TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ 5ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 4ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች በመርሃግብሩ እውቅና አግኝተዋል፡፡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ፎቶ ክሬዲት ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን እና ኦኤምኤን @tikvahethiopia
" ስለተፈጠረው ስህተት ህዝባችንን ይቅርታ እንጠይቃለን። ለአርቲስት አንዷለም ጎሳ የሰጠነው ሽልማት ተሰርዟል ! " - ፋውንዴሽኑ
የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ባዘጋጀው 4ኛው የሃጫሉ አዋርድ ላይ በምርጥ ወንድ ድምጻዊ ዘርፍ አሸናፊ አድርጎ የመረጠውን የአርቲስት አንዷለም ጎሳን ሽልማት መሰረዙን ገልጿል።
ሽልማቱ በተለይም የወጣት ቀነኒ አዱኛ ጥቃትን የሚያመለክቱ ፎቶዎችና ቪዲዮዎች በስፋት በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ከተለቀቁ በኋላ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።
በዚህም ሽልማቱ እንዲነሳ የ24 ሰዓት የማኅበራዊ ሚዲያ ንቅናቄዎች ሲካሄዱ ነበር። ውሳኔውም ይኸው የሰዓት ገደብ ካበቃ ከሰዓታት በኋላ የተላለፈ ነው።
ፋውንዴሽኑ በመግለጫው ሽልማቱን ጉዳዩን ከሚመለከተው የህግ አካል የተጻፈ ደብዳቤ ይዘን የሸለምን ቢሆንም ከህዝብ በደረሰን አስተያየት ውሳኔያችን ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ሲል ገልጿል።
አክሎም " ስለተፈጠረው ስህተት ህዝባችንን ይቅርታ እየጠየቅን ለአርቲስት አንዷለም ጎሳ የሰጠነው ሽልማት የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን " ሲል አስታውቋል።
Via @TikvahethMagazine
የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ባዘጋጀው 4ኛው የሃጫሉ አዋርድ ላይ በምርጥ ወንድ ድምጻዊ ዘርፍ አሸናፊ አድርጎ የመረጠውን የአርቲስት አንዷለም ጎሳን ሽልማት መሰረዙን ገልጿል።
ሽልማቱ በተለይም የወጣት ቀነኒ አዱኛ ጥቃትን የሚያመለክቱ ፎቶዎችና ቪዲዮዎች በስፋት በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ከተለቀቁ በኋላ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።
በዚህም ሽልማቱ እንዲነሳ የ24 ሰዓት የማኅበራዊ ሚዲያ ንቅናቄዎች ሲካሄዱ ነበር። ውሳኔውም ይኸው የሰዓት ገደብ ካበቃ ከሰዓታት በኋላ የተላለፈ ነው።
ፋውንዴሽኑ በመግለጫው ሽልማቱን ጉዳዩን ከሚመለከተው የህግ አካል የተጻፈ ደብዳቤ ይዘን የሸለምን ቢሆንም ከህዝብ በደረሰን አስተያየት ውሳኔያችን ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ሲል ገልጿል።
አክሎም " ስለተፈጠረው ስህተት ህዝባችንን ይቅርታ እየጠየቅን ለአርቲስት አንዷለም ጎሳ የሰጠነው ሽልማት የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን " ሲል አስታውቋል።
Via @TikvahethMagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
" የአሁኑ ጥቃት ከከዚህ ቀደሙ ከበድ ያለ ነበር " የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ፤ በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " በሰጠው ቃል ፤ በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሚገኘው ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና 3 የአካባቢው ነዋሪዎች…
" ወደ 80 ሚሊዮን ብር የሚመት ንብረት ነው በታጣቂዎቹ የወደመው። ይሄ ለፋብሪካችን ቀላል ሀብት አይደለም " - ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ
" ታግተው የነበሩ 17 ሠራተኞች ተለቀዋል ! "
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሱሉለ ፊንጫ ወረዳ ታጣቂዎች የፋብሪካውን ሠራተኞች አታግተው ወስደው እንደነበርና በተሽከርካሪዎቹ ላይ ቃጠሎ እንዳደረሱበት ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ታጣቂዎች በፋብሪካው ፈጸሙት ስለተባለው እገታ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ ኃይለማርያም፣ " 17 ሰዎች ትላንትና ማታ ተለቀው ወደ ቤተሰባቸው ገብተዋል። ጥቃቱ ትክክል ነው ተፈጽሟል። ሥራ ቦታ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ናቸው አግተው የወሰዷቸው" ሲሉ ነግረውናል።
" በአንድ ሎደር እና ሀይሉክስ ቶዮታ ተሽከርካሪዎች ነው ውድመት የደረሰው " ያሉ ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ የእገታ ጥቃቱና የንብረት ውድመቱ ያደረሱት ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ መሆኑ ተመልክቷል።
የንብረት ውድመቱ በገንዘብ ሲተመን ምን ያክል እንደሆነ ላቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ መንግስቱ፣ " ወደ 80 ሚሊዮን ብር የሚመት ንብረት ነው በታጣቂዎቹ የወደመው። ይሄ ደግሞ ለፋብሪካችን ቀላል ሀብት አይደለም " ሲሉም የጉዳቱን ክብደት አጽንኦት ሰጥተውበታል።
