተ አምልኮዎችን ይዛ አትቀጥልምና፤ ከእንግዲህ ወዲህም በእርሷ ዘንድ በዓላት አይከበሩምና፡፡ የአሕዛብ አገራትም እንደዚሁ ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ ያዝናሉ፤ መጽሐፍ “የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው” እንዳለ ኀዘን የበረከት ምንጭ ነውና ይተክዛሉ (ማቴ.5፡4)፡፡ አዎ! ትርጉም ለሌላቸው በዓላቶቻቸውና ሥርዓት ለሌላቸው ዘፈኖቻቸው ለርኵሳት መናፍስት ይቀርብ እንደ ነበረ ዐውቀው ያዝናሉ፤ ይተክዛሉም፡፡ ዛሬ አሕዛብ ያከናውኑአቸው ለነበሩት ክፉ ክፉ ነገሮች እንዴት እንደሚጸጸቱባቸው አስተውሉ፤ ከነቢዩ ጋር በአንድነት እንዲህ ይላሉና፡- “በድለናል፤ በሐፍረታችንም ጠፍተናል፤ በዓመፃ ተሞልተናልና ኃጢአታችን ሸፍናናለች፡፡ እንደ አባቶቻችን በድለናል፡፡”
እንግዲያውስ እኛም ስለ ሠራናቸው ኃጣውእ እናልቅስ፤ እንዘንም፡፡ ተስፋችንን በእርሱ ላይ.አኑረን ወደ ቅዱስ መስቀሉ እንጠጋ፡፡ እኛ ሥራ ሠርተን አንበቃምና ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብሩና ጌትነቱ አንድ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነትና ሰውን መውደድ የመንግሥቱ ወራሾች እንኾን ዘንድ በመስቀሉ [ቃል] ተምረን አሳባችንን በሰማያት እናኑር፤ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ለዓለም ወለዓለም፥ አሜን!!!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
🟢🟡🔴
✨መስከረም 17 | #በዓለ_መስቀል ✨
🌼◦✞◦🌼
መስከረም ዐሥራ ሰባት በዚች ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ለከበረ መስቀል በዓሉ ነው። ይህም የጻድቁ ንጉሥ የቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት ዕሌኒ ከተሠወረበት የገለጠችው ነው።
የጎልጎታን ኮረብታ በአስጠረገች ጊዜ የከበረ መስቀልን አገኘችው። ታላቅ ኮረብታም የሆነበት ምክንያት እንዲህ ነው፦
ብዙዎች ድንቆች ተአምራት ክብር ይግባውና ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመቃብሩና ከመስቀሉ የሚገለጡ ሁነው ሙታን ይነሡ ነበርና የጎበጡና በሽተኞች ሁሉ ይፈወሱ ነበር።
ስለዚህም አይሁድ ተቆጡ እንዲህም ሥርዓትን ሠርተው አዘዙ። "በይሁዳ አገር ሁሉና በኢየሩሳሌም ቤቱን የሚጠርግ ሁሉ ወይም አፈር ወይም ጉድፍ የሚጠርግ በናዝሬቱ ኢየሱስ መቃብር ላይ ይጥል ዘንድ" እንዲህም እያደረጉ ዕሌኒ ንግሥት እስከ መጣች ድረስ ከሦስት መቶ ዓመት በላይ ኖሩ።
እርሷም በመጣች ጊዜ ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብርን እስከ አሳዩዋት ድረስ አይሁድን ይዛ አሠቃየቻቸው። ያንን ኮረብታም እስከ ጠረጉ ድረስ አስገደደቻቸው የከበረ መስቀሉም ከተቀበረበት ተገልጦ ወጣ።
ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራች። በዚች ቀንም አከበሯት። ለመስቀሉም በዓልን መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን አከበሩለት።
✨ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በምሕረቱ አደረሳችሁ ✨
🌼◦✞◦🌼
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
✨መስከረም 17 | #በዓለ_መስቀል ✨
🌼◦✞◦🌼
መስከረም ዐሥራ ሰባት በዚች ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ለከበረ መስቀል በዓሉ ነው። ይህም የጻድቁ ንጉሥ የቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት ዕሌኒ ከተሠወረበት የገለጠችው ነው።
የጎልጎታን ኮረብታ በአስጠረገች ጊዜ የከበረ መስቀልን አገኘችው። ታላቅ ኮረብታም የሆነበት ምክንያት እንዲህ ነው፦
ብዙዎች ድንቆች ተአምራት ክብር ይግባውና ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመቃብሩና ከመስቀሉ የሚገለጡ ሁነው ሙታን ይነሡ ነበርና የጎበጡና በሽተኞች ሁሉ ይፈወሱ ነበር።
ስለዚህም አይሁድ ተቆጡ እንዲህም ሥርዓትን ሠርተው አዘዙ። "በይሁዳ አገር ሁሉና በኢየሩሳሌም ቤቱን የሚጠርግ ሁሉ ወይም አፈር ወይም ጉድፍ የሚጠርግ በናዝሬቱ ኢየሱስ መቃብር ላይ ይጥል ዘንድ" እንዲህም እያደረጉ ዕሌኒ ንግሥት እስከ መጣች ድረስ ከሦስት መቶ ዓመት በላይ ኖሩ።
