SRATEBETKRSTYANE Telegram 7591
D#ነገረ #ክርስቶስ #ክፍል #፵
ጌታ ክርስቶስ በባሕርይው ፍቅር ነው። ይህ ማለት ጥላቻ አይስማማውም ማለት ነው። አይሁድ እርሱን ጌታን ከኃጢአተኞችና ከቀራጮች ጋር ሲበላ አይተውት ነቅፈውት ነበር። "የቀራጮችና የኃጢአተኛዎች ወዳጅ" ብለውታል (ማቴ. ፲፩፣፲፱)። ኢየሱስ ኃጢኣታችን እንደ ምድር አሸዋ የበዛ ቢሆን እንኳ ንስሓ ብንገባ ይቅር የሚል አምላክ ስለሆነ ኃጥአንን ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ ምክንያት ለመሆን አብሯቸው ይበላ ይጠጣ ነበር። 

ጌታ ሰዎች ተአምራቱን አይተው፣ ትምህርቱን ሰምተው ከኃጢአታቸው ተመልሰው መልካም ሥራን ይሠሩ ዘንድ በከተማዎችና በመንደሮች እየተመላለሰ ያስተምር ነበር። ነገር ግን ይህ ሁሉ ተደርጎላቸው ከኃጢአታቸው ያልተመለሱ ሀገሮች ስለነበሩ ወዮልሽ ኮራዚ ወዮልሽ ቤተሳይዳ እያለ ወቅሷቸዋል። በፍርድ ቀን መከራ እንደሚበዛባቸውም ነግሯቸዋል (ማቴ. ፲፩፣፳-፳፭)። ጌታ ኃጥአንን እንጂ ኃጢአታቸውን አይወድም። ኃጥአንን ከኃጢአታቸው ለመለየት ብዙ ተአምራትን አሳይቷል። ነገር ግን በባሕርይው ፍቅር የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርይው በትክክል የሚፈርድ (ፈታሒ በርትዕ) ስለሆነ ለሁሉም እንደየሥራው ይከፍለዋል። ፍቅሩና ፍርዱ የተስማማለት ጌታ ነው።

ስለዚህ ኢየሱስ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነው እያልን ኃጥአን እንሁን ማለት ትልቅ በደል ነው። ጌታ ኃጥአንን በባሕርያቸው ይወዳቸዋል በግብራቸው ግን ይጠላቸዋል። ጻድቃንን ደግሞ በባሕርያቸውም በግብራቸውም ይወዳቸዋል። ስለዚህ እንደ ጻድቃን በግብርም ለመወደድ መልካም ሥራን መሥራት ይገባናል።



tgoop.com/sratebetkrstyane/7591
Create:
Last Update:

D#ነገረ #ክርስቶስ #ክፍል #፵
ጌታ ክርስቶስ በባሕርይው ፍቅር ነው። ይህ ማለት ጥላቻ አይስማማውም ማለት ነው። አይሁድ እርሱን ጌታን ከኃጢአተኞችና ከቀራጮች ጋር ሲበላ አይተውት ነቅፈውት ነበር። "የቀራጮችና የኃጢአተኛዎች ወዳጅ" ብለውታል (ማቴ. ፲፩፣፲፱)። ኢየሱስ ኃጢኣታችን እንደ ምድር አሸዋ የበዛ ቢሆን እንኳ ንስሓ ብንገባ ይቅር የሚል አምላክ ስለሆነ ኃጥአንን ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ ምክንያት ለመሆን አብሯቸው ይበላ ይጠጣ ነበር። 

ጌታ ሰዎች ተአምራቱን አይተው፣ ትምህርቱን ሰምተው ከኃጢአታቸው ተመልሰው መልካም ሥራን ይሠሩ ዘንድ በከተማዎችና በመንደሮች እየተመላለሰ ያስተምር ነበር። ነገር ግን ይህ ሁሉ ተደርጎላቸው ከኃጢአታቸው ያልተመለሱ ሀገሮች ስለነበሩ ወዮልሽ ኮራዚ ወዮልሽ ቤተሳይዳ እያለ ወቅሷቸዋል። በፍርድ ቀን መከራ እንደሚበዛባቸውም ነግሯቸዋል (ማቴ. ፲፩፣፳-፳፭)። ጌታ ኃጥአንን እንጂ ኃጢአታቸውን አይወድም። ኃጥአንን ከኃጢአታቸው ለመለየት ብዙ ተአምራትን አሳይቷል። ነገር ግን በባሕርይው ፍቅር የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርይው በትክክል የሚፈርድ (ፈታሒ በርትዕ) ስለሆነ ለሁሉም እንደየሥራው ይከፍለዋል። ፍቅሩና ፍርዱ የተስማማለት ጌታ ነው።

ስለዚህ ኢየሱስ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነው እያልን ኃጥአን እንሁን ማለት ትልቅ በደል ነው። ጌታ ኃጥአንን በባሕርያቸው ይወዳቸዋል በግብራቸው ግን ይጠላቸዋል። ጻድቃንን ደግሞ በባሕርያቸውም በግብራቸውም ይወዳቸዋል። ስለዚህ እንደ ጻድቃን በግብርም ለመወደድ መልካም ሥራን መሥራት ይገባናል።

BY ✝️ስርዓተ ቤተክርስቲያን መመሪያ ✝️


Share with your friend now:
tgoop.com/sratebetkrstyane/7591

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.” Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. Telegram channels fall into two types: Some Telegram Channels content management tips
from us


Telegram ✝️ስርዓተ ቤተክርስቲያን መመሪያ ✝️
FROM American