" የሚያሳዝን ነገር ነው። ድርጅቱ በደንብ ወደ ሥራ ተመልሶ እየሰራ ባለበት ወቅት ባልተጠበቀ ሁኔታ ነው ይሄ ጉዳት የደረሰው " ሲሉም ሁነቱን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ታጋቾቹን በምን መልኩ ነው ከእገታ ማስለቀቅ የተቻለው? አጋቾቹ ከፍተኛ ገንዘብ እየጠየቁ እንደነበር ተሰምቷል፤ ሠራኞቹ የተለቀቁት ገንዘብ ተከፍሎ ነው ? ሲል ሥራ አስኪያጁን ጠይቋል።
እሳቸውም፣ " የኛም ሠራተኞች ሥራ ላይ ነበሩ፤ ጉዳቱ እንደተሰማ የጸጥታ አካላት ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። የፌደራል ፓሊስና ኮማንዶ ኃይልም ሰፊ ርብርብ አድርገው በሄዱበት ቦታ ሂዶ ሰዎቹን ለማዳን ተሳትፈው ነበር በእለቱ ግን ማግኘት አልቻሉም " ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
" በማግስቱ የመከላከያ ኃይልም ተጨምሮ ሰፊ የሆነ ውይይትና ሰፊ አሰሳም አድርጓል። ግን ታጋቾቹ በራሳቸው ጊዜ ተለቀዋል የሚል መረጃ ስላገኘን የፋብሪካው አመራሮች ሰዎቹ አለን ካሉበት ቦታ ላይ ሂደው በመኪና ይዘዋቸው መጥተዋል " ሲሉም አክለዋል።
የገንዘብ ጥያቄውን በተመለከተ በሰጡን ምላሽ ደግሞ፣ " እሱን ማጣራት ይፈልጋል። እኔም እንዲህ አይነት መረጃ ሰምቼ ነበር፤ ግን ሰዎቹ ድንጋጤ ላይ ስለነበሩ እንኳን ደኀና ገባችሁ ከማለት ውጪ እንደከፈሉና እንዳልከፈሉ መጠየቅ/ማረጋገጥ አልተቻለም " ብለዋል።
" በድርጅቱ ሀብት ጉዳት የሚያደርሱ፣ አገዳን የሚያቃጥሉ ኃይሎችን ህዝቡ ከራሱ ነጥሎ ማውጣት አለበት። ሰላም ሆኗል ብለን ተስፋ ስናደርግ ችግር ያጋጥማል። ከህዝቡ ውስጥ ሆኖ መሳሪያ ታጥቆ ብቅ ጥልቅ እያለ የድርጅቱን ሀብት የሚያወድመውን ኃይል ተው ሊል ይገባል " ሲሉም ማህበረሱ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ታግተው የነበሩ 17 ሠራተኞች ተለቀዋል ! "
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሱሉለ ፊንጫ ወረዳ ታጣቂዎች የፋብሪካውን ሠራተኞች አታግተው ወስደው እንደነበርና በተሽከርካሪዎቹ ላይ ቃጠሎ እንዳደረሱበት ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ታጣቂዎች በፋብሪካው ፈጸሙት ስለተባለው እገታ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ ኃይለማርያም፣ " 17 ሰዎች ትላንትና ማታ ተለቀው ወደ ቤተሰባቸው ገብተዋል። ጥቃቱ ትክክል ነው ተፈጽሟል። ሥራ ቦታ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ናቸው አግተው የወሰዷቸው" ሲሉ ነግረውናል።
" በአንድ ሎደር እና ሀይሉክስ ቶዮታ ተሽከርካሪዎች ነው ውድመት የደረሰው " ያሉ ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ የእገታ ጥቃቱና የንብረት ውድመቱ ያደረሱት ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ መሆኑ ተመልክቷል።
የንብረት ውድመቱ በገንዘብ ሲተመን ምን ያክል እንደሆነ ላቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ መንግስቱ፣ " ወደ 80 ሚሊዮን ብር የሚመት ንብረት ነው በታጣቂዎቹ የወደመው። ይሄ ደግሞ ለፋብሪካችን ቀላል ሀብት አይደለም " ሲሉም የጉዳቱን ክብደት አጽንኦት ሰጥተውበታል።
" የሚያሳዝን ነገር ነው። ድርጅቱ በደንብ ወደ ሥራ ተመልሶ እየሰራ ባለበት ወቅት ባልተጠበቀ ሁኔታ ነው ይሄ ጉዳት የደረሰው " ሲሉም ሁነቱን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ታጋቾቹን በምን መልኩ ነው ከእገታ ማስለቀቅ የተቻለው? አጋቾቹ ከፍተኛ ገንዘብ እየጠየቁ እንደነበር ተሰምቷል፤ ሠራኞቹ የተለቀቁት ገንዘብ ተከፍሎ ነው ? ሲል ሥራ አስኪያጁን ጠይቋል።
እሳቸውም፣ " የኛም ሠራተኞች ሥራ ላይ ነበሩ፤ ጉዳቱ እንደተሰማ የጸጥታ አካላት ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። የፌደራል ፓሊስና ኮማንዶ ኃይልም ሰፊ ርብርብ አድርገው በሄዱበት ቦታ ሂዶ ሰዎቹን ለማዳን ተሳትፈው ነበር በእለቱ ግን ማግኘት አልቻሉም " ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
" በማግስቱ የመከላከያ ኃይልም ተጨምሮ ሰፊ የሆነ ውይይትና ሰፊ አሰሳም አድርጓል። ግን ታጋቾቹ በራሳቸው ጊዜ ተለቀዋል የሚል መረጃ ስላገኘን የፋብሪካው አመራሮች ሰዎቹ አለን ካሉበት ቦታ ላይ ሂደው በመኪና ይዘዋቸው መጥተዋል " ሲሉም አክለዋል።
የገንዘብ ጥያቄውን በተመለከተ በሰጡን ምላሽ ደግሞ፣ " እሱን ማጣራት ይፈልጋል። እኔም እንዲህ አይነት መረጃ ሰምቼ ነበር፤ ግን ሰዎቹ ድንጋጤ ላይ ስለነበሩ እንኳን ደኀና ገባችሁ ከማለት ውጪ እንደከፈሉና እንዳልከፈሉ መጠየቅ/ማረጋገጥ አልተቻለም " ብለዋል።
" በድርጅቱ ሀብት ጉዳት የሚያደርሱ፣ አገዳን የሚያቃጥሉ ኃይሎችን ህዝቡ ከራሱ ነጥሎ ማውጣት አለበት። ሰላም ሆኗል ብለን ተስፋ ስናደርግ ችግር ያጋጥማል። ከህዝቡ ውስጥ ሆኖ መሳሪያ ታጥቆ ብቅ ጥልቅ እያለ የድርጅቱን ሀብት የሚያወድመውን ኃይል ተው ሊል ይገባል " ሲሉም ማህበረሱ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🕊#Peace
" የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ ተቆጠቡ " - ጉባኤው
" በትግራይ የእርስ በርስ መተላለቅ የሚጋብዝ ፕሮጀክት የተወገዘና ተቀባይነት የሌለው ነው " አለ የትግራይ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ።
ጉባኤው የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ሲል በፅኑ ተማፅኗል።