እርሷም በመጣች ጊዜ ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብርን እስከ አሳዩዋት ድረስ አይሁድን ይዛ አሠቃየቻቸው። ያንን ኮረብታም እስከ ጠረጉ ድረስ አስገደደቻቸው የከበረ መስቀሉም ከተቀበረበት ተገልጦ ወጣ።
ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራች። በዚች ቀንም አከበሯት። ለመስቀሉም በዓልን መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን አከበሩለት።
✨ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በምሕረቱ አደረሳችሁ ✨
🌼◦✞◦🌼
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ
****
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኅንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ቦታው በዓታ ለማርያም በተባለው ቦታ 1934 ዓ.ም ተወለዱ።
ፊደልና ንባብና የቃል ትምሕርት በመማር ለግብረ ዲቁና የሚያበቃቸውን ትምሕርት ከየኔታ ክንፈ ገብርኤል በመማር ማዕረገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ዜማ ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም ተንቤን፤ ቅኔ ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም ተንቤን እንዲሁም ቅኔን ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ ጎንደር ትርጓሜ መጻሕፍት፣ እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትባል ገዳም ፤ ቅኔና ትርጓሜ መጽሐፍት እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሣነ ወርቅ ጎጃም ፤ ቅኔ ከየኔታ ዲበኩሉ ጎጃም በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህርነት በቅተዋል፡፡
በተጨማሪም መዝገብ ቅዳን ከየኔታ ልዑል ቦረራ ሚካኤል ተምረዋል፡፡በወቅቱ የጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ የቅስናና የቁምስና ማዕረግ ተቀብለዋል፡፡ብፁዕነታቸው በሊቀ ጵጵስና በአክሱም፣በምሥራቅ ሐረርጌና በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም አገልግለዋል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
****
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኅንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ቦታው በዓታ ለማርያም በተባለው ቦታ 1934 ዓ.ም ተወለዱ።
ፊደልና ንባብና የቃል ትምሕርት በመማር ለግብረ ዲቁና የሚያበቃቸውን ትምሕርት ከየኔታ ክንፈ ገብርኤል በመማር ማዕረገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ዜማ ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም ተንቤን፤ ቅኔ ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም ተንቤን እንዲሁም ቅኔን ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ ጎንደር ትርጓሜ መጻሕፍት፣ እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትባል ገዳም ፤ ቅኔና ትርጓሜ መጽሐፍት እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሣነ ወርቅ ጎጃም ፤ ቅኔ ከየኔታ ዲበኩሉ ጎጃም በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህርነት በቅተዋል፡፡
በተጨማሪም መዝገብ ቅዳን ከየኔታ ልዑል ቦረራ ሚካኤል ተምረዋል፡፡በወቅቱ የጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ የቅስናና የቁምስና ማዕረግ ተቀብለዋል፡፡ብፁዕነታቸው በሊቀ ጵጵስና በአክሱም፣በምሥራቅ ሐረርጌና በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም አገልግለዋል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን
@ortodoxtewadochannal
@ortodoxtewadochannal
የብፁእ አቡነ ሰላማ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተከናወነ ይገኛል።
#እንኳን_አደረሳቹሁ
ቴሌግራም ቻናል⤵️
🥀በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!