" ህዝብን በማሳተፍ ለሰላም ፣ ለፍቅር ለፍትህና ለአንድነት እሰራለሁ " ሲል ያሳወቀው ጉባኤው " በመሪዎች መካከል የተፈጠረው ተግባብቶ ያለመስራት ችግር ህዝቡ ለስደት፣ ለመፈናቀልና ለሞት የዳረገ የሚወገዝ ተግባር ነው " ብሏል።
" ገና ከጦርነት ባለገገመች ትግራይ ትግራዋይ ከትግራዋይ ለመተላለቅ ያለመ ፕሮጀክት ተደግሷል " ያለው ጉባኤው " ይህ አደገኛ ፕሮጀክት ለትግራይ ህዝብ ታሪክ የማይመይጥን ነው " ብሎታል።
በአገር ውስጥና በመላ ዓለም የሚገኝ ትግራዋይ ሆደ ሰፊና አስተዋይ እንዲሆን መክሮ " በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ በጋራ እንቁም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ ተቆጠቡ " - ጉባኤው
" በትግራይ የእርስ በርስ መተላለቅ የሚጋብዝ ፕሮጀክት የተወገዘና ተቀባይነት የሌለው ነው " አለ የትግራይ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ።
ጉባኤው የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ሲል በፅኑ ተማፅኗል።
" ህዝብን በማሳተፍ ለሰላም ፣ ለፍቅር ለፍትህና ለአንድነት እሰራለሁ " ሲል ያሳወቀው ጉባኤው " በመሪዎች መካከል የተፈጠረው ተግባብቶ ያለመስራት ችግር ህዝቡ ለስደት፣ ለመፈናቀልና ለሞት የዳረገ የሚወገዝ ተግባር ነው " ብሏል።
" ገና ከጦርነት ባለገገመች ትግራይ ትግራዋይ ከትግራዋይ ለመተላለቅ ያለመ ፕሮጀክት ተደግሷል " ያለው ጉባኤው " ይህ አደገኛ ፕሮጀክት ለትግራይ ህዝብ ታሪክ የማይመይጥን ነው " ብሎታል።
በአገር ውስጥና በመላ ዓለም የሚገኝ ትግራዋይ ሆደ ሰፊና አስተዋይ እንዲሆን መክሮ " በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ በጋራ እንቁም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል" - የዕድሜ ባለፀጋዉ አቶ ማኖ ማገሶ
➡️ " ከአምስተኛ ክፍል የወረዳ አልፎም የአዉራጃ አስተዳዳሪ ሆኜ ነበር ፤ ትክክለኛዉ ዕድሜዬ 91 ነዉ ! "
አቶ ማኖ ማገሶ የ85 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ዘንድሮ በሁለተኛዉ ዙር የፈተና ፕሮግራም ከካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካቀኑ የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ ናቸዉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በልጃቸዉ በኩል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።
ከልጅ ልጃቸዉ ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልፀዉ " ትምህርት በዕድሜ ሊገደብ አይገባም " ሲሉ ሃሳባቸው አጋርተዋል።
የ5 ወንዶችና የ6ሴቶች የ11 ልጆች አባት እንደሆኑ የገለፁት አቶ ማኖ በንጉሱ ዘመን በሁለት ዓመት ዉስጥ በነበራቸዉ ቀልጣፋ የትምህርት አቀባበል ክፍል እያጠፉ 5ኛ ክፍል መድረሳቸዉንና ከ5ኛ ክፍል ተወስደዉ የቦንኬ ወረዳ አመራር ተደርገዉ ተሹመዉ እንደነበርና ባሳዩት ጠንካራ አመራርም የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር አስታዉሰዋል።
በኋላም ደርግ መንበረ ስልጣኑን ሲይዝ ለእስር ተዳርገዉ ለ21 ዓመታት በአርባምንጭ ማረሚያ ታስረዉ መቆየታቸዉንና ደርግ ከወደቀ በኋላ ከማረሚያ ወጥተዉ ልጆቻቸዉን በማስተማር ቦታ ቦታ ካስያዙ በኋላ አቋርጠዉ የቆዩትን ትምህርት በመቀጠል ዘንድሮ በትምህርት መረጃ ላይ 85 ዓመት እሳቸዉ " ትክክለኛ ዕድሜዬ ነዉ " በሚሉት 91 ዓመታቸዉ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ከልጅ ልጃቸዉ ጋር አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልጸዋል።
ለትምህርት ካላቸዉ ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በአመራርነት ዘመናቸዉ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እንዳስገነቡ የገለፁት አቶ ማኖ እሳቸዉ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት አግብተዉ ትምህርታቸዉን አቋርጠዉ የነበሩ ልጆቻቸዉን ጭምር ከተፈቱ በኋላ ከባሎቻቸዉ ጭምር እንዲማሩ አድርገዉ በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ዩኒቨርሲቲ እገባለሁ " ብለዋል።
" ትምህርት በእድሜ የማይገደብ የሕይወት ምግብ ነዉ " ሲሉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ማኖ ማገሶን ፅናታቸውን እያደነቀ መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው ይመኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " ከአምስተኛ ክፍል የወረዳ አልፎም የአዉራጃ አስተዳዳሪ ሆኜ ነበር ፤ ትክክለኛዉ ዕድሜዬ 91 ነዉ ! "
አቶ ማኖ ማገሶ የ85 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ዘንድሮ በሁለተኛዉ ዙር የፈተና ፕሮግራም ከካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካቀኑ የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ ናቸዉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በልጃቸዉ በኩል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።
ከልጅ ልጃቸዉ ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልፀዉ " ትምህርት በዕድሜ ሊገደብ አይገባም " ሲሉ ሃሳባቸው አጋርተዋል።
የ5 ወንዶችና የ6ሴቶች የ11 ልጆች አባት እንደሆኑ የገለፁት አቶ ማኖ በንጉሱ ዘመን በሁለት ዓመት ዉስጥ በነበራቸዉ ቀልጣፋ የትምህርት አቀባበል ክፍል እያጠፉ 5ኛ ክፍል መድረሳቸዉንና ከ5ኛ ክፍል ተወስደዉ የቦንኬ ወረዳ አመራር ተደርገዉ ተሹመዉ እንደነበርና ባሳዩት ጠንካራ አመራርም የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር አስታዉሰዋል።
በኋላም ደርግ መንበረ ስልጣኑን ሲይዝ ለእስር ተዳርገዉ ለ21 ዓመታት በአርባምንጭ ማረሚያ ታስረዉ መቆየታቸዉንና ደርግ ከወደቀ በኋላ ከማረሚያ ወጥተዉ ልጆቻቸዉን በማስተማር ቦታ ቦታ ካስያዙ በኋላ አቋርጠዉ የቆዩትን ትምህርት በመቀጠል ዘንድሮ በትምህርት መረጃ ላይ 85 ዓመት እሳቸዉ " ትክክለኛ ዕድሜዬ ነዉ " በሚሉት 91 ዓመታቸዉ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ከልጅ ልጃቸዉ ጋር አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልጸዋል።
ለትምህርት ካላቸዉ ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በአመራርነት ዘመናቸዉ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እንዳስገነቡ የገለፁት አቶ ማኖ እሳቸዉ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት አግብተዉ ትምህርታቸዉን አቋርጠዉ የነበሩ ልጆቻቸዉን ጭምር ከተፈቱ በኋላ ከባሎቻቸዉ ጭምር እንዲማሩ አድርገዉ በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ዩኒቨርሲቲ እገባለሁ " ብለዋል።
" ትምህርት በእድሜ የማይገደብ የሕይወት ምግብ ነዉ " ሲሉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ማኖ ማገሶን ፅናታቸውን እያደነቀ መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው ይመኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" ፈጣሪ ጠብቋቸዉ እንጂ ጉዳቱ የከፋ ሊሆን ይችል ነበር " - የብርብር ከተማ ፖሊስ
ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ የነበረ መኪና የትራፊክ አደጋ አጋጥሞት በሰዉና በንብረት ጉዳት መድረሱን የብርብር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ምትኩ ፉላሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ ከቦሮዳ ወረዳ ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-09846 ደሕ የሆነ FSR መኪና ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ይጓዝ ከነበረ ኮድ 3-32326 ኦሮ ከሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ እንደሆነ አዛዡ አስታዉቀዋል።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ23 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የገለፁት አዛዡ ተጎጅዎችም በብርብር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸዉን ገልፀዋል።
" ከቦታዉ ዳገታማነትና ከመኪኖቹ ፍጥነት አንፃር ሊደርስ ይችል የነበረዉ አደጋ ዘግናኝ ይሆን ነበር " ያሉት ፖሊስ አዛዡ " ፈጣሪ ጠብቋቸዉ የሞት አደጋ እስካሁን አልተከሰተም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ የነበረ መኪና የትራፊክ አደጋ አጋጥሞት በሰዉና በንብረት ጉዳት መድረሱን የብርብር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ምትኩ ፉላሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ ከቦሮዳ ወረዳ ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-09846 ደሕ የሆነ FSR መኪና ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ይጓዝ ከነበረ ኮድ 3-32326 ኦሮ ከሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ እንደሆነ አዛዡ አስታዉቀዋል።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ23 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የገለፁት አዛዡ ተጎጅዎችም በብርብር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸዉን ገልፀዋል።
" ከቦታዉ ዳገታማነትና ከመኪኖቹ ፍጥነት አንፃር ሊደርስ ይችል የነበረዉ አደጋ ዘግናኝ ይሆን ነበር " ያሉት ፖሊስ አዛዡ " ፈጣሪ ጠብቋቸዉ የሞት አደጋ እስካሁን አልተከሰተም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ቶምቦላ ዛሬ እስከ 11 ሰዓት ብቻ!
አዎ! "በ11ኛው ሰዓት ገዝቼ ዛሬ በ11 ሰዓት አሸነፍኩ!" ሊሉ ይችላሉ።
አፍሪካ ህብረት አጠገብ ጃምቦ ሪል ስቴት ያስገነባው ባለ 12 ፎቅ ህንጻ ውስጥ ያሉትን እጅግ ዘመናዊ ባለ ሶስትና ሁለት መኝታ አፓርትመንት ቤቶች እንዲሁም ተወዳጆቹን ቮልስዋገን ID.6 እና BYD Song Plus SUV መኪናዎችን የራስዎ ማድረግ አይፈልጉም?
የቤቶቹ አድራሻ https://maps.app.goo.gl/mgqFwSerUqyBnrZL6?g_st=aw ይሄ ነው። ተገንብተዋል ይገቡባቸዋል! መኪኖቹም ተዘጋጅተዋል ያሽከረክሩዋቸዋል!