መስከረም 21-ብዙኃን ማርያም (የእመቤታችን የበዓሏ መታሰቢያ ነው፡፡)
🥀ዳግመኛም በዚኽች ዕለት አስቀድሞ ኃይለኛ ሥራየኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም አምኖ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ አንገቱን የተሰየፈው ቅዱስ ቆጵርያኖስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት ነው፡፡
🥀ቆጵርያኖስን ያሳመነችውና ስሟ በተጠራበት ቦታ ሰይጣናት እንደ ትቢያ በነው የጠፉት ድንግሊቱ ዮስቴናም በሰማዕትነት ያረፈችው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
🥀ዳግመኛም ይህች ዕለት የከበሩ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ አበው ሊቃውንት በ325 ዓ.ም አርዮስን አስተምለው ለመመለስ በኒቅያ የተሰበሰቡባት ዕለት ናት፡፡ የጉባኤውም ፍጻሜ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ኅዳር ዘጠኝ ነው፡፡
+ የጌታችን ቅዱስ መስቀል ግሸን ደብረ ከርቤ የገባበት ዕለት ነው፡፡ (የመስከረም ዓሥራ ሰባቱን ይመለከቷል፡፡)
🥀 ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ጢባርዮስ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡
ቅዱስ ቆጵርያኖስና ድንግሊቱ ዮስቴና፡- ይኽም ቆጵርያኖስ አስቀድሞ ከሃዲና ሥራየኛ ነበር፡፡ እንዲያውም ለሥራየኖች ሁሉ አለቃቸው ነበር፡፡ በዚህ በጥንቆላ ሥራው ከመመካቱ የተነሣ ‹‹ሥራይ በማድረግ የሚስተካከለኝ ካለ ልይ እስቲ…›› በማለት ወደ አንጾኪያ አገር ሄደ፡፡ ቆጵርያኖስም አንጾኪያ በገባ ጊዜ ወሬው ሁሉ በሀገሪቱ ተሰማ፡፡ በአንጾኪያ የሚኖር አንድ ወጣት በመልኳ እጅግ ውብ የሆነችውን ወጣት ዮስቴናን ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትሄድ እያያት እጅግ አድርጎ ወደዳት ነገር ግን እርሷ የክርስቶስ ሙሽራ ናትና እሺ ልትለው ስላልቻለች ሊያገኛት አልቻለም፡፡ ገንዘብ በመስጠት፣ በጉልበት በማስፈራራት፣ በሥራይ ሥራ በእነዚህ ሁሉ ሊያገኛት ስላልቻለ ወጣቱ አሁን የቆጵርያኖስን ወደ ከተማው መምጣትና ዝናውን በሰማ ጊዜ ደስ ብሎት ሄዶ ዮስቴናን እጅግ አድርጎ እንደወደዳትና ሊያገኛት እንዳልቻለ ነገረው፡፡
ቆጵርያኖስም ያንን ወጣት ‹‹እኔ የልብህን እፈጽምልሃለሁ አትዘን›› አለው፡፡
🥀ከዚህምም በኋላ ቆጵርያኖስ ድንግሊቱን ዮስቴናን እንዲያመጧት በሥራዩ የአጋንንትን ሠራዊት ላካቸው፡፡ እነዚያ በሥራይ ወደ እርሷ ተላኩ አጋንንትም ወደ ድንግሊቱ ዮስቴና በፍጹም ሊቀርቧት አልቻሉም ምክንያቱም እርሷ ዮስቴና በጾም በጸሎቷ የጸናች ናትና ከጸሎቷ የተነሣ አጋንንቱ ተቃጠሉ፡፡ ቆጵርያኖስ በሥራዩ ኃይል ዮስቴናን ያመጡለት ዘንድ ደጋግሞ ላካቸው ነገር ግን አጋንንቱ ቅድስት ዮስቴና በፍጹም ሊቀርቧት አልቻሉም፡፡ ከዚም በኋላ ቆጵርያኖስ ሁሉንም አጋንንት ጠርቶ ‹‹ድንግል ዮስቴናን ይዛችሁ ካላመጣችሁልኝ እኔ ከእናንተ ተለይቼ ክርስቲያን እሆናለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የሰይጣናት አለቃ ቆጵርያኖስን ሊሸነግለው አሰበና ከሰይጣናት ውስጥ አንዱን ሰይጣን በዮስቴና ተመስሎ ለቆጵርያኖስ እንዲታየው አደረገ፡፡ ሰይጣኑም አለቃው እንዳዘዘው እንዲሁ አድርጎ (ዮስቴናን መስሎ) ተዘጋጀ፡፡