እንግዲያውስ ዛሬ እስከ 11 ሰዓት ብቻ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሚወጣውን የቶምቦላ ሎተሪ በ100 ብር በቴሌብር ሱፐር አፕ ሰዓቱ ሳይደርስ አሁኑኑ ይግዙ!
ይቅናዎ!
ለበለጠ መረጃ በ +251977717272 ፣
+251950189808 እና
+251950199808 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
አዎ! "በ11ኛው ሰዓት ገዝቼ ዛሬ በ11 ሰዓት አሸነፍኩ!" ሊሉ ይችላሉ።
አፍሪካ ህብረት አጠገብ ጃምቦ ሪል ስቴት ያስገነባው ባለ 12 ፎቅ ህንጻ ውስጥ ያሉትን እጅግ ዘመናዊ ባለ ሶስትና ሁለት መኝታ አፓርትመንት ቤቶች እንዲሁም ተወዳጆቹን ቮልስዋገን ID.6 እና BYD Song Plus SUV መኪናዎችን የራስዎ ማድረግ አይፈልጉም?
የቤቶቹ አድራሻ https://maps.app.goo.gl/mgqFwSerUqyBnrZL6?g_st=aw ይሄ ነው። ተገንብተዋል ይገቡባቸዋል! መኪኖቹም ተዘጋጅተዋል ያሽከረክሩዋቸዋል!
እንግዲያውስ ዛሬ እስከ 11 ሰዓት ብቻ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሚወጣውን የቶምቦላ ሎተሪ በ100 ብር በቴሌብር ሱፐር አፕ ሰዓቱ ሳይደርስ አሁኑኑ ይግዙ!
ይቅናዎ!
ለበለጠ መረጃ በ +251977717272 ፣
+251950189808 እና
+251950199808 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
" የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አልባ በመሆናቸው ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው " - ማኅበሩ
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር ከአዲስ አበባ ብስራት ፕሮሞሽን ጋር በማበር፣ የመንገድ ላይ ደኅንነትን፣ የትራንስራንስፓርት ተሽከርካሪዎች እና የአገልገሎት መስጫ ተቋማት ተደራሽነት ችግር አካቶ የያዘ "ከቤት እስከ ጎዳና" በሚል ያዘጋጀውን ዶክመንትሪ ፊልም ለመንግስት አካላት በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል አቅርቧል።
በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲ ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንትና ሌሎች ተቋማት ታድመው የነበረ ሲሆን፣ ማኀበሩም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናታዊ ፅሑፍ ጭምር እነዚሁ አካላት ባሉበት አቅርቧል። ባለድርሻ አካላቱም የተለያዩ አስተያየቶችን በመስጠት የተነሱትን ክፍተቶች ለመቅረፍ ቃል ገብተዋል።
በመርሃ ግብሩ የተነሳው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተለይ ለዓይነ ስውራን አደጋ የደቀኑ በመሆናቸው ሕግና ፓሊሲ በማውጣት መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ የሚያሳስብ የነበረ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ መግባት በዓይነ ስውራን የሚያስከትለው ጉዳት ምንድነው? ምንስ መደረግ አለበት? ያለው ክፍተትስ ምንድን ነው? ሲል ማህበሩን ጠይቋል፡፡
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ምን መለሱ ?
" መንግስት በጣም የሚደነግበት ቦታ ቢኖር እዚህ ኤሪያ ላይ ነው፡፡ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ይሄንን ጉዳይ ስናወራቸው ምንም ያላሰቡበት ነገር እንደሆነ ነው የነገሩን።
የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አላባ/ድመጽ አልባ አድርጎ መንዳት የሚችሉ ናቸው፡፡ ይሄ ሲሆን ግን እይታ የሌላቸው ነገር ግን ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው።
መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ለመቀየር እቅድ ይዟል። ይሄንን እቅድ ሲይዝ ግን ቀጥታ የጉዳቱ ሰለባ የሆኑትን ዓይነ ስውራንን ያገናዘበው ፖሊሲም፣ ሕግም ስታንዳርድም የለም፡፡ ይሄ ጉዳይ በአሜሪካ ምክር ቤት ክርክር ተደርጎበት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሙሉ ለሙሉ ድምጽ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስገዳጅ ሕግ ወጥቶለታል።
በኢትዮጵያ ግን ለነዳጅ የምናወጣውን የውጭ ምንዛሬ ስለሚያስቀርልን፣ ኢንቫይሮመንታሊ ፍሬንድ ስለሆኑ በሚል እሳቤ ተሸከርካሪዎቹን ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባናቸው ነው።
መግባቱን ይግቡ ግን ቴክኖሎጅው ሁሉም ነገር የተገጠመለት ነው፤ ነገር ግን እኛ ጋር የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፍ ስለሌለ ዝም ብለን አስገብተን በመንገድ ላይ ጥቅም እንዲሰጡ እያደረግናቸው ነው ያለነው፡፡ ይህ ለዓይነ ስውራን አደገኛ የሆነ አካሄድ ስለሆነ መንግስት ሊያስብበት ይገባል፡፡
ምክንያቱም ተሽከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው መጥተው ሲገጩን ብቻ ነው የምናውቀው፡፡ አንድ ዓይነ ስውር በሚጓዝበት ወቅት አደጋ መኖርና አለመኖሩን የሚለየው ድምጽ በመስማትና በነጭ ብትሩ በመዳበስ ነው" ብለዋል።
በአጠቃላይ በዘርፉ ስላለው ችግር ሲያስረዱም፣ "የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው ዓይነ ስውራን ራሱ ቢገቡባቸውና/ቢጋጩ የአሽከርካሪዎች ኃላፊነት ከፍተኛ ድርሻ ስለሚይዝ ሊጣል የሚገባው ካሳ ሊቀንስልኝ ይገባል በሚል ክርክር ውሳኔው ምንድን ነው? በሚለው ዙሪያ በዓይነ ስውራን ወገኖች ረገድ ሕግ የለም " ነው ያሉት።
የመፍትሄውን ሃሳብ በተመለከተ ለጊዜው መንግስት በዚሁ ረገድ ሰርኩላር በትኖ የቁጥጥር ስልቱን መንደፍና መተግበር፣ በዘላቂነትም የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ ሕግና ፖሊሲ እንዲያወጣም አሳስበዋል፡፡