🥀ሰይጣኑም ለቆጵርያኖስ ‹‹እነሆ አሁን ዮስቴና መጥታለች›› አለው፡፡ ቆጵርያኖስም እውነት ዮስቴና የመጣች መስሎት እጅግ ደስ ብሎት ሊቀበላት ተነሣ፡፡ በዮስቴና አርአያ የተመሰለውንም ምትሀት ባየ ጊዜ ‹‹የሴቶች እመቤት ዮስቴና ሆይ! መምጣትሽ መልካም ሆነ›› አላት፡፡ ቆጵርያኖስም የቅድስት ዮስቴናን ስሟን መጥራት በጀመረ ጊዜ በእርሷ ተመሰለው ሰይጣን እንደጢስ በኖ ጠፋ፡፡
🥀ቆጵርያኖስም በዚህ ጊዜ የሽንገላው ምክንያት ምትሐቱ ሁሉ ከንቱ እንደሆነ ዐወቀ፣ አስተዋለ፡፡ በልቡም እንዲህ አለ፡- ‹‹ስሟን በጠሩበት ቦታ አጋንንት እንደ እንደጢስ የሚበኑ ከሆነ በቅድስት ዮስቴና ፊት ሊቆሙ ሊሸነግሏትስ እንዴት ይቻላቸዋል?›› አለ፡፡ ይህንንም ብሎ ወዲያውኑ የጥንቆላ መጻሕፍቶቹን አቃጠላቸው፡፡ ሄዶም ቅድስት ዮስቴናን አገኛትና ሰገደላት፡፡ እርሷም ሃይማኖትን አስተማረችውና ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ ሄዶ ንስሓ ገብቶ ተምሮ አምኖ ተጠመቀ፡፡ የምንኩስና ልብስንም ለበሰ፡፡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ዲቁና ሾመው፡፡ አገልግሎቱንና መንፈሳዊ ተጋድሎውንም ባየ ጊዜ ዳግመኛም ቅስና ሾመው፡፡
🥀ቆጵርያኖስም በተጋድሎና በአገልግሎት ከኖረ በጎ ምግባሩ፣ ሃይማኖት፣ ትሩፋቱ ከፍ ባለ ጊዜ በምዕራባዊቷ ግዛት ኤጲስ ቆጶስነት ተሾመ፡፡ ቅድስት ዮስቴናንም ወስዶ ለደናግል ገዳም እመ ምኔት አደረጋት፡፡
በግርጣግና የቅዱሳን ስብሰባ በሆነ ጊዜ ቅዱስ ቆጵርያኖስ ከጉባው አባላት አንዱ ነበር፡፡ ከብዙ ወራት በኋላም ከሃዲው ንጉሥ ዳኬዎስም ስለ ቅዱስ ቆጵርያኖስና ስለ ቅድስት ዮስቴና ሰማ፡፡ ንጉሡም ወደ እርሱ አስመጣቸውና የክብርን ባለቤት ክርስቶስን ክደው ለጣኦት እንዲሰግዱ አዘዛቸው፡፡ ቅዱስ ቆጵርያኖስና ቅድስት ዮስቴና ግን የጌታችንን አምላክነት ክብር በመመስከር ጣዖታቱን ረገሙበት፡፡ ንጉሡም እነርሱ ክርስቶስን በማመን እስከመጨረሻው ድረስ መጽናታቸውን ባየ ጊዜ ልዩ ልዩ በሆኑ ጽኑ ሥቃዮች እጅግ አድርጎ አሠቃያቸው፡፡ በመጨረሻም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ የቅዱስ ቆጵርያኖስን የቅድስት ዮስቴን እንዲሁም የሌሎች ሦስት ወንዶችን በየተራ ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ አስቆረጣቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
«ግሸን ደብረ ከርቤ»
🥀ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
🥀ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ
ቴሌግራም ቻናል⤵️
🥀በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!
መስከረም 21-ብዙኃን ማርያም (የእመቤታችን የበዓሏ መታሰቢያ ነው፡፡)
🥀ዳግመኛም በዚኽች ዕለት አስቀድሞ ኃይለኛ ሥራየኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም አምኖ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ አንገቱን የተሰየፈው ቅዱስ ቆጵርያኖስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት ነው፡፡
🥀ቆጵርያኖስን ያሳመነችውና ስሟ በተጠራበት ቦታ ሰይጣናት እንደ ትቢያ በነው የጠፉት ድንግሊቱ ዮስቴናም በሰማዕትነት ያረፈችው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
🥀ዳግመኛም ይህች ዕለት የከበሩ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ አበው ሊቃውንት በ325 ዓ.ም አርዮስን አስተምለው ለመመለስ በኒቅያ የተሰበሰቡባት ዕለት ናት፡፡ የጉባኤውም ፍጻሜ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ኅዳር ዘጠኝ ነው፡፡
+ የጌታችን ቅዱስ መስቀል ግሸን ደብረ ከርቤ የገባበት ዕለት ነው፡፡ (የመስከረም ዓሥራ ሰባቱን ይመለከቷል፡፡)
🥀 ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ጢባርዮስ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡
ቅዱስ ቆጵርያኖስና ድንግሊቱ ዮስቴና፡- ይኽም ቆጵርያኖስ አስቀድሞ ከሃዲና ሥራየኛ ነበር፡፡ እንዲያውም ለሥራየኖች ሁሉ አለቃቸው ነበር፡፡ በዚህ በጥንቆላ ሥራው ከመመካቱ የተነሣ ‹‹ሥራይ በማድረግ የሚስተካከለኝ ካለ ልይ እስቲ…›› በማለት ወደ አንጾኪያ አገር ሄደ፡፡ ቆጵርያኖስም አንጾኪያ በገባ ጊዜ ወሬው ሁሉ በሀገሪቱ ተሰማ፡፡ በአንጾኪያ የሚኖር አንድ ወጣት በመልኳ እጅግ ውብ የሆነችውን ወጣት ዮስቴናን ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትሄድ እያያት እጅግ አድርጎ ወደዳት ነገር ግን እርሷ የክርስቶስ ሙሽራ ናትና እሺ ልትለው ስላልቻለች ሊያገኛት አልቻለም፡፡ ገንዘብ በመስጠት፣ በጉልበት በማስፈራራት፣ በሥራይ ሥራ በእነዚህ ሁሉ ሊያገኛት ስላልቻለ ወጣቱ አሁን የቆጵርያኖስን ወደ ከተማው መምጣትና ዝናውን በሰማ ጊዜ ደስ ብሎት ሄዶ ዮስቴናን እጅግ አድርጎ እንደወደዳትና ሊያገኛት እንዳልቻለ ነገረው፡፡
ቆጵርያኖስም ያንን ወጣት ‹‹እኔ የልብህን እፈጽምልሃለሁ አትዘን›› አለው፡፡
🥀ከዚህምም በኋላ ቆጵርያኖስ ድንግሊቱን ዮስቴናን እንዲያመጧት በሥራዩ የአጋንንትን ሠራዊት ላካቸው፡፡ እነዚያ በሥራይ ወደ እርሷ ተላኩ አጋንንትም ወደ ድንግሊቱ ዮስቴና በፍጹም ሊቀርቧት አልቻሉም ምክንያቱም እርሷ ዮስቴና በጾም በጸሎቷ የጸናች ናትና ከጸሎቷ የተነሣ አጋንንቱ ተቃጠሉ፡፡ ቆጵርያኖስ በሥራዩ ኃይል ዮስቴናን ያመጡለት ዘንድ ደጋግሞ ላካቸው ነገር ግን አጋንንቱ ቅድስት ዮስቴና በፍጹም ሊቀርቧት አልቻሉም፡፡ ከዚም በኋላ ቆጵርያኖስ ሁሉንም አጋንንት ጠርቶ ‹‹ድንግል ዮስቴናን ይዛችሁ ካላመጣችሁልኝ እኔ ከእናንተ ተለይቼ ክርስቲያን እሆናለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የሰይጣናት አለቃ ቆጵርያኖስን ሊሸነግለው አሰበና ከሰይጣናት ውስጥ አንዱን ሰይጣን በዮስቴና ተመስሎ ለቆጵርያኖስ እንዲታየው አደረገ፡፡ ሰይጣኑም አለቃው እንዳዘዘው እንዲሁ አድርጎ (ዮስቴናን መስሎ) ተዘጋጀ፡፡