(ተጨማሪ አለን በቀጣይ ይቀርባል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር ከአዲስ አበባ ብስራት ፕሮሞሽን ጋር በማበር፣ የመንገድ ላይ ደኅንነትን፣ የትራንስራንስፓርት ተሽከርካሪዎች እና የአገልገሎት መስጫ ተቋማት ተደራሽነት ችግር አካቶ የያዘ "ከቤት እስከ ጎዳና" በሚል ያዘጋጀውን ዶክመንትሪ ፊልም ለመንግስት አካላት በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል አቅርቧል።
በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲ ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንትና ሌሎች ተቋማት ታድመው የነበረ ሲሆን፣ ማኀበሩም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናታዊ ፅሑፍ ጭምር እነዚሁ አካላት ባሉበት አቅርቧል። ባለድርሻ አካላቱም የተለያዩ አስተያየቶችን በመስጠት የተነሱትን ክፍተቶች ለመቅረፍ ቃል ገብተዋል።
በመርሃ ግብሩ የተነሳው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተለይ ለዓይነ ስውራን አደጋ የደቀኑ በመሆናቸው ሕግና ፓሊሲ በማውጣት መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ የሚያሳስብ የነበረ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ መግባት በዓይነ ስውራን የሚያስከትለው ጉዳት ምንድነው? ምንስ መደረግ አለበት? ያለው ክፍተትስ ምንድን ነው? ሲል ማህበሩን ጠይቋል፡፡
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ምን መለሱ ?
" መንግስት በጣም የሚደነግበት ቦታ ቢኖር እዚህ ኤሪያ ላይ ነው፡፡ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ይሄንን ጉዳይ ስናወራቸው ምንም ያላሰቡበት ነገር እንደሆነ ነው የነገሩን።
የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አላባ/ድመጽ አልባ አድርጎ መንዳት የሚችሉ ናቸው፡፡ ይሄ ሲሆን ግን እይታ የሌላቸው ነገር ግን ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው።
መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ለመቀየር እቅድ ይዟል። ይሄንን እቅድ ሲይዝ ግን ቀጥታ የጉዳቱ ሰለባ የሆኑትን ዓይነ ስውራንን ያገናዘበው ፖሊሲም፣ ሕግም ስታንዳርድም የለም፡፡ ይሄ ጉዳይ በአሜሪካ ምክር ቤት ክርክር ተደርጎበት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሙሉ ለሙሉ ድምጽ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስገዳጅ ሕግ ወጥቶለታል።
በኢትዮጵያ ግን ለነዳጅ የምናወጣውን የውጭ ምንዛሬ ስለሚያስቀርልን፣ ኢንቫይሮመንታሊ ፍሬንድ ስለሆኑ በሚል እሳቤ ተሸከርካሪዎቹን ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባናቸው ነው።
መግባቱን ይግቡ ግን ቴክኖሎጅው ሁሉም ነገር የተገጠመለት ነው፤ ነገር ግን እኛ ጋር የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፍ ስለሌለ ዝም ብለን አስገብተን በመንገድ ላይ ጥቅም እንዲሰጡ እያደረግናቸው ነው ያለነው፡፡ ይህ ለዓይነ ስውራን አደገኛ የሆነ አካሄድ ስለሆነ መንግስት ሊያስብበት ይገባል፡፡
ምክንያቱም ተሽከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው መጥተው ሲገጩን ብቻ ነው የምናውቀው፡፡ አንድ ዓይነ ስውር በሚጓዝበት ወቅት አደጋ መኖርና አለመኖሩን የሚለየው ድምጽ በመስማትና በነጭ ብትሩ በመዳበስ ነው" ብለዋል።
በአጠቃላይ በዘርፉ ስላለው ችግር ሲያስረዱም፣ "የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው ዓይነ ስውራን ራሱ ቢገቡባቸውና/ቢጋጩ የአሽከርካሪዎች ኃላፊነት ከፍተኛ ድርሻ ስለሚይዝ ሊጣል የሚገባው ካሳ ሊቀንስልኝ ይገባል በሚል ክርክር ውሳኔው ምንድን ነው? በሚለው ዙሪያ በዓይነ ስውራን ወገኖች ረገድ ሕግ የለም " ነው ያሉት።
የመፍትሄውን ሃሳብ በተመለከተ ለጊዜው መንግስት በዚሁ ረገድ ሰርኩላር በትኖ የቁጥጥር ስልቱን መንደፍና መተግበር፣ በዘላቂነትም የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ ሕግና ፖሊሲ እንዲያወጣም አሳስበዋል፡፡
(ተጨማሪ አለን በቀጣይ ይቀርባል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አልባ በመሆናቸው ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው " - ማኅበሩ የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር ከአዲስ አበባ ብስራት ፕሮሞሽን ጋር በማበር፣ የመንገድ ላይ ደኅንነትን፣ የትራንስራንስፓርት ተሽከርካሪዎች እና የአገልገሎት መስጫ ተቋማት ተደራሽነት ችግር አካቶ የያዘ "ከቤት…
" ከ47 በመቶ በላይ አሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ ነው የሚያሽከረክሩት ! "
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበር ዘርፉን በተመለከተ አዘጋጅቶት በነበረው መድረክ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጀመንት ባለስልጣን መጥተው የነበሩት አቶ ደረጀ የተባሉ አካል " በየዓመቱ ከ2000 እስከ 300ዐ ለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጡ፣ ኢንፍራስትራክቸር በተለይ ለአካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተይዞ መሰራት እንዳለበት፣ አቅም በፈቀደ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
" ነገር ግን የትራፊክ ግጭቱ ስታቲስቲክሱ ሲታይ በዓመት አዲስ አበባ ከተማ ብቻ 401 ሰው ይሞታል። በአመት 401 ሰው ይሞታል ማለት በቀን ከ1 ሰው በላይ ይሞታል ማለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የሚፈጠረው ግጭት ደግሞ መቆጣጠር የሚቻል፤ በሰዎች ስህተት የሚፈጠር እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት "ብለዋል።
" አንድ ክርክር አለ የትራፊክ አደጋ ነው ወይስ ግጭት ነው? የሚል። ከ95 በመቶ በላይ በሰዎች ባህሪ ላይ ሰርተን ለውጥ ማምጣት፤ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የወጡ ህጎችን ማክበር የምንችል ከሆነ ግጭቶችን መቀነስ የምንችልበት እድል ሰፊ ስለሆነ አደጋ ተብሎ ሊያዙ የሚገባ አይደሉም የሚል መከራከሪያ ይነሳል " ነው ያሉት።
" እውነት ነው፤ አንደኛው በአዲስ አበባ ላይ የግጭት አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ፍጥነት ነው። ከ47 በመቶ በላይ አሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ ነው የሚያሽከረክሩት " ብለው፣ " ስለዚህ አንድ አካል ጉዳተኛ ዜብራ መንገድ እያቋረጠ እያለ በፍጥነት የሚመጣ አሽከርካሪ ተሽከርካሪውን ተቆጣጥሮ ከአደጋው ሊታደገው አይችልም " ሲሉም ተናግረዋል።
በመዲናዋ በመኪና አደጋ ግጭት ጭምር በየጊዜው የበርካቶች ሕይወት እንደሚያልፍ፣ በተለይ ዓይነ ስውራን ደግሞ ለዚህ ተጋላጭ እንደሆኑ ይነገራል፤ ጥናት አድርጋችሁ ነበር? ማኀበሩ ባለው መረጃ መሠረት ስንት ዓይነ ስውራን በዚሁ አደጋ ሞተዋል? ስንልም የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበርን ጠይቀናል።
የማበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ምላሽ፣ " የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአካል ጉዳተኞች ሰብዓዊ መብቶች ቃል ኪዳን አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ዳታ ሊኖራቸው እንደሚገባ በመንግስታት ላይ ግልጽ የሆነ ግዴታ ይጥላል። ነገር ግን በመንግስት በኩል እንደዚህ አይነት የተደራጀ አሰራር የለም " ብለዋል።
" እንደ ኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኅበር ከጥር 18 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ብዙ የመኪና ሞት አደጋዎች መድረሳቸውን ያለን መረጃ ያሳያል (ይህ ከአዲስ አበባ ውጪ የሚያጋጥሙትን የሚያካትት አይደለም)። አደጋው ከፍተኛ ነው ማለት እንችላለን " ብለዋል።
" በጥር 18/2016 ዓ/ም አንድ የሞት አደጋ ሁለት ከባድ የአካል ጉዳት፣ በመጋቢት ለሚኩራ አንድ የሞት አደጋ ደርሶ ነበር፣ በሚያዚያ ወርም የሞት አደጋ ደርሷል፣ በመስከረም 2017 ዓ/ም በዓይነ ስውራን ላይ የሞት አደጋ ደርሷል፤ በሚያዚያ 2017 ዓ/ም በኮየ ፈጬ አንድ የሞት አደጋ ተመዝግቧል። አደጋው ከፍ እያለ እንደሆነ ነው የሚያሳየው " ነው ያሉት።
የችግሩ ምክንያቶች ሁለት እንደሆኑ በጥናት መዳሰሱን ገልጸው፣ "አንደኛው የኢንፍራስትራክቸር ችግር፤ ሁለተኛ ደግሞ Unsafe የሆነ የአሽከርካሪዎች አነዳድ እንደሆነ በጥናቱ ተመልክቷል" ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበር ዘርፉን በተመለከተ አዘጋጅቶት በነበረው መድረክ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጀመንት ባለስልጣን መጥተው የነበሩት አቶ ደረጀ የተባሉ አካል " በየዓመቱ ከ2000 እስከ 300ዐ ለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጡ፣ ኢንፍራስትራክቸር በተለይ ለአካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተይዞ መሰራት እንዳለበት፣ አቅም በፈቀደ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
" ነገር ግን የትራፊክ ግጭቱ ስታቲስቲክሱ ሲታይ በዓመት አዲስ አበባ ከተማ ብቻ 401 ሰው ይሞታል። በአመት 401 ሰው ይሞታል ማለት በቀን ከ1 ሰው በላይ ይሞታል ማለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የሚፈጠረው ግጭት ደግሞ መቆጣጠር የሚቻል፤ በሰዎች ስህተት የሚፈጠር እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት "ብለዋል።
" አንድ ክርክር አለ የትራፊክ አደጋ ነው ወይስ ግጭት ነው? የሚል። ከ95 በመቶ በላይ በሰዎች ባህሪ ላይ ሰርተን ለውጥ ማምጣት፤ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የወጡ ህጎችን ማክበር የምንችል ከሆነ ግጭቶችን መቀነስ የምንችልበት እድል ሰፊ ስለሆነ አደጋ ተብሎ ሊያዙ የሚገባ አይደሉም የሚል መከራከሪያ ይነሳል " ነው ያሉት።
" እውነት ነው፤ አንደኛው በአዲስ አበባ ላይ የግጭት አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ፍጥነት ነው። ከ47 በመቶ በላይ አሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ ነው የሚያሽከረክሩት " ብለው፣ " ስለዚህ አንድ አካል ጉዳተኛ ዜብራ መንገድ እያቋረጠ እያለ በፍጥነት የሚመጣ አሽከርካሪ ተሽከርካሪውን ተቆጣጥሮ ከአደጋው ሊታደገው አይችልም " ሲሉም ተናግረዋል።
በመዲናዋ በመኪና አደጋ ግጭት ጭምር በየጊዜው የበርካቶች ሕይወት እንደሚያልፍ፣ በተለይ ዓይነ ስውራን ደግሞ ለዚህ ተጋላጭ እንደሆኑ ይነገራል፤ ጥናት አድርጋችሁ ነበር? ማኀበሩ ባለው መረጃ መሠረት ስንት ዓይነ ስውራን በዚሁ አደጋ ሞተዋል? ስንልም የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበርን ጠይቀናል።
የማበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ምላሽ፣ " የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአካል ጉዳተኞች ሰብዓዊ መብቶች ቃል ኪዳን አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ዳታ ሊኖራቸው እንደሚገባ በመንግስታት ላይ ግልጽ የሆነ ግዴታ ይጥላል። ነገር ግን በመንግስት በኩል እንደዚህ አይነት የተደራጀ አሰራር የለም " ብለዋል።
" እንደ ኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኅበር ከጥር 18 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ብዙ የመኪና ሞት አደጋዎች መድረሳቸውን ያለን መረጃ ያሳያል (ይህ ከአዲስ አበባ ውጪ የሚያጋጥሙትን የሚያካትት አይደለም)። አደጋው ከፍተኛ ነው ማለት እንችላለን " ብለዋል።