🥀ሰይጣኑም ለቆጵርያኖስ ‹‹እነሆ አሁን ዮስቴና መጥታለች›› አለው፡፡ ቆጵርያኖስም እውነት ዮስቴና የመጣች መስሎት እጅግ ደስ ብሎት ሊቀበላት ተነሣ፡፡ በዮስቴና አርአያ የተመሰለውንም ምትሀት ባየ ጊዜ ‹‹የሴቶች እመቤት ዮስቴና ሆይ! መምጣትሽ መልካም ሆነ›› አላት፡፡ ቆጵርያኖስም የቅድስት ዮስቴናን ስሟን መጥራት በጀመረ ጊዜ በእርሷ ተመሰለው ሰይጣን እንደጢስ በኖ ጠፋ፡፡
🥀ቆጵርያኖስም በዚህ ጊዜ የሽንገላው ምክንያት ምትሐቱ ሁሉ ከንቱ እንደሆነ ዐወቀ፣ አስተዋለ፡፡ በልቡም እንዲህ አለ፡- ‹‹ስሟን በጠሩበት ቦታ አጋንንት እንደ እንደጢስ የሚበኑ ከሆነ በቅድስት ዮስቴና ፊት ሊቆሙ ሊሸነግሏትስ እንዴት ይቻላቸዋል?›› አለ፡፡ ይህንንም ብሎ ወዲያውኑ የጥንቆላ መጻሕፍቶቹን አቃጠላቸው፡፡ ሄዶም ቅድስት ዮስቴናን አገኛትና ሰገደላት፡፡ እርሷም ሃይማኖትን አስተማረችውና ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ ሄዶ ንስሓ ገብቶ ተምሮ አምኖ ተጠመቀ፡፡ የምንኩስና ልብስንም ለበሰ፡፡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ዲቁና ሾመው፡፡ አገልግሎቱንና መንፈሳዊ ተጋድሎውንም ባየ ጊዜ ዳግመኛም ቅስና ሾመው፡፡
🥀ቆጵርያኖስም በተጋድሎና በአገልግሎት ከኖረ በጎ ምግባሩ፣ ሃይማኖት፣ ትሩፋቱ ከፍ ባለ ጊዜ በምዕራባዊቷ ግዛት ኤጲስ ቆጶስነት ተሾመ፡፡ ቅድስት ዮስቴናንም ወስዶ ለደናግል ገዳም እመ ምኔት አደረጋት፡፡
በግርጣግና የቅዱሳን ስብሰባ በሆነ ጊዜ ቅዱስ ቆጵርያኖስ ከጉባው አባላት አንዱ ነበር፡፡ ከብዙ ወራት በኋላም ከሃዲው ንጉሥ ዳኬዎስም ስለ ቅዱስ ቆጵርያኖስና ስለ ቅድስት ዮስቴና ሰማ፡፡ ንጉሡም ወደ እርሱ አስመጣቸውና የክብርን ባለቤት ክርስቶስን ክደው ለጣኦት እንዲሰግዱ አዘዛቸው፡፡ ቅዱስ ቆጵርያኖስና ቅድስት ዮስቴና ግን የጌታችንን አምላክነት ክብር በመመስከር ጣዖታቱን ረገሙበት፡፡ ንጉሡም እነርሱ ክርስቶስን በማመን እስከመጨረሻው ድረስ መጽናታቸውን ባየ ጊዜ ልዩ ልዩ በሆኑ ጽኑ ሥቃዮች እጅግ አድርጎ አሠቃያቸው፡፡ በመጨረሻም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ የቅዱስ ቆጵርያኖስን የቅድስት ዮስቴን እንዲሁም የሌሎች ሦስት ወንዶችን በየተራ ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ አስቆረጣቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
«ግሸን ደብረ ከርቤ»
🥀ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
🥀ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