" በጥር 18/2016 ዓ/ም አንድ የሞት አደጋ ሁለት ከባድ የአካል ጉዳት፣ በመጋቢት ለሚኩራ አንድ የሞት አደጋ ደርሶ ነበር፣ በሚያዚያ ወርም የሞት አደጋ ደርሷል፣ በመስከረም 2017 ዓ/ም በዓይነ ስውራን ላይ የሞት አደጋ ደርሷል፤ በሚያዚያ 2017 ዓ/ም በኮየ ፈጬ አንድ የሞት አደጋ ተመዝግቧል። አደጋው ከፍ እያለ እንደሆነ ነው የሚያሳየው " ነው ያሉት።
የችግሩ ምክንያቶች ሁለት እንደሆኑ በጥናት መዳሰሱን ገልጸው፣ "አንደኛው የኢንፍራስትራክቸር ችግር፤ ሁለተኛ ደግሞ Unsafe የሆነ የአሽከርካሪዎች አነዳድ እንደሆነ በጥናቱ ተመልክቷል" ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር እንደሆነ ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተነግሯል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ ነው።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ።
አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር እንደሆነ ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተነግሯል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ ነው።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ።
አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
19 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !
ታዳጊዋ አያንቱ ቱና ላይ የግበረስጋ ድፍረት የፈጸመው ግለሰብ በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ የ13 ዓመቷን ታዲጊ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረውና በፖሊስ ተባባሪነት ጭምር አምልጦ ከ1 ዓመት በላይ ተሰዉሮ የነበረዉ ወጣት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ መረጃው ከተሰራጨ በኋላ በተደረገ ክትትልና ፍለጋ ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ዉሎ ክስ ተመስርቶበት እንደነበር የአያንቱ ታላቅ ወንድም ወጣት ጴጥሮስ ቱና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይኸው ግለሰብ አርብ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የአያንቱ ወንድም ተናግሯል።
የሻፋሞ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሴ ፉና ስለጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " የወረዳዉ ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ ያቀረቡትን ጠንከር ያለ ምርመራ፣ የሰነድ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎችን የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት ግለሰቡን ጥፋተኛ ነዉ በማለት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል " ብለዋል።
" ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማቆያ ዉስጥ የምትገኘዉ አያንቱ ደፋሪዋ እንደተያዘ ከተነገራት በኋላ ጥሩ መሻሻል ታይቶባታል " የሚለዉ የታዳጊዋ ወንድም ጴጥሮስ " ከዚህ በኋላ ከማቆያ ወጥታ ወደ ትምህርት ገበታዋ ትመለሳለች " ብሏል
" የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ለታዳጊዋ ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
19 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !
ታዳጊዋ አያንቱ ቱና ላይ የግበረስጋ ድፍረት የፈጸመው ግለሰብ በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ የ13 ዓመቷን ታዲጊ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረውና በፖሊስ ተባባሪነት ጭምር አምልጦ ከ1 ዓመት በላይ ተሰዉሮ የነበረዉ ወጣት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ መረጃው ከተሰራጨ በኋላ በተደረገ ክትትልና ፍለጋ ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ዉሎ ክስ ተመስርቶበት እንደነበር የአያንቱ ታላቅ ወንድም ወጣት ጴጥሮስ ቱና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይኸው ግለሰብ አርብ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የአያንቱ ወንድም ተናግሯል።
የሻፋሞ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሴ ፉና ስለጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " የወረዳዉ ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ ያቀረቡትን ጠንከር ያለ ምርመራ፣ የሰነድ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎችን የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት ግለሰቡን ጥፋተኛ ነዉ በማለት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል " ብለዋል።
" ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማቆያ ዉስጥ የምትገኘዉ አያንቱ ደፋሪዋ እንደተያዘ ከተነገራት በኋላ ጥሩ መሻሻል ታይቶባታል " የሚለዉ የታዳጊዋ ወንድም ጴጥሮስ " ከዚህ በኋላ ከማቆያ ወጥታ ወደ ትምህርት ገበታዋ ትመለሳለች " ብሏል
" የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ለታዳጊዋ ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